05/04/2026
... የዝች የልጅ እናት ስቃይ አይቶ የሚያሳልፍ ሰው፣ እውነት ሰው አይደለም💔🤔
--
.እቺ እንዲህ ፊትዋ አብጦ ልጅዋን ምታጠባ ያለችው፣ እናት እያያችሁ እንዴት ዝም ብላችሁ ታልፋላችሁ?
#ሼር አድርጉላት🙏
(ክፉዎች ግን ዝም ብላችሁ እለፉ)
"ነገም በኔ ነው"
-
.........................🤲🤲🤲.............................
-🤲-
-🤲-
🌐ዩቲዩብ ቻናሌ Subscribe አድርጉ🌐
https://www.youtube.com/
╭══✧•|❀:✧๑♡๑๑♡๑✧❀|: ✧══╮
Yared Hiruy - ያሬድ ህሩይ
╰══✧•ೋ•✧๑♡๑๑♡๑✧• ✧══╯
👍 🔗 💬
14/02/2026
😭
(እባክዎ መልዕክቱን ሼር ያድርጉ)
ይህች የምታይዋት እህታችን ቤዛ ምንዳ ትባላለች። በቸርች ያደገች በደንብ የተማረች የማስተርስ ዲግሪ ያላት ጥሩ ስራ የነበራት እህት ነች። ከእለታት በአንድ ቀን ግን አዳማ ስብሰባ ላይ እያለች በጣም አሟት ሆስፒታል ስትሄድ ሁለቱም ኩላሊቶቿ ፌል እንዳደረጉ ተነገራት። ከዛ ጊዜ ጀምሮ የበራው ነገዋ ጨልሞ፣ ህልሟ ጠፍቶ የአልጋ ቁራኛ ሆና ቤት ከዋለች አመት ሊሞላት ነው። ከዚህ በፊት የዚህችን እህታችንን አሳዛኝ ታሪክ ሰዎች ነግረውን አዳማ ድረስ ሄደን ያለችበትን ሁኔታ ወደ እናንተ አድርሰን ነበር።
ቤዛ በዛን ጊዜ ወንድሟ ኩላሊት እንደሚሰጣት ከእሷ ጋርም ኩላሊቱ ማች እንዳደረገ በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታልም ንቅለ ተከላውን ማድረግ እንደምትችል እንደተነገራት ያን ለማድረግ ግን ገንዘብ የቅም እንደሌላት ነግራን እኛም ነገሩን ወደእናንተ አድርሰን ብዙዎቻችሁ የአቅማችሁን ደግፋችኋት ነበር። እህታችን ቤዛ ጌታ ረድቷት እናንተም አግዛችኋት የኩላሊት ንቅለ ተከላዋን ለማድረግ ብዙ ፕሮሰሶችን ከሄደች በኋላ ግን ያልጠበቀችው ዱብዳ ተፈጠረ
እንግዲህ እንደሰማችሁት ይህች ለሀገር ለምድር ለቤተሰብ ለቤተክርስቲያን ልትጠቅም የምትችል እህት ህንድ ሀገር ሄዳ በፍጥነት ንቅለተከላዋን ካላደረገች በህይወት እናጣታለን እሷ በራሷ አቅም እንኳን ውጭ ሀገር ሄዳ ልትታከም ለዲያሊሲስ እና ለመድሀኒቶች የምታወጣው ወጭ ራሱ ከአቅሟ በላይ ሆኗል። ይህች ወጣት የተማረች ልጅ በገንዘብ እጦት ምክንያት የሞቷን ቀን እየጠበቀች ትገኛለች። እናም ይሄን የምትመለከቱ በጌታ የተወደዳችሁ ቅዱሳን የአቅማችኋን እንድትደግፏት እንለምናችኋለን👏 የጎፈንድ ሚ አካውንቷም እዚህ ላይ ይገኛል።
CBE Account Number: 1000106311618
Name: Bezawit Menda Beyene.
እባካችሁ መልዕክቱን ሼር በማድረግ አግዟት😭
07/02/2026
#በኢትዮጵያ ታሪክ ከ12 ጊዜ በላይ ኬሞ ኖሮት አያውቅም። ነገር ግን በእግዚአብሔር ቸርነት ከ36 ዙር በላይ ኬሞዎችን አድርጓል። ለመኖር እየታገለ ያለ ወንድማችን ነው። በጡት ካንሰር የሚሰቃየውን ወንድማችንን እንርዳው። በጊፍት ለምተረዱ ገቢዉ ለእሱ ነዉ 😭,እባካችሁ 🙏
17/09/2025
ታዋቂው ጉምቱ ፖለቲከኛ ወንድማችን ክርስቲያን ታደለ በህመም ምክንያት ጤናው በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ ስለሆነ ተገቢውን ህክምና እንዲያገኝና ትኩረት በመንግስት በኩል እንዲሰጠው እንጠይቃለን ።ወንድማችን እግዚአብሔር ፈውሱን ይላክልህ።
03/09/2021
#በመነጋገር በመግባባት በጠረጴዛ ዙርያ የሀሣብ ልዩነትን በውይይት መፍታት የስልጡንነት መገለጫ ነው።
31/05/2021
#የሁሉም ነገር መነሻ እውቀት ነው፡፡የስልጣኔ መሥፈንጠርያ የእድገት ማማ ከፍታ የሚደረሰው በትምህርት ነው፡፡ትምህርት የድንቁርና ጨለማን በመግፈፍ የስልጣኔን ጮራ የሚያሣይና የሚፈነጥቅ የህይወት ብርሀን ነው፡፡
07/04/2021
የምዥጋ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት "የአለም ስፖርት ቀንን"ለመጀመርያ ጊዜ በት/ቤት ደረጃ አከበረ፡፡
"ስፖርት ለጤንነት፣ስፖርት ለአንድነትና ለወዳጅነት" የበአሉ መሪ ቃልም ነበር፡፡የምዥጋ ክላስተር ሱፐርቫይዘር በበአሉ ላይ ተገኝተው እንደተናገሩት "ስፖርት ለጤንነት ብቻ ሳይሆን አንድነታችንን ለማጠናከርና ሰላምን ለማስፈን በት/ቤት ደረጃና በአገር ብሎም በአለም አቀፍ ደረጃ የላቀ ሚና እንደሚጫወት"ገልፀዋል፡፡
በኮሮና ቫይረስየተቀዛቀዘውን የስፖርት ትምህርትና የተለያዩ ውድድሮችን በክላስተር ደረጃ ወቅቱን ባማከለ መልኩ እንደሚሠጥ ገልፀዋል፡፡