አሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ Assosa Polytechnic College

  • Home
  • Ethiopia
  • Asosa
  • አሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ Assosa Polytechnic College

አሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ Assosa Polytechnic College ወቅታዊ የአሶሳ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መረጂያዎችን ተደራሽ ማድረግ።

የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የክረምት በጎ ፍቃድ የሥራ አካል የሆነውን የአቅመ-ደካሞች ቤት ግንባታ ተረከበ።              (ነሐሴ 12/2018 ዓ.ም አሶሳ)  የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ...
18/08/2026

የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የክረምት በጎ ፍቃድ የሥራ አካል የሆነውን የአቅመ-ደካሞች ቤት ግንባታ ተረከበ።

(ነሐሴ 12/2018 ዓ.ም አሶሳ)

የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የክረምት በጎ ፈቃድ የሥራ አካል አንዱ የሆነውን የአቅመ-ደካሞች ቤት ግንባታ፤ በኮሌጁ የገንዘብ ምንጭ ለመገንባት ከአሶሳ ከተማ አስተዳደር የወረዳ አንድ ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ አሙና አብዱልዋሂድ
እና ሌሎች የወረዳው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ደረጃውን የጠበቀ ሁለት ክፍል ቤት ለመገንባት የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ምክትል ዲን አቶ ግዛቸው በጋንፄ በዛሬው እለት የተረከቡ ሲሆን፤በርክክቡ ወቅትም አቶ ግዛቸው በታቀደለት የጊዜ ገደብ ሰርተው እንደሚያስረክቡ ገልጸዋል።

ዘገባው የኮሌጁ የህዝብ ግንኙነት ነው!
==============//=========

በአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለግብርና ናሙና ጥናት መረጃ ሰብሣቢዎችና ተቆጣጣሪዎች ሥልጠና መስጠት ተጀመረ።                (ንሐሴ 7/2018 ዓ.ም  አሶሳ)  በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሚ...
13/08/2026

በአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለግብርና ናሙና ጥናት መረጃ ሰብሣቢዎችና ተቆጣጣሪዎች ሥልጠና መስጠት ተጀመረ።

(ንሐሴ 7/2018 ዓ.ም አሶሳ)

በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሚካሔደው የገጠርና ከተማ ግብርና ናሙና ጥናት ለሚሰማሩ መረጃ ሰብሣቢዎች፣የመስክ ተቆጣጣሪዎችና እስታቲሽያኖች የሚሰጠው ስልጠና ዛሬ በአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መካሔድ ጀምሯል።

በስልጠናው የማስጀመሪያ መርሐ-ግብር ላይ የአሶሳ እስታቲክስ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ተወካይ አቶ ደሳለኝ ዶጃ እንደገለጹት፤ለ20 ተከታታይ ቀናት በሚቆየው የሥልጠና መርሐ ግብር ሰልጣኞች "ጥናቱ" በሀገር አቀፍ ደረጃ ፋይዳው ከፍተኛ መሆኑን በመረዳት ሥልጠናውን በትኩረትና በአግባቡ መከታተል እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ተመስጌን ኃይሉ በበኩላቸው፤ ኮሌጁ ለስልጠናው ሥኬታማነት ምቹ የመሰልጠኛ ከፍሎች መዘጋጀታቸውን ጠቅሰው፣ በቆይታችሁ ወቅት የሚያጋጥሙ ችግሮች ቢኖሩ እንኳን በጋራ ለመፍታት ዝግጁ መሆናቸውን ገለጸው፤ መልካም የሥልጠና ጊዜን ተመኝተዋል።

ዘገባው የኮሌጁ ህዝብ ግንኙነት ነው!
****************//***********

 ( ) መመዘን ለምትፈልጉ በሙሉ ከዚህ በታች በተገለጸው ማስታወቂያ መሰረት የምትስተናገዱ መሆኑን እንገልጻለን።                             !
13/08/2026


( ) መመዘን ለምትፈልጉ በሙሉ ከዚህ በታች በተገለጸው ማስታወቂያ መሰረት የምትስተናገዱ መሆኑን እንገልጻለን።

!

የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሠራተኞች ገበያ ተኮር ችግኞችን በዘመቻ ተከሉ።              (ነሐሴ 5/2018 ዓ.ም አሶሳ)  የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሠራተኞች በተቋሙ ግቢ ውስጥ ገበያ...
11/08/2026

የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሠራተኞች ገበያ ተኮር ችግኞችን በዘመቻ ተከሉ።

(ነሐሴ 5/2018 ዓ.ም አሶሳ)

የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሠራተኞች በተቋሙ ግቢ ውስጥ ገበያ ተኮር የሆኑ የተለያዩ የአትክልት አይነቶች በዘመቻ ተከሉ።

በእለቱ በተካሔደው የችግኝ ተከላ መርሐ-ግብር ችግኞችን በክላስተር በማደራጀት የሙዝ፣ የፓፓያ፣የዘይቱንና እንዲሁም የቡና ክላስተርን ጨምሮ ዝርያቸው የተጠና ሌሎች ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ያላቸው እፅዋቶች በግቢው ውስጥ ተተክለዋል።

በዚሁ መርሐ-ግብር ላይ የኮሌጀ ዲን አቶ ተመስጌን ኃይሉ እንደገለጹት፤የተካሔደው የችግኝ ተከላ ፕሮግራም አካባቢን ከማስዋብ ባሻገር በዘላቂነት ለኮሌጁ ተጨማሪ የገቢ ምንጭ እንዲሆን ታስቦ የተከናወነ መሆኑን አብራርተዋል።

አክለውም አቶ ተስጌን ይህ እንቅስቃሴ ኮሌጁ የገቢ አቅም ለማጠናከር እና የተፈጥሮ ሀብትን ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም ከማዋል ባለፈ ዘርፈ-ብዙ ፋይዳውን በመረዳት ጭምር መሆኑንም አመላክተዋል።

ዘገባው የኮሌጁ የህዝብ ግንኙነት ነው!
=============//==========

የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለ20 የሩሐማ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የቴክኖሎጂ ሥልጠና መስጠት ጀመረ።               (ነሐሴ 4/2018 ዓ.ም አሶሳ)  የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የክምት...
10/08/2026

የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለ20 የሩሐማ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የቴክኖሎጂ ሥልጠና መስጠት ጀመረ።

(ነሐሴ 4/2018 ዓ.ም አሶሳ)

የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የክምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል በማድረግ ለ20 የሩሐማ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ለአንድ ወር የሚቆይ የቴክኖሎጂ ሥልጠና በዛሬው ዕለት መሥጠት ጀመረ።

ሥልጠናውን የኮሌጁ ዲን አቶ ተመስጌን ኃይሉ ያሥጀመሩ ሲሆን በኮሌጁ ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT)ትምህርት ክፍል በየሳምንቱ ሰኞ፣ረቡዕ እና ዓርብ የሚሰጥ ሲሆን፤በዋናነት
(Java)ፕሮግራሚንግ

(Solid works)ዲዛይን ላይ ትኩረቱን ያደረገ መሆኑን ተመላክቷል።

ዘገባው የኮሌጁ የህዝብ ግንኙነት ነው!
****************//*************

10/08/2026



ነገ ማክሰኞ (ነሐሴ 5 ቀን 2018 ዓ.ም) በግቢያችን የችግኝ ተከላ መርሐ-ገብር ተዘጋጅቷል። በዚሁ እለት በመገኘት የመርሐ-ግብሩ ተሳታፊ እንድትሆኑ ጥሪውን ያስተላልፋል።

!

የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሁለገብ (Holistic)የብቃት ምዘና መስጠት ጀመረ።                (ንሐሴ 4/2018 ዓ.ም አሶሳ)  የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ13 የትምህርት ክፍሎ...
10/08/2026

የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሁለገብ (Holistic)የብቃት ምዘና መስጠት ጀመረ።

(ንሐሴ 4/2018 ዓ.ም አሶሳ)

የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ13 የትምህርት ክፍሎች ያሠለጠናቸውን የደረጃ 4 እና የደረጃ 5 የ2018 ዓ.ም ተመራቂዎች እንዲሁም በመንግስታዊና መንግስታዊ በልሆኑ ተቋማት ባለሙያዎችን ጨምሮ ወንድ 200 ሴት220 በድምሩ 420 ተመዛኞች በዓዲሱ የቴክኒክና ሙያ ምዘና ስርአት መሠረት የሁለገብ (Holistic) የንድፈ-ሐሳብና የተግባር ብቃት ምዘና (Coc) መስጠት ጀምሯል።

ለተከታታይ አራት ቀናት ቆይታ የሚያደርገውን የብቃት ምዘናው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ከልል ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሠይድ አብዱረሂም በቦታው ተገኝተው የጎበኙ ሲሆን፣ የምዘና ሒደቱ የሚሔድበትን ሁኔታም ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

ይህ ምዘናም ተመዛኞች በሥራው ዓለም የሚያስፈልጋቸውን የንድፈ-ሐሳብና የተግባር እውቀትና ክህሎት በአግባቡ መያዛቸውን ለማረጋገጥ የሚረዳና ወሳኝ መሆኑን ተመላክቷል።

ዘገባው የኮሌጁ የህዝብ ግንኙነት የሥራ ክፍል ነው!
===================//============

 ፦
05/08/2026

የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአጫጭር የሥልጠና መርሃ-ግብር በምግብ ዝግጅት ያሠለጠናቸውን  ሴቶች አስመረቀ።               (ሐምሌ 28/2018 ዓ.ም አሶሳ)  የአሶሳ  ፖሊ ቴክኒክ ኮ...
04/08/2026

የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአጫጭር የሥልጠና መርሃ-ግብር በምግብ ዝግጅት ያሠለጠናቸውን ሴቶች አስመረቀ።

(ሐምሌ 28/2018 ዓ.ም አሶሳ)

የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮና በአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር በ3R - 4 -CACE ፕሮጀክት የገንዘብ ድጋፍ ከ3 ወረዳዎች ማለትም ከኦዳ ቡልድጊሉ፣ከሰዳል ወረዳና ማኦ ኮሞ ልዩ ወረዳ የተውጣጡ ሴቶች ሲሆኑ፤

ሰልጣኞች በምግብ ዝግጅት ሙያ መሰልጠናቸውን የሚገልጽ የምስክር ወረቀት ከኮሌጁ ተሠጥቷቸዋል።

በዚሁ መርሃ-ግብር ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሥራና ክህሎት ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሰይድ አብዱረሂም፣
ከቤ/ጉ/ክ/መ/ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ም/ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ድንቅነሽ ማሞ እንዲሁም የኮሌጁ ዲን አቶ ተመስጌን ኃይሉ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን ጨምሮ ተገኝተውበታል።

ዘገባው የኮሌጁ ህዝብ ግንኙነት ነው!
============//==========

የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሠራተኞች በሆሞሻ ወረዳ ፆሬ የስደተኞች ማዕከል የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር አካሔዱ።            (ሆሞሻ ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም)   የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌ...
03/08/2026

የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሠራተኞች በሆሞሻ ወረዳ ፆሬ የስደተኞች ማዕከል የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር አካሔዱ።

(ሆሞሻ ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም)

የአሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሁለቱም ምክትል ዲኖች አቶግዛቸው በጋንፄ እና አቶ አበደታ ደሬሳ ጨምሮ ሌሎች የተቋሙ ሠራተኞችን አካቶ በሆሞሻ ወረዳ በሚገኘው የፆሬ ስደተኞች ማዕከል በመገኘት እንደ ሀገር
" !"በሚል መሪ ቃል መርሃ-ግብር የኮሌጁ ሠራተኞች በችግኝ ተከላው ንቁ ህዝባዊ ተሳትፏቸውን አሳይተዋል።

ይህ የአካባቢን ጥበቃ ለማጠናከርና አረንጓዴ አሻራን ለማሳረፍ ያለመው የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር የኮሌጁ ሠራተኞች ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በጋራ በመሆን ሀገራዊና ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ያደረጉት ተግባራዊ ክዋኔ በስኬት ማከናዎን ተችሏል።

ዘገባው የኮሌጁ ህዝብ ግንኙነት ነው!
***************//*************

Address

Asosa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አሶሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ Assosa Polytechnic College posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category