Arbaminch Mekane Yesus college

Arbaminch Mekane Yesus college

Share

Arba Minch Mekane Yesus Technical College was established in 1964 E.C named Arba Minch Vocational Sc

Photos from Arbaminch Mekane Yesus college's post 21/10/2025

የምሥራች ለሥራ ፈላጊዎች በሙሉ!

አርባምንጭ መካነ ኢየሱስ ቴክኒካል ኮሌጅ እየቀጠረች ነው!!

ኮሌጁ
1. በ Accounting and Finance

2. በ Management

3. በ Cooperative Accounting and Auditing

4. በ Cooperative Marketing

5. በ Information Teleology (IT)

6. በ Auto-mechanics

7. በ Animal Health

8. በ Animal Production

9. በ Secretarial and Office Administration ት/ት ክፍሎች እና ሌሎችም የሥራ መደቡን መስፈርት የሚያሟሉትን አወዳድሮ ለመቅጠር ቀጥሎ የተለጠፈውን ማስታወቂያ አውጥቷል።

ስለዚህ መስፈርቱን የሚታሟሉ ሁሉ በማስታወቂያው እንደተገለጸ በአካል፣ በቴሌግራም እና ኢ-ሜይል አማራጮች መመዝገብ የሚትችሉ በመሆኑ እድላችሁን ሞክሩ።

መልካም ዕድል!!!

አርባ ምንጭ መካነ ኢየሱስ ቴክኒካል ኮሌጅ!

Photos from Arbaminch Mekane Yesus college's post 19/10/2025

💢💢 አስደሣች ዜና በጋሞ ዞንና አከባቢው ላላችሁ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ 💢💢

💪💪 አንጋፋው የቀድሞ አርባ ምንጭ ተግባረ-ዕድ የዛሬው አርባምንጭ መካነ ኢየሱስ ቴክኒካል ኮሌጅ በ2018 የትምህርት ዘመን ተማሪዎችን የኢፌዴሪ ሥራና ክህሎት ሚንስቴር ለቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ባወጣው የመቁረጫ ነጥብ መሠረት ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል :- በዝሁ መሠረት

1. ለወንዶች ደረጃ - 4 ለመማር የኢንቴራንስ ውጤት 135 እና ከዚያ በላይ
2. የሴቶች ደረጃ - 4 ለመማር የኢንቴራንስ ውጤት 122 እና ከዚያ በላይ ያመጡትን እና የመጀመሪያ ድግሪ ተመዝግበው ለመማር መስፈርቶቹን የሚያሟሉ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር ዝግጅት አጠናቆ ምዝገባ በይፋ መጀመሩን በደስታ ይገልጻል!!

👉👉 ኮሌጃችን የበርካታ ምሁራን መፍለቅያ ከመሆን አልፎ በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ዜጎችን ስያፈራ ቆይቷል።

🙏🙏 ተግባራዊ ዕውቀት ከፈለጉና በምሠሩበት ሁሉ ውጤታማ ለመሆን የአርባምንጭ መካነ ኢየሱስ ቴክንካል ኮሌጂን ይምረጡ !!🙏🙏

🏃🏃🏃 ኮሌጁ መርጠውት የሚመጡ ተማሪዎችን እንኳን ደህና መጣችሁ እያለ 2018 ዓ/ም መልካም የት/ት ዘመን እንድሆንላችሁ ይመኛል!!!

18/10/2025

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Etalem Girma, Bilen Muluneh, Tariku Tadesse, Mesfin Mes
Welcome

18/10/2025

አንጋፋው የቀድሞ አርባ ምንጭ ተግባረ-ዕድ የዛሬው አርባምንጭ መካነ ኢየሱስ ቴክኒካል ኮሌጅ በ2018 የትምህርት ዘመን ተማሪዎችን የኢፌዴሪ ሥራና ክህሎት ሚንስቴር ለቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ባወጣው የመቁረጫ ነጥብ:-
1. የወንዶች ደረጃ - 4 ለመማር የኢንቴራንስ ውጤት 135
2. የሴቶች ደረጃ - 4 ለመማር የኢንቴራንስ ውጤት 122 ያመጡትን እና የመጀመሪያ ድግሪ ተመዝግበው ለመማር መስፈርቶቹን የሚያሟሉ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር ዝግጅት አጠናቆ ምዝገባ በይፋ መጀመሩን በደስታ ይገልጻል!

ተማሪዎቻችን እንኳን ደህና መጣችሁ!!

መልካም የት/ት ዘመን ይሁንላችሁ!!!

Photos from Arbaminch Mekane Yesus college's post 01/10/2025

ውድ የአርባምንጭ መካነየሱስ ቴክኒካል ኮሌጅ ተማሪዎች እንኳን ለ2018 ዓ.ም ለት/ት ዘመን በሠላም አደረሳችሁ!!

መልካም የት/ት ዘመን እንድሆንላችሁ እየተመኘን:-- የ2018 ዓ.ም መደበኛ ት/ት ሥራውን ኮሌጁ የጀመረና በሁሉም ትምህርት ክፍሎች የመማሪያ ጊዜ ሰሌዳ ያወጣ መሆኑን አውቃችሁ ከቀን 22/1/2018 ዓ.ም በትምህርት ክፍላችሁ እንድትገኙ ይሁን!

ለአድሱ አመት ኮሌጁ ሁሉንም አስፈላጊ ዝግጅቶችን በማጠናቀቅ ለነባርና አድስ ተማሪዎች:.... ከመማር ማስተማር ሥራው ጋር አካቢው ምቹና አስደሳች እንድሆንላችሁ
የእግር ኳስ ሜዳ
የቫሊቦል (መረብ ኳስ) ሜዳ
የቴኒስ ቴብል ስፖርት
የነፃ 24 ሰዓት የሚያገለግሉ Wi-fi አግልግሎት በተንጣለለው ግቢ በማዘጋጀት እናንተን ይጠብቃል ኑ እየተዝናናችሁ ተማሩ እኛ ጋር!

ሁለም ለትምህርት ጥራት እንተጋለን!!

አርባምንጭ መካነየሱስ ቴክኒካል ኮሌጅ (ተግባ-ራዕድ ኮሌጅ)!!

Photos from Arbaminch Mekane Yesus college's post 05/09/2025

የአርባምንጭ መካነ-እየሱስ ቴክኒካል ኮሌጅ በተለያዩ የሙያ መስኮች አጫጭር ስልጠና የወሰዱ 43 ሰልጣኞች አስመረቀ።

‎አርባምንጭ፣ ነሐሴ 30/ 2017 ዓ/ም (አርባምንጭ መካነ ኢየሱስ ቴክኒካል ኮሌጅ)

‎ኮሌጁ ከደቡብ ከኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤ/ክ መካነ ኢየሱስ ደቡብ ምዕራብ ሲኖዶስ በዳስክ- አድራ ጀርመን Green Energy TVET Project ድጋፍ በሶላር ዲዛይን፣ ተከላ እና ጥገና በአጫጭር ሥልጠና ፕሮግራም ለ3ኛ ዙር ተቀብሎ ለተከታታይ 4 ወራት ስልጠና የወሰዱ 43 ሰልጣኞች ማስመረቁ አስመርቋል።

‎መርሃግብሩም በቄስ አመስግነው መርዕድ ምክር፣ ትምህርትና ፀሎት ተጀምሯል።

‎የደቡብ ምዕራብ ሲኖዶስ የልማትና ማህበራዊ አገልግሎት ዳስክ ዳይሬክቶሬት ዶ/ር ኦርካይዶ ኦልቴ በመክፈቻ ንግግራቸው እንደተናገሩት ተቋሙ ከመንፈሳዊ አገልግሎት ጎን ለጎን በልማትና ማህበራዊ ዘርፎች ላይ ትኩረት በመስጠት ለአከባቢው ህብረተሰብ ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን እየሰጠ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

‎አለማችን በኢኮኖሚው እያንቀሳቀሱ የሚገኙት ስራ ፈጣሪዎች መሆናቸውን የጠቆሙት ዶ/ር ኦርካይዶ ከተለያዩ ተቋማትና ድርጅቶች ጋር በመተባበር የሀገራችን ልማት የሚደግፉ ሙያዎችን የኃይል ምንጮች ላይ ያለውን ክፍተቶች ለመሙላትና በአረንጓዴ ኢኮኖሚ ዘርፍ ዘላቂ ለውጥ ለማምጣት ረዥምና አጫጭር ስልጠናዎችን እንደሚሰጡም ገልፀዋል።

‎በዛሬው ዕለትም የተመረቁ ሰልጣኞች በሰለጠኑትን ሙያ ህብረተሰቡን በማገልገል ከራሳቸው አልፎ ለሀገር የሚጠቅሙ ዜጎች እንዲሆኑም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

‎የጋሞ ዞን ሙና ቴክኒክ ትምህርትና ሥልጠና መምሪያ ኃላፊ አቶ ወንድሙ ኡቶ የቴክኒክና ሙያ ተቋም የተለያዩ ስልጠናዎችን ተደራሽነትና ፍትሃዊነት በማሳደግ ቴክኖሎጂን በማስፋፋት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት በማሳደግ የሀገርን ሁለንተናዊ ዕድገት እውን ለማድረግ የሰለጠነ ዜጋና የበቃ የሰው ኃይል ቁልፍ መሳሪያ መሆኑን ተናግረዋል።

‎የሙያ ስልጠና የአገራችን ኢኮኖሚ በዝቅተኛ፣ በመካከለኛ ደረጃ የሚያስፈልገውን የሰለጠነ ሙያተኞችን በማፍራትና ቴክኖሎጂ በማቅረብ በኩል ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ጠቁመዋል።

‎ተመራቂዎችም ብቁና በራሳቸው የሚተማመኑ በመሆን ከተቀጣሪነት ስሜት በመላቀቅ ከተቋሙ የወሰዱትን እውቀትና ክህሎት ወደ ተግባር በመቀየር የህዝባችንን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቅንነት እንዲያገለግሉ አሳስበዋል።

‎የአርባምንጭ መካነ-እየሱስ ቴክኒካል ኮሌጅ ዲን አቶ አደን አብዱራሃማን ኮሌጁ በመማር ማስተማር፣ በምርምርና በማህበረሰብ አገልግሎት ፍላጎት መር በሆኑ ረዥምና አጫጭር ስልጠናዎች በመስጠት ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎችን ለመፍጠር በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

‎ተቋሙ የመንግሥትን የትኩረት አቅጣጫ ተከትሎ እንደሚሰራ የተናገሩት አቶ አደን ዜጎች ከሥራ ጠባቂነት ተላቆ ስራ ፈጣሪ እንዲሆን ከተለያዩ ባለድርሻ ተቋማት ጋር በመቀናጀት የአከባቢ ፀጋዎችን በመለየት ተግባር ተኮር ስልጠናዎች በመስጠት ወደ ስራ እንዲሰማሩ ከሚመለከታቸው አካላት በመተባበር እንደሚሰሩም አስረድተዋል።

‎በዛሬው ዕለም ኮሌጁ ከደቡብ ከኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤ/ክ መካነ ኢየሱስ ደቡብ ምዕራብ ሲኖዶስ በዳስክ- አድራ ጀርመን Green Energy TVET Project ድጋፍ በሶላር ዲዛይን፣ ተከላ እና ጥገና በአጫጭር ሥልጠና ፕሮግራም ለ3ኛ ዙር ተቀብሎ ለተከታታይ 4 ወራት ስልጠና የወሰዱ 43 ሰልጣኞች ማስመረቁን አስረድተዋል።

‎የኮሌጁ ፕሪንሲፓል የሆኑት አቶ ተካልኝ ተፈሪ በበኩላቸው ተቋሙ የሀገራችንን የኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ ችግሮችን ለመፍታት በሚያግዙ ሙያዎች ላይ መሠረታዊና

12/08/2025

ምዝገባ ላይ ነን!

Photos from Arbaminch Mekane Yesus college's post 02/08/2025

#🎓ለ48ኛው ዙር አስመርቀናል🎓🎓
🎓አርባምንጭ መካነ ኢየሱስ ኮሌጅ❤🎓🎓
‎የአርባምንጭ መካነኢየሱስ ቴክኒካል ኮሌጅ በቴክኒክና ሙያ ትምህርት ዘርፍ ለ48ተኛ ዙር በዲፕሎማ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመረቀ።

‎አርባምንጭ ሐምሌ 26/2017 ዓ.ም

‎ኮሌጁ በቀንና በማታ መርሃግብር በአራት መስኮች ያሰለጠናቸውን 258 ተማሪዎችን የጋሞ ዞንና የከተማ አመራሮች በተገኙበት አስመርቋል።

‎የአርባምንጭ ከተማ ም/ል ከንቲባና ገቢ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ከንቲባ ትምህርት ሀገርን ለሚመራት ቀጣዩን ትውልድ ለማነፅና ለሀገር እድገት መሠረት እንደመሆኑ መጠን ሁለንተናዊ ችግሮችን በእውቀትና በተግባር ለመቅረፍ ጉልህ ሚና እንዳለው ጠቁመው በእውቀት የተገነባ ትውልድ ለአንድ ሀገር መሠረቱ የፀና፣ጠንካራና የማይደፈር ልዕልናን የሚያላብስ ሲሆን ትምህርት ደግሞ ትልቁ መሣሪያ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

‎መንግስት የትምህርት ተደራሽንን ለማስፋትና ለማሻሻል በራሱና አልሚ በሆኑ የግል ባለሀብቶች፤ በቤተእምነቶች የተጀመሩ የትምህርት መሠረተ ልማት ማሻሻያና የተቋማት ግንባታ ሥራዎችን አጠናክሮ እየሰራና እየደገፈ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

‎ትውልዱ ተገቢውን ትምህርት እንዲያገኝ ለማድረግ መንግስት ርብርብ እያደረገ በሚንገኝበት በዚህ ወቅት ተባፕብረንና አስተባብረን ህብረተሰቡን የሚቀይር ነገር ከሰራን ከድህነት መውጣት እንችላለን ያሉት ኃላፊዋ ‎እናት ቤተክርስቲያን ከምትሰጠው መንፈሳዊ አገልግሎት በተጨማሪ ትውልድን በእውቀትና በክህሎት በማነፅ ላበረከተችው ከፍተኛ አስተዋጽኦ ለምታካሂደው በጎ ተግባር በከተማ አስተዳደር ስም ምስጋናቸውንም አቅርበዋል።

‎የሀገራችን ብልጽግና እውን ለማድረግ በእውቀት፣ በክህሎት፣ በአመላካከትና በስነ-ምግባር የታነፀ ትውልድ መፍጠር ያስፈልጋል ያሉት የጋሞ ዞን አስተዳደር ተወካይና ልዩ አማካሪና አቶ ደረጀ ጳውሎስ ለዚህ በተለያዩ ሙያ የተመረቁ ተማሪዎች በተግባር የመወጣት ኃላፊነት እንዳለባቸው ተናግረዋል።

‎የጋሞ ዞን ሙና ቴክኒክ ትምህርትና ሥልጠና መምሪያ ኃላፊ አቶ ወንድሙ ኡቴ የሙያ ስልጠና የአገራችን ኢኮኖሚ በዝቅተኛ፣ በመካከለኛ ደረጃ የሚያስፈልገውን የሰለጠነ ሙያተኞችን በማፍራትና ቴክኖሎጂ በማቅረብ በኩል ከፍተኛ ሚና የሚጫወትና በዘርፉ አገሪቱን ከግብርና መር ወደ ኢንዱስትሪ ሽግግር አቅምና መሰረት የሚጥል መሆኑን አስረድተዋል።

‎ተመራቂዎችም ከተቀጣሪነት ስሜት በመላቀቅ ከተቋሙ የወሰዱትን እውቀትና ክህሎት ወደ ተግባር በመቀየር የህዝባችንን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቅንነት እንዲያገለግሉ አሳስበዋል።

‎የአርባምንጭ መካነኢየሱስ ቴክኒካል ኮሌጅ ዲን አቶ አደን አብዱረህማን ኮሌጁ በ1971 ከተመሠረተ ጊዜ ጀምሮ ታሪክ ሊረሳዉ የማይችለዉን ደማቅ የእውቀትና ጥበብ ቀለማትን በትውልድ አስተውሎት እያስቀመጠ ብዙ ውጣ ውረዶችን እያሳለፈና እራሱን በማሳደግ በርካታ ሥራዎችን እየሰራ ያለ ተቋም መሆኑን ገልፀዋል

‎ኮሌጁ ጥራት ያለዉን ት/ት ለሠልጣኞቹ ተደራሽ በማድረግ የማያወላዳ ትውልድ ተኮር አቋም ያለዉ ሲሆን ለዚህም ተግባር ግብአቶችን አቅም በፈቀደ መጠን በሟሟላት መማር ማስተማሩን ሥራ በቂ ሞያ፤ ዕውቀትና ክህሎት ባላቸው መምህራን እንደሚገኝም አስረድተዋል።

‎ኮሌጁ በድግሪ በማነጅሜንት፣ በአካውንቲንግ እና ማርኬቲንግ ማኔጅመንት ፕሮግራሞችም ተማሪዎችን ተቀብሎ እያስተማረ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

‎በመቀናጀት ፍላጎት መሪ በሆኑ የክህሎት ማበልፀጊያ ሥልጠና 403 ወጣቶችን ሥራ አጥ በማሠልጠን አስመርቋል፡፡ እንደሁም የመንግሥትን የትኩረት አቅጣጫ በ

Photos from Arbaminch Mekane Yesus college's post 31/07/2025

አርባምንጭ መካነ ኢየሱስ ተክኒካል ኮሌጅ እየተከለች ነው!

የአርባምንጭ መካነ ኢየሱስ ቴክኒካል ኮሌጁ በመላው አገር ''በመትከል ማንሰራራት'' በምል መርህ ቃል የተጀመረውን የአረንጓዴ ልማት ሥራ መላ የኮሌጁን አካዳሚክ እና አስተዳደር ሠራተኞችን በማንቀሳቀስ አከናውናለች። በመረሐ-ግብሩም የኮሌጁ ሠራተኞች በባለፈው በልግ ዝናብ ወቅት የተተከሉ ችግኞችን የኮተኮቱ ሲሆን ሌሎች የደን ዛፍ ዝሪያ ችግኞችንም በመትከል ውሃ አጠጥቷል።

ኮሌጁ በአውቶሞቲቭ ቴክኖሎጅ፣ በIT ዘርፍ፣ በሶላር ቴክኖሎጂ፣ በአጠቃላይ ብረታ ብረት እና በግብርና ዘርፍ በሁሉም የት/ት መስኮች የረጅም ዓመታት ልምድና የተሻለ የት/ት ዝግጅት ባላቸው መምህራን በጥራት እያሰለጠነ ይገኛል።

ቀጣይም ኮሌጁ ተፈጥሮን ጠብቆና ተንከባክቦ ቀጣይነት ያለውን ዕድገት ለማረጋገጥ እንደ አገር እና ክልላችን አልፎም በዞን ደራጀ እየተሠራ ያለውን የአረንጓዴ ልማት ሥራ በትኩረት ይደግፋል፤ ይፈጽማልም።

በመትከል ማንሰራራት!!!

Want your school to be the top-listed School/college in Arba Minch'?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Category

Telephone

Address


Arba Minch'