Mohammed Hanfere High school

Mohammed Hanfere High school Mohammed Hanfere high school is established in 1947 E.C in Aysaita woreda. know in the school there are above 1609 students learn.

የመ/ሐ/ከ/ሁ/ደ/መ/ት/ት ቤት የቴክኖሎጂ ቀንን በማስመልከት ከ 'Project Initiative Ethiopia' ጋር በመተባበር የተማሪ ወላጆች ባሉበት ደማቅ ፕሮግራም አቅርቧል።ፕሮግራሙን ያ...
26/04/2025

የመ/ሐ/ከ/ሁ/ደ/መ/ት/ት ቤት የቴክኖሎጂ ቀንን በማስመልከት ከ 'Project Initiative Ethiopia' ጋር በመተባበር የተማሪ ወላጆች ባሉበት ደማቅ ፕሮግራም አቅርቧል።

ፕሮግራሙን ያስጀመሩት የት/ት ቤቱ ርዕሰ መምህር አቶ ሀቢብ ያሲን ቴክኖሎጂ የመጪው ትውልድ መፃዒ እድል የሚወሰንበት መሆኑን አውስተው ት/ት ቤቱ የቴክኖሎጂ ስራዎችን እንደሚያበረታታ ገልፀዋል።

የአ/ከ/ት/ፅ/ቤት ሐላፊ አቶ ሀቢብ ሐንፈሬ ከተማሪ ወላጆች ለቀረቡ ጥያቄዎች መልስ ሰጥተው መሐመድ ሐንፈሬ ት/ት ቤት የሚያስፈልጉትን የእድሳት ስራ እንዲያከናውን ወላጆች በቻሉት እንዲያግዙና ስራውን ለማስጀመር ጥሪ አቅርበው ሌሎች እገዛ ሊያደርጉ ከሚችሉ ባለድርሻ አካላት ጋርም እንደሚነጋገሩ ገልፀዋል።

ወደፊት ኮሚቴ በማቋቋም ለት/ት ቤቱ አዲስ አካውንት በመክፈት በት/ት ቤቱ የተማሩ፤የት/ት ቤቱ ወዳጆችና የከተማችን ነዋሪዎች በፈቃዳቸው አሻራቸውን የሚያሳርፉበት መንገድ እንደሚመቻች ተጠቁሟል።

የመ/ሐ/ከ/ሁ/ደ/መ/ት/ት ቤት የእግር ኳስ ውድድር ዛሬ በቀን 17/08/2017 አ.ም በይፋ ተጀምሯል።ውድድሩን ያስጀመሩት የት/ት ቤቱ ርዕሰ መምህር ስፖርት በአካልና በስነልቦና ጠንካራ ትው...
25/04/2025

የመ/ሐ/ከ/ሁ/ደ/መ/ት/ት ቤት የእግር ኳስ ውድድር ዛሬ በቀን 17/08/2017 አ.ም በይፋ ተጀምሯል።

ውድድሩን ያስጀመሩት የት/ት ቤቱ ርዕሰ መምህር ስፖርት በአካልና በስነልቦና ጠንካራ ትውልዶችን ለመፍጠር እንደሚረዳ ለተማሪዎች መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ ተማሪዎች ለድል ከመነሳሳት ባሻገር በጥሩ ስነምግባር መጫወት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

ውድድሩ በወጣለት ፕሮግራም መሰረት ለቀጣዮቹ ሁለት ሳምንታት ቀጥሎ የሚከናወን ሲሆን የዳካይቶ ስፖርት ሰልጣኖችም በመክፈቻው ዝግጅት ላይ ትርዒታቸውን አሳይተዋል።

ውድድሮቹን መመልከት የሚፈልጉ የከተማችን ነዋሪዎች ከሰኞ እስከ አርብ ከሰአት 10:00 እና ቅዳሜና እሁድ ጧት 02:00 መታደም እንደሚችሉ በዚህ አጋጣሚ መልዕክት እናስተላልፋለን።

Celebrating my 11th year on Facebook. Thank you for your continuing support. I could never have made it without you. 🙏🤗🎉
22/04/2025

Celebrating my 11th year on Facebook. Thank you for your continuing support. I could never have made it without you. 🙏🤗🎉

😘ትልቁ ቤታችንን ደሳሳ ጎጆ ሳይሆን የእድሳት እንቅስቃሴ ለመጀመር አስተምሮ ለትልቅ ደረጃ ያደረሳቸውን ልጆቹንና ወዳጆቹን በተቻለ መጠን ማስተባበር ይፈልጋል።ውድ የአሳይታ ልጆች፣የአሳይታ ወዳ...
11/04/2025

😘ትልቁ ቤታችንን ደሳሳ ጎጆ ሳይሆን የእድሳት እንቅስቃሴ ለመጀመር አስተምሮ ለትልቅ ደረጃ ያደረሳቸውን ልጆቹንና ወዳጆቹን በተቻለ መጠን ማስተባበር ይፈልጋል።

ውድ የአሳይታ ልጆች፣የአሳይታ ወዳጆች፣በትምህርት ቤቱ የተማራችሁና ትምህርት ቤቱን በሀሳብም በገንዘብም ማገዝ ለምትፈልጉ በሀገር ውስጥም ከሀገር ውጭ ላላችሁ እንቁ ልጆቻችን ጥሪያችንን በአክብሮት እናቀርባለን።

በሀሳብ ማገዝ ለምትፈልጉ:-
ዋና/ር/መ/ር ሀቢብ ያሲን 👉0927376523
ም/ር/መ/ር ኡትባን አህመድ👉 0928319891

በገንዘብ ለምታግዙን እንቁ ልጆቻችን:-
የት/ት ቤቱ የባንክ አካውንት ስም:-መ/ድ ሀንፈሬ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት
የንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 👉 CBE:-1000554816022

"ትልቁ ቤታችንን ደሳሳ ጎጆ ሳይሆን እንታደገው"መሐመድ ሐንፈሬ ትምህርት ቤት በ 1947 አ.ም የተመሰረተ ለአሳይታና አከባቢው ወረዳዎች አገልግሎት የሰጠ/አሁንም እየሰጠ የሚገኝ ጥንታዊ ቤታች...
11/04/2025

"ትልቁ ቤታችንን ደሳሳ ጎጆ ሳይሆን እንታደገው"

መሐመድ ሐንፈሬ ትምህርት ቤት በ 1947 አ.ም የተመሰረተ ለአሳይታና አከባቢው ወረዳዎች አገልግሎት የሰጠ/አሁንም እየሰጠ የሚገኝ ጥንታዊ ቤታችን ነው።

የትምህርት ቤቱ ልጆች ተምረው ለወረዳቸው፣ ለክልላቸው፣ለአጎራባች ክልሎች፣ለሀገራቸው፣ለአህጉራቸውና ለአለማችን ኩራት ለመሆን በቅተዋል።ወደፊትም ይሆናሉ።

ነገር ግን ይህ ትልቁ ቤታችን የቅጥር ግቢው፣ የክፍሎቹ በሮች፤ኮርኒሶቹ፤የተማሪዎቹ ወንበሮች በሙሉ እድሳት የሚሹ በመሆናቸው የመማር ማስተማሩ ሒደት ላይ እክል ፈጥረዋል።ስለሆነም ትምህርት ቤቱ የእድሳት እንቅስቃሴ ለመጀመር አስተምሮ ትልቅ ደረጃ ያደረሳቸውን ልጆቹንና ወዳጆቹን በተቻለ መጠን ማስተባበር ይፈልጋል።

ውድ የአሳይታ ልጆች፣የአሳይታ ወዳጆች፣በትምህርት ቤቱ የተማራችሁና ትምህርት ቤቱን በሀሳብም በገንዘብም ማገዝ ለምትፈልጉ በሀገር ውስጥም ከሀገር ውጭ ላላችሁ እንቁ ልጆቻችን ጥሪያችንን በአክብሮት እናቀርባለን።

በሀሳብ ማገዝ ለምትፈልጉ:-
ዋና/ር/መ/ር ሀቢብ ያሲን 0927376523
ም/ር/መ/ር ኡትባን አህመድ 0928319891

በገንዘብ ለምታግዙን እንቁ ልጆቻችን:-
የት/ት ቤቱ የባንክ አካውንት ስም:-መ/ድ ሀንፈሬ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት
የንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር:-1000554816022

ለብዙዎች ይደርስ ዘንድ ሼር በማድረግ ይተባበሩን።

ማሳሰቢያ:-ወደፊት ትምህርት ቤቱን በተመለከቱ ለሚኖሩን ማናቸውም ስራዎች በራሱ የትምህርት ቤቱ የፌስቡክ ገፅ ለመለጠፍ በእንቅስቃሴ ላይ እንገኛለን።

17/04/2022
17/04/2022
19/10/2020

ለ ነባር 12ኛ ክፍል ማለትም (የ2012 ዓ.ም የዩንቨርስቲ መግቢያ ፈተና የምትወስዱ) ተማሪዎች ከነገ ማክሰኞ 10/02/2013 ዓ.ም የ45 ቀን የማካካሻ ትምህርት ስለሚጀመር ሁላችሁም የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶች(ደብተር ፥ እስክርቢቶ፥ ዩኒፎርም) በመያዝ ት/ቤት እንድትገኙ የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል ት/ቤቱ መግቢያ በር ላይ እየተሰጣችሁ የምትገቡ መሆኑን እናሳውቃለን። መረጃ ላልሰሙ ተማሪዎች መናገር ባህላችን እናድርግ።

👉👉👉👉👉 ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ !በመሀመድ ሃንፍሬ ከ/2ኛ/ደ/መ/ት/ቤት በ2012 የትምህርት ዘመን  ለ12ኛ ከፍል ተማሪዎች ሞዴል ፈተና በማዘጋጀት በት/ቤቱ የቴሌግራም ቻናል http...
20/06/2020

👉👉👉👉👉 ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ !
በመሀመድ ሃንፍሬ ከ/2ኛ/ደ/መ/ት/ቤት በ2012 የትምህርት ዘመን ለ12ኛ ከፍል ተማሪዎች ሞዴል ፈተና በማዘጋጀት በት/ቤቱ የቴሌግራም ቻናል https://t.me/MHSS_learning ተደራሽ ለማድረግ ዝግጅቱን ያጠናቀቀ በመሆኑ እና የሞዴል ፈተናዎቹ ከሰኞ ማለትም ከሰኔ 15/10/2012 ዓ/ም ጀምሮ በት/ቤቱ ባወጣዉ የሞዴል ፈተና የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የሚሰጥ ሰለሆነ ተማሪዎች የቴሌግራም ቻናላችንን በመከታተል የሞዴል ፈተናዉን በአግባቡ እንድትወስዱ እና እራሳችሁን እንድታዘጋጁ ወላጆችም ተገቢዉን እገዛ እንድታደርጉላቸዉ እና በአግባቡ ፈተናዉን መውሰዳቸዉን እንድታረጋግጡ እንጠይቃለን፡፡
ፈተናዉ በወጣዉ መርሃ ግብር እና ሰአት መሰረት በት/ቤቱ ቴሌግራም ላይ የሚቀርብ ሲሆን የሞዴል ፈተና መልስንም ፈተናዉ ከተጠናቀቀ በሃላ በምናወጣዉ ማስታወቂያ መስረት ተደራሽ የሚሆን መሆኑን እንገልጻለን፡፡
👁👁ማሳሰቢያ
ስማርት ፎን ስልክ ያላችሁ በቴሌግራም ስማርት ፎን ስልክ ለሌላችሁ በሀርድ ኮፒ ማስተር ፎቶ ቤት እየሄዳችሁ ኮፒ ማድረግ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
👉 የጥያቄዎቹን መልስ የምትመልሱበት ቀን
የሰኞውን ፈተና—————— ማክሰኞ
የማክሰኞ ፈተና—————— ዕሮብ
የዕሮብ ፈተና——————- ሀሙስ
የሀሙስ ፈተና—————— ዓርብ
👉መልሱን ስማርት ፎን ስልክ ላላችሁ በቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስማርት ፎን ስልክ ለሌላችሁ በሀርድ ኮፒ ት/ቤት እንድታመጡ በማሳሰብ በተጨማሪም ስም እና ሴክሽን መፃፋችሁን እንዳትዘነጉ።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!

You can view and join right away.

በመሀመድ ሃንፍሬ ከ/2ኛ/ደ/መ/ት/ቤት የተዘጋጀ የ 12ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና  ከሰኔ 15/10/2012 ዓ.ም የሚቀረበ ሲሆን ተማሪዎች ተገቢውን ዝግጅት በማድረግ እራሳችሁን እንድትፈትሹበትና ...
17/06/2020

በመሀመድ ሃንፍሬ ከ/2ኛ/ደ/መ/ት/ቤት የተዘጋጀ የ 12ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና ከሰኔ 15/10/2012 ዓ.ም የሚቀረበ ሲሆን ተማሪዎች ተገቢውን ዝግጅት በማድረግ እራሳችሁን እንድትፈትሹበትና ወላጆችም ተገቢዉን እገዛ እንድታደርጉላቸዉ እና በአግባቡ ፈተናዉን መውሰዳቸዉን እንድታረጋግጡ እንጠይቃለን፡፡

ለመሀመድ ሀንፍሬ(ኢላልታ) ከፍተኛ 2ተኛ ደረጃ መሰናዶ ት/ቤት ተማሪዎች  እንደሚታወቀው በአገራችን በCOVID-19 ወረርሽኝ ምክንያት ት/ት መቋረጡ ይታወቃል። በመሆኑም የመማር ማስተማሩን ሂ...
23/04/2020

ለመሀመድ ሀንፍሬ(ኢላልታ) ከፍተኛ 2ተኛ ደረጃ መሰናዶ ት/ቤት ተማሪዎች እንደሚታወቀው በአገራችን በCOVID-19 ወረርሽኝ ምክንያት ት/ት መቋረጡ ይታወቃል። በመሆኑም የመማር ማስተማሩን ሂደት ለማስቀጠል ሁሉም ተማሪ በቤቱ ሁኖ በቴሌግራም ሁሉንም የትምህርት አይነቶች እንድትከታተሉ ት/ቤቱ ያሳውቃል።

ቻናሉን ጆይን በማረግ https://t.me/mohammedhanfere

እንዲሁም ያልገባችሁን ጥያቄ ለመጠየቅ በጉርፑ https://t.me/MHSS_school

ለበለጠ መረጃ 0945121292

Address

Afar Region Aysaita, Welo
Asayta
28

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mohammed Hanfere High school posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The School

Send a message to Mohammed Hanfere High school:

Shortcuts

Share