28/11/2025
የ2018 ዓ.ም የ 1ኛ ሴሚስቴር አጋማሽ /MID/ፈተና በሰላም ተማሪዎች ስወሰዱ።
Eduction is facts, skills &ideas that have been learned either formally or informally
28/11/2025
የ2018 ዓ.ም የ 1ኛ ሴሚስቴር አጋማሽ /MID/ፈተና በሰላም ተማሪዎች ስወሰዱ።
ክብርና ምስጋና ለዕውቀት ወላጆቻችን!
መልካም የመምህራን ቀን!!
መስከረም 25 ቀን 2018 ዓ.ም
✍️ የምንወዳቸውን መምህራን ስማቸውን በመጥቀስ እናመስግናቸው። 🙏🙏🙏🙏
04/10/2025
ዛሬም በቀን 24/01/2018 ዓ.ም ከኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የመጡ እንግዶች (Tim and His Team) መሠረተ ድንጋይ የተቀመጠበትን ቦታ ጉብኝት አድርጓል።
ከኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የመጡ እንግዶች (Tim and His Team) የአረካ ከተማ ቁ.1 ቃለ ሕይወት ቤ/ያን ቅድሜ መደበኛ: አንደኛ እና መመካከለኛ ት/ቤት ጉብኝት እና የ2ኛ ደረጃ ት/ቤት መሠረተ ድንጋይ ያረፈበትን ቦታ ጎብኝተዋል።
03/10/2025
የአረካ ከተማ ቁ.1 ቃ/ሕ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት መሠረተ-ድንጋይ ተቀመጠ።
አረካ ከተማ ቁ.1 አጥቢያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ት/ቤት ስሆን ከዚህ በፊት አፀደ ሕፃናት፣አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት እስከ 8ኛ ክፍል ድረስ በማስተማር በቀለም እውቀትና በሥነ-ምግባር የታነጸ ትውልድ በማፍራት ምሳሌ በመሆን የቆየ ት/ቤት ሲሆን በቀን 22/01/2018 ዓ.ም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመገንባት መሠረተ-ድንጋይ የማኖር ሥነ-ሥርዓት የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤ/ክ ፕረዚዳንት ዶክተር ስምዖን ሄሊሶ እና የወላይታ ቀጠና ዋና ፀሐፊ መጋቢ አብርሃም ቦታ እና ሌሎች እንዲሁም የወላይታ ዞንና የአረካ ከተማ አስተዳደር ተወካዮች በተገኙበት መሠረተ-ድንጋይ ተቀመጠ።
የቤተ ክርስቲያኒቱ ባለ ራዕይ መሪዎችን ከልብ እናመሰግናለን ። ስለሁሉም እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን !!
12/08/2025
አስደሳች ዜና
ለትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ
እነሆ አጋፋው የአረካ ከተማ ቁ.1 ቃለ ሕይወት ቤተክርሰቲያን አፀደ ሕፃናት፤ አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት ለ2018 ዓ.ም የተማሪዎች ቅበላ/ምዝገባ ስለጀመሪን ያለንም ቦታ ውስን ስለሆነ ነባር እና አዲስ ተማሪዎች በተባለው ጊዜ መጥታችሁ እንድትመዘገቡ እንገልጻለን፡፡
ነባር ተማሪዎች ምዝገባ ከነሐሴ 07-16/17 ዓ.ም
አዲስ ተማሪዎች ምዝገባ ከነሐሴ 19-21/17 ዓ.ም
ስለሆነ ዘውትር በስራ ሰዓት ምዝግባ የምናካሂድ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
08/08/2025
እንኳን ደስ አለን !!
እንኳን ደስ አላችሁ !!!
#🅒🅞🅝🅖🅡🅐🅣🅤🅛🅐🅣🅘🅞🅝
...........
ት/ቤታችን ዘንድሮ ባስፈተነው የ8 ኛ ክፍል ተማሪዎች #በክልል ደረጃ በከፍተኛ ውጤት 1ኛ እንዲሁም ተማሪ ብሩክ አብራሃም በክልል ደረጃ ከፍተኛ ውጤት 100 በማስመዝገቡ 1ኛ በመውጣቱ እንኳን ደስ አላችሁ ደስ አለን።
ዘንድሮም የተፈተኑት የ 6 ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች ጥሩ ውጤት በማምጣት አልፈዋል።
.......
ለዚህ ጥሩ ውጤት የደከማችሁ መምህራን፣ ርሳነ መምህራንና ባለ ድርሻ አካላት እንዲሁም የተማሪ ወላጆች ይሄ በሁሉ ጥረት የተገኘ ድል ነውና እንኳን ደስ አላችሁ!!
08/07/2025
ሰኔ 30/2017ዓ.ም ግሩም ቀን ነበር።
አረካ ከተማ ቁ.1 ቃለ ህይወት አፀደ ህፃናት: መጀመሪያ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የKG ተመራቂዎችን አሰመርቀዋል እንዲሁም ከ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎችን በከፍተኛ ውጤት 1ኛ ደረጃ ለወጡ ተማሪዎች የቀጣዩን ዓመት የ ክፍል የመጀመሪያውን ወር ክፊያ በነፃ እንደማሩና በ2ኛና በ3 ኛ ደረጃ የወጡ ደግሞ የተለያዩ የትም/ት ቍሳቁስ እንድሽለሙ በማድረግ ወላጆችና ከተለያዩ ሥፍራ የተጠሩ ክብር እንግዶች በተገኙበት የካርድ አሰጣጥ ሥርዓቱን ሲያጠናቅቅ ላቅ ያለ ደስታ ይስማዋል!
አረካ ቊ. 1 ቃለ ሕይወት አካዳሚ!
Happy follow-versary to my awesome followers. Thanks for all your support! Eshetu Tadese
07/06/2025
አዲሱ የቁ.1 ቃለ ሕይወት ቤ/ያን ት/ቤት ለሀይስኩል ት/ቤት መሥሪያ ቦታ ዝግጅት ሥራ ተጀመረ።
29/05/2025
የ2017 ዓ.ም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ሞዴል ፈተና ስወሰዱ።
ተማሪዎቻችን መልካም ውጤት
11/01/2025
Assessment and feedback practices for students' learning: A training for Areka town No.1 Kale Hiwot Church primary school teachers.
በምል ርዕስ 2ኛ ዙር (ከአምናዉ የቀጠለ) በቀን 02/05/2017 ሙሉ ቀን በዶ/ር በረከት ተለሞስ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና በሰላምና በስኬት ተጠናቋል።
ስልጠናውም በመማር ማስተማር ሂደት ውስጥ ግብረመልስ ልምምድ፣ ቀጣይነት ያለዉ ሚዘናና ግምገማ ምን መምሰል እንዳለበት የሚያሳይ እና በተማሪዎች ዉጤት መሻሻል ላይ ትኩረት የሚያደርግ ሲሆን ሁሉም የት/ቤት መምህራን በተገኙበት ስልጠናው በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።
የአረካ ከተማ ት/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደነቀ ኦንችሬ ስልጠናውን በተመለከተ መክፈቻ ንግግር በማድረግ ዶ/ር በረከት ተለሞስን በማመስገን ሰልጣኞችም ከዚህ ያገኙትን እዉቀት ተግባራዊ እንዲያደርጉም ጭምር አሳስበዋል።
ስልጠናውን በፈቃደኝነት የሰጠውን ዶ/ር በረከት ተለሞስን ከልብ እናመሰግናለን። 🙏
እንኳን ደስ አለን !!
እንኳን ደስ አላችሁ !!!
...........
በት/ቤታችን ዘንድሮ የተፈተኑት የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ አልፈዋል።
እንዲሁም ባለፌው እንደገለጽነው ዘንድሮ የተፈተኑት የ 8 ኛ ክፍል ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ ጥሩ ውጤት በማምጣት ማለፋቸው ይታወሳል።
.......
ለዚህ ጥሩ ውጤት የደከማችሁ መምህራን፣ ርሳነ መምህራንና ባለ ድርሻ አካላት እንዲሁም የተማሪ ወላጆች ይሄ በሁሉ ጥረት የተገኘ ድል ነውና እንደገናም እንኳን ደስ አላችሁ!!