29/05/2025
1,070,000 ኢትዮጵያዊያን ሞቱ!
"ልጄ ለሞተ ሰው አልቅስለት እዘንለት ራስህንም አሳዝን እንደ ሥርዓቱም መታሰቢያን አርግለት ያገለገለሀን ሰው ሞት ቸል አትበል:: ከልብህ አልቅስለት አጽንተህም እዘንለት እንደ አገሩም ልማድ አልቅስሰት ስለ አገሩም ሕግም አንድ ቀን ሁለት ቀን አልቅስለት::" ሲራክ 38÷15-16
ወንድማችን ዶክተር ተሾመ እሸቱ በአዳማ ሆስፒታል ሲያገለግል የቆየ እንቁ የአጥንት እስፔሻሊስት ሀኪም ነው፡፡
ወንድማችን ብዙ ህሙማንን ያገለገለ ለኢትዮጵያን ብዙ ተስፍ ያለው እንቁ ሀኪም ነበር ።
ነገርግና ምን ሆነ ተገደለ?! ሞቶ አረፈ፡፡
እኔ ይገርመኛል በሀገራችን የአጥንት እስፔሻሊስት ሀኪሞች ትንሽ ናቸው በጣም አናሳ ናቸው፡፡
የሚገርመው 1 የእጥንት እስፔሻሊስት ሀኪም ለ1,070,000 ሰዎች ነው አግልግሎት እየሰጠ ያለው፡፡
ዶክተር ተሾመ እሸቱ ሞተ ማለት 1,070,000 ኢትዮጵያዊያን ሞቱ ማለት ነው፡፡
ትናንት የሞተው አንድ ዶክተር ሳይሆን 1,070,000 ኢትዮጵያዊያን ናቸው፡፡
⚓️ይህን ማን አስተዋለ?!
⚓️እንዴት ማስተዋል አቃተን?!
እንዳትሳሳቱ ትላንት የሞተው 1,070,000 ኢትዮጵያዊያን ናቸው።
ኢትዮጵያ ባድራዋን ዝቅ አርጋ ልታዝን ይገባት ነበር ነገር ግን ገዳይ ሆና ተገኝታለች፡፡ እኛ ጭራሽ ያገለገለንን ሰው ልናዝንልት ይቅርና እንገለዋለን!
ኢትዮጵያዊያ ሆይ ወዴት ነው እየሄድክ ያለሹ/ያለኽው?!
ምንድ ነው እያደረግሽ ያለሽው/ያለኽው?!
©Dn. Dr. Tadesse Fanta Gela (General surgeon)