18/06/2026
የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አሰራሩን በዘመነ መልኩ መሥራት ከሚያሥችለው ተቋም ጋር በጋራ መሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ።
(ሰኔ11/2018 ዓ.ም)
የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሥራዎችን ዲጅታል ቴክኖሎጂን
በመጠቀም የተሳለጠ ሥራ ማከናዎን ከሚያስችለው "ከኢትዮ ቴሌኮም" ምዕራብ ሪጅን አሶሳ ቅርንጫፍ በጋራ ለመስራት የሚያሥችል የመግባቢያ ሥምምነት /MOU/በዛሬው ዕለት ተፈራርመዋል።
ይህም ሥምምነት ኮሌጁ የዕለት ተዕለት ሥራዎቹን በማዘመንና የሰለጠነ የሰው ኃይልን በቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ ቀልጣፋ አሰራርና አስተማማኝ የመረጃ አያያዝ ከመፍጠሩም በላይ ኮሌጁን ወጀ ዲጅታል ተቋም የመቀየር እሳቤውን እንደሚያፋጥን ተመላክቷል።
ዘገባው የኮሌጁ ህዝብ ግንኙነት ነው!
=============//==========
12/06/2026
በአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አካታች የሙያ ሥልጠና የወሰዱ የኮሌጁ ምሩቃን በኢንኩቬሽን ማዕከል ሥልጠና በመውሰድ ላይ ናቸው።
(ሰኔ 5/2018 ዓ.ም አሶሳ)
በአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አካታች የሙያ ሥልጠና በGIZ የገንዘብ ድጋፍ የሰለጠኑ የIVC3 ምሩቃን የ10 ቀን ቆይታ ያለው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና በመሰጠት ላይ ነው።
የስልጠናው ይዘት ትኩረቱን፦በኢንተርፕርነርሽፕ፣በንግድ ሥራ ኃሳብ፣በሕይዎት ክህሎትና በገንዘብ አያያዝ ዙሪያ ሲሆን በዘርፉ የማሰልጠን ፍቃድ ባላቸው አሰልጣኞች ሥልጠናው ተጠናክሮ መቀጠሉን የፕሮግራሙ ዋና አስተባባሪ አሰልጣኝ ገመችስ ገነቲ አብራርተዋል።
ዘገባው የኮሌጁ ህዝብ ግንኙነት ነው!
============//==========
05/06/2026
የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአጫጭር የስልጠና መርሀ-ግብር ያሰለጠናቸውን 160 ሠልጣኞች አሰመረቀ።
(ግንቦት28/2018 ዓ.ም አሶሳ)
የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአጫጭር የሥልጠና መርሀ-ግብር በ8 የሙያ መስኮች ያሠለጠናቸውን ሠልጣኞች ከጀርመን ዓለም አቀፍ የልማት ተራዶ ድርጅት
"GIZ"በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ሲሆን፤ ተመራቂዎቹ ከአካባቢ ማህበረሰብና ከሀገር ውስጥ ተፈናቃይ የተውጣጡ
ወንድ 77 ሴት 83 በድምሩ 160 ሥራ አጥ ወጣቶች መሆናቸውን ተመላክቷል።
በምርቃት ስነ-ስርዓቱ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልእክት ያስተላለፉት የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ዋና ዲን አቶ ተመስጌን ኃይሉ ይህ የሥልጠና መርሀ-ግብር በአካባቢው የሚገኙ ሥራ አጥ ወጣቶች "በሙያ በማብቃት" እራሳቸውን እንዲችሉና በየአካባቢያቸው ለሚስተዋሉ የሥራ እድል እጥረት መፍትሔ ለመስጠት የታሰበ በመሆኑ ሁሉም የዛሬ ተመራቂዎች እንደሰለጠናችሁበት የሙያ መስክ ጠንክሮ በመስራት ሥኬታማ መሆን ይጠበቅባችኋል ብለዋል።
የቤ/ጉ/ክ/መንግስት ሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ የሆኑት አቶ ሠይድ አብዱረሂም በበኩላቸው የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለገበያ ተፈላጊ የሆኑ ልዩ ልዩ የሙያ መስኮች ላይ ትኩረት በማድረግ ከGIZ ጋር በጋራ እየተሰራ ያለው ስራ ውጤታማና አበረታች መሆኑን ገልፀው፤ ለዚህም ማሳያ እናንተ የዛሬ ተመራቂዎች "የሙያ ባለቤት በማድረግ"ማስመረቁ ሌላው ማሳያ ሲሆን ከዚህ በፊት የተመረቁ ሠልጣኞች ከሥራ ጋር ተሳሥረው ውጤት እያስመዘገቡ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
በዚሁ ፕሮግራም ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተውበታል።
ዘገባው የኮሌጁ ህዝብ ግንኙነት ነው!
*************//**************
03/06/2026
የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በተቋሙ የውስ በጀት በመጠቀም "የICT"ማዕከሉን በማደስ ምቹ የማሰልጠኛ ማዕከል ማድረግ ተችሏል።
26/05/2026
የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ተመስጌን ኃይሉ ለመላው
እንኳን #ለ1447ኛ ዓመተ-ሂጅራ #የዒድ አል-አድሃ( #አረፋ)
በዓል በሠላም አደረሳችሁ አደረሰን በማለት የመልካም ምኞት መግለጫቸውን አስተላልፈዋል።
አቶ ተመስጌን የአረፋ በዓል ሲከበር የተለመደ የመረዳዳት
ባህላችን በማሰብ ካለን ላይ ለተቸገሩት በማካፈል ሊሆን ይገባል ብለዋል።
በመጨረሻም በዓሉ የሠላም፣የደስታና የመተሳሰብ ይሆን ዘንድ ተመኝተዋል። በድጋሜ መልካም በአል!!
።
26/05/2026
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ-መዲና በአሶሳ ከተማ የብልፅግና ፖርቲ በጠራው የድጋፍ ሰልፍ የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የስታፍ አባላት በድጋፍ ሰልፉ የተሳተፉ በከፊል።
ግንቦት 18
2018 ዓ.ም
አሶሳ
* * *