24/09/2021
ሰበር ዜና‼️
: የአፋር ክልል ልዩ ሀይልና ሚኒሻዎች በአብአላ በኩል ወደ ትግራይ ክልል ዘልቆ በመግባት 4 የትግራይ ከተማዎችን መቆጣጠራቸው ተነገረ ይህ በኢንዲህ እንዳለ በአሁን ሰአትም ከመቀሌ በ30ኪሎ ሜትር ላይ የምትገኘውና ለመቀሌና ለጁንታው ሀይል ቁልፍና እስትራቴጂክ ከተማ የሆነችውን ምላዛት የምትባል ከተማን በአፋር ሀይሎች ቁጥጥር ስር መሆኖ ተረጋግጦል፡፡
24/09/2021
በኢትዮጵያ አዲሱ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ዝርያ (ዴልታ) በከፍተኛ ሁኔታ እየተስፋፍ በዜጎች ላይ ጉዳት እያደረሰ ይገኛል።
የቫይረሱ ስርጭት መስፋፋት በቫይረሱ የሚያዙ ፣ በፅኑ የሚታመሙና ህይወታቸው የሚያጡ ሰዎች ቁጥር እያሻቀበ መሆኑ ጥንቃቄ ይሻል።
ለአዲሱ ቫይረስ መስፋፋት ቫይረሱን ለመከላከል ሚተገበሩ "የጥንቃቄ እርምጃዎች በተገቢው አለመተግበራቸው በአላትን ጨምሮ ጥንቃቄ የጎደላቸው ትምህርት ቤቶች በመከፈት ላይ መሆናቸው፤ ልዩ ልዩ በአላት የሚከበሩ መሆኑ ፤የተማሪዎች ምረቃ በመካሄድ ላይ መሆናቸው እና ሌሎች ማህበራዊ ክንውኖች የቫይረሱን ሰርጭት መስፍፍት ምክንያቶች በመሆናቸው
ይህ መሆኑ ደግሞ በቫይረሱ የሚያዙ እና የሚሞቱ ዜጎችን እንዲጨምር እያደረገ በመሆኑ ህብረተሰቡ የጥንቃቄ እርምጃዎችን ከመውሰድ ጀምሮ የኮሮና ቫይረስ ከትባቶችን እንዲወሰድ ይጠበቃል ።
የመነሻ አሳብ የጤና ሚኒስትር መግለጫ
የደ/ብ/ብ /ክ/ መንግስት ጤና ቢሮ
17/08/2021
ዜና እረፍት
ዶ/ር ተሾመ በላቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
ዶ/ር ተሾመ በላቸው በክልሉ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች በባለሙያነት እንደሁም በሃላፊነት ህዝባቸውን በታማኝነትና በቅንነት ሲያገለግሉ መቆየታቸውን የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል ።
ዶ/ር ተሾመ በሞያቸው ህዝባቸውን በህክምናው ረገድ ከማገልገላቸው ባሻገር በወረዳ ጤና ጽ/ቤት ሃላፊነት እንዲሁም የቡታጅራ ሆስፒታል በስራ አስኪያጅነት የተጣለባቸውን ሃላፊነት በብቃት መፈፀማቸው የሀገርና የህዝብ ባለውለታ መሆናቸውን የማይዘነጋ ያደርገዋል ።
ዶ/ር ተሾመ በትምህርትና በተሰማሩበት አኩሪ የሙያ ዘርፍ እራሳቸውና ለማሳደግና ህዝባቸውን የበለጠ ለማገልገል በነበራቸው የላቀ የትምህርት ፍላጎት በይርጋዓለም ኮሌጅ ኦፍ ሜድስን ትምህርታቸውን በመከታተል በከፍተኛ ማዕረግ በመመረቅ በኮሌጅ በምክትል ዲንነት ሲያገለግሉም ቆይተዋል።
እኚህ ሀገርና ወገንን ወዳድ ባለብሩዕ አህምሮው ዶ/ር ለቤተሰቦቻቸው በነበራቸው ፍቅር በቅርበት አብሮ ለመኖር በመሻታቸው ወደ ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ቡኢ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተዘዋውረው ህዝባቸውን በማገልገል ላይ እያሉ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል ።
የደ ብ/ብ/ሕ/ክ/ መንስት ጤና ቢሮ በኚህ የህዝብና የሀገር ባለውለታ በሆኑት በዶ/ር ተሾመ በላቸው ህልፈተ ህይወት የተሰማውን አዘን በመግለፅ ለጓደኞቻቸው፣ለስራ ባልደረቦቻቸው፣ ለቤተሰቦቻቸው እንዲሁም ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ልባዊ መጽናናትን ይመኛላቸዋል ።
የደ/ብ/ብ/ህ/ክ/መንግስት ጤና ቢሮ