26/07/2023
ድላችን አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት
"ትምህርት ለትውልድ"
ፊደል የቆጠርንባት፣ የልጅነት ትዝታችንና ፍቅራችን የተቀረፀባት፣ ጥሩና መጥፎን የለየንባት፣ የዜግነት ክብር ብለን የዘመርንባት፣ ከድንቁርና ዓለም ተለይተን እውቀትና ጥበብ የቀሰምንባት፣ ሙሉ ሰው ሆነን ማሰብ የቻልንባት በጥሩ ሥነ- ምግባር ያደግንባት ትምህርት ቤታችን፣ በተለያዩ የትምህርት ጥራት ችግሮች ውስጥ ያለች በመሆኗ ሙሉ እንድትሆንና የመማር ማስተማር ሂደቱም ምቹ እንዲሆን የትምህርት ቤት መሠረት ልማት ለመማር ማስተማር ስራው ዋናው ቁልፍ ጉዳይ በመሆኑ የትውልድ ጉዳይ የሚያሳስበው የቀድሞ ተማሪዎች፣ ባለሀብቶችና ማንኛውም በጎ አድራጎት ድርጂት ድላችን አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ድረስ በመምጣት የጎደለንን ቁሳዊ ሀብት ታሟሉልን ዘንድ በት/ቤታችን የትምህርት ማህበረሰብና ተማሪዎች ስም እንጠይቃለን፡፡
05/05/2022
በወላይታ ዞን የ11ኛ ክፍል ተማሪ ኢ ቲ አር ኤስ1 ኬ ኤም የተባለ ሮኬት በዩኒቨርሲቲው ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት ትብብር መሰራቱ ተገልጿል።
ወጣት ሳሙኤል ዘካሪያስ በወላይታ ዞን የ11ኛ ክፍል ተማሪ ሲሆን በዩኒቨርሲቲው ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎትተብሎ ምክትል ፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት የገንዘብ ድጋፍና ትብብር( ETR S1KM የሚጠራ ሮኬት መስራቱን በዛሬው እለት አስታውቋል።
ወጣት ሳሙኤል ዘካሪያስ ከዚህ በፊት ከአከባቢው ያገኘውን የተለያዩ ቁሳቁስ በመጠቀም ኤክስካባተር መኪና እንዲሁም የቆሻሻ ማፈሻ መኪና ሰርቶ በሀገር አቀፍ ደረጃ ተሸላሚ እንደነበር ተገልጿል፡፡
በቅርቡም የተሳካ የማስወንጨፍ ሙከራ እንደሚያደርግ ተመላክቷል።
ወጣቱ የሰራው ሮኬት አንድ ኪሎ ሜትር ድረስ የመወንጨፍ አቅም ያለው መሆኑንና፥ ሮኬቱን የሚሸከመው መኪናም አብሮ መሰራቱ ታውቋል።
ለወጣት ሳሙኤል ዘካሪያስ የተደረገው ድጋፍ በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል መገለጹን የዩኒቨርሲቲው መረጃ ያመላክታል።
👇🏻👇🏻👇🏻🔔📖🗣👇👇👇
በፍጥነት ለማግኘት እንዲሁም ጠቃሚና ትምህርታዊ መረጃዎችን ለማግኘት አሁኑኑ የቴሌግራም ፣ የፊስቡክ ገፃችንን እና የዩትዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ ወይም በቀጥታ ሊንኩን በመጫን የትምህርት ቤታችን ቤተሰብ ይሁኑ ለሌሎችም ሼር በማድረግ ያጋሩ!
👇👇👇👇👇👇
telegram:
: https://www.facebook.com/DilachenGeneralSecondaryScሽhool
youtube: https://www.youtube.com/channel/UC4-cbnEnqvn-CMr2FHvqzNQ
🙏🙏🙏✍✍✍🙏🙏🙏
01/05/2022
👉ለእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1443ኛዉ ኢድ አል-ፈጥር በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን!
🙏ኢድ ሙባረክ!🙏
ድላችን አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት
30/04/2022
በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በመደበኛ መርሃ-ግብር በመጀመሪያ ዲግሪ
አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች ሚያዚያ 28 እስከ 30/2014 ዓ.ም ሪፖርት አድርጉ ተብሏል።
የማመልከቻ ካምፓሶች፦
👉 የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በዘንዘልማ ካምፓስ፣
👉 የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በይባብ ካምፓስ፣ 👉 የተፈጥሮ እና ማኅበራዊ ሳይንስ በመምህርነት
ተማሪዎች በሰላም ካምፓስ
ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት የዩኒቨርሲቲውን ድረ-ገጽ https://bdu.edu.et/registrar/ መጠቀም ይቻላል።
ለምዝገባ ወደ ተቋሙ ስትሄዱ መያዝ የሚገባችሁ፦
• የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ውጤት ዋናውና ኮፒ
• ጉርድ ፎቶግራፍ (4)
• አንሶላ፣ ብርድልብስና የትራስ ልብስ
• የስፖርት ትጥቅ
በሌላ በኩል በተለያየ ምክንያት ትምህርት አቋርጣችሁ ለመልሶ ቅበላ ውጤታችሁ የሚያበቃችሁና የመልሶ ቅበላ ፎርም የሞላችሁ ተማሪዎች አዲስ ከተመደቡ አንደኛ ዓመት ተማሪዎች ጋር በመቅረብ በ2014 ዓ.ም የመጀመሪያ ሴሚስተር ለመልሶ ቅበላ ግንቦት 01 እና 02/2014 ዓ.ም እንድታመለክቱ ተብሏል።
ከተጠቀሱት ቀናት ውጪ የሚመጡ ተማሪዎችን እንደማያስተናግድ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።
👇🏻👇🏻👇🏻🔔📖🗣👇👇👇
በፍጥነት ለማግኘት እንዲሁም ጠቃሚና ትምህርታዊ መረጃዎችን ለማግኘት አሁኑኑ የቴሌግራም ፣ የፊስቡክ ገፃችንን እና የዩትዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ ወይም በቀጥታ ሊንኩን በመጫን የትምህርት ቤታችን ቤተሰብ ይሁኑ ለሌሎችም ሼር በማድረግ ያጋሩ!
👇👇👇👇👇👇
telegram:
: https://www.facebook.com/DilachenGeneralSecondaryScሽhool
youtube: https://www.youtube.com/channel/UC4-cbnEnqvn-CMr2FHvqzNQ
🙏🙏🙏✍✍✍🙏🙏🙏
30/04/2022
📝📕🗣👉🏽በፈተና ወቅት ጥሩ ውጤት ለማምጣት የሚረዱ ምክሮች🙏🏽✍🏽🙏🏽
26/04/2022
🗣ለሁሉም የትምህርት ቤቱ ተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች⏰
25/04/2022
የድላችን አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት 2014 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የቅዳሜ ማጠናከሪያ ትምህርት ከፊል ገፅታ...
👇🏻👇🏻👇🏻🔔📖🗣👇👇👇
በፍጥነት ለማግኘት እንዲሁም ጠቃሚና ትምህርታዊ መረጃዎችን ለማግኘት አሁኑኑ የቴሌግራም ፣ የፊስቡክ ገፃችንን እና የዩትዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ ወይም በቀጥታ ሊንኩን በመጫን የትምህርት ቤታችን ቤተሰብ ይሁኑ ለሌሎችም ሼር በማድረግ ያጋሩ!
👇👇👇👇👇👇
telegram:
: https://www.facebook.com/DilachenGeneralSecondaryScሽhool
youtube: https://www.youtube.com/channel/UC4-cbnEnqvn-CMr2FHvqzNQ
🙏🙏🙏✍✍✍🙏🙏🙏
25/04/2022
የዩኒቨርስቲ ምደባ ይፋ ሆነ
-----------------------------
ትምህርት ሚኒስቴር የ2013ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርስቲ ምደባ ይፋ አድርጓል።
የ2013 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ መንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) የመግቢያ መቁረጫ ነጥብ ላመጡ ተማሪዎች ምደባ ተደርጓል።
ከዚህ በፊት በተገለጸዉ የመቁረጫ ነጥብ እና ከኦሮሚያ፣ አማራ፣ አፋርና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ተጨማሪ ተማሪዎች ምደባ የሚያስገኝላቸው ውሳኔ መተላለፉ ይታወሳል፡፡
በዚህም መሰረት ተማሪዎች ከዛሬ ጀምሮ የተመደቡበትን ዩኒቨርስቲ ለማየት በድህረገፅ፡-https://result.ethernet.edu.et ፣ በSMS፡- 9444 እንዲሁም በቴሌግራም፡- መጠቀም ይችላሉ።
ተማሪዎች ከምደባ ጋር ተያይዞ ላላችው ማንኛውም ጥያቄ በድህረገፅ https://complaint.ethernet.edu.et በማመልከት ጥያቄዎቻቸውን ማቅረብ ይችላሉ፡፡
ዩኒቨርሲቲዎች እስከ ሚያዝያ 24/2014 ዓ.ም ድረስ ተገቢዉን ዝግጅት አድርገው የመጀመሪያ ዓመት አዲስ ገቢ ተማሪዎችን የቅበላ መርሃ ግብር የሚያሳዉቁ በመሆኑ ተማሪዎች አስፈላጊዉን ዝግጅት እንዲያደርጉም ሚኒስቴሩ ጥሪ ያቀርባል፡፡
👇🏻👇🏻👇🏻🔔📖🗣👇👇👇
በፍጥነት ለማግኘት እንዲሁም ጠቃሚና ትምህርታዊ መረጃዎችን ለማግኘት አሁኑኑ የቴሌግራም ፣ የፊስቡክ ገፃችንን እና የዩትዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ ወይም በቀጥታ ሊንኩን በመጫን የትምህርት ቤታችን ቤተሰብ ይሁኑ ለሌሎችም ሼር በማድረግ ያጋሩ!
👇👇👇👇👇👇
telegram:
: https://www.facebook.com/DilachenGeneralSecondaryScሽhool
youtube: https://www.youtube.com/channel/UC4-cbnEnqvn-CMr2FHvqzNQ
🙏🙏🙏✍✍✍🙏🙏🙏
24/04/2022
👏ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ትሳኤው አደረሳችሁ፣ አደረሰን!!
መልካም ፋሲካ👏👏
20/04/2022
' የትምህር ቤት ክፍያ '
የአዲስ አበባ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የ2015 የትምህርት ዘመንን የክፍያ ጭማሪ አስመልክቶ ከትምህርት ቤቶች ጋር ምክክር አድርጎ ነበር።
በዚህም ፥ በ2014 ዓ/ም ጭማሪ ያደረጉ ትምህርት ቤቶች በ2015 ዓ/ም የትምህርት ዘመን ምንም አይነት ጭማሪ ማድረግ እንደማይችሉ ተገልጿል።
ነገር ግን ላለፉት 2 እና 3 አመታት ጭማሪ ሳያደርጉ የቆዩ ትምህርት ቤቶች በሚያቀርቡት ፕሮፖዛል እና ከወላጅ ጋር በሚያደርጉት መግባባት መሰረት ጭማሪ ማድረግ ይችላሉ ተብሏል።
በአዲስ አበባ ከተማ ቅርንጫፎቻቸውን ጨምሮ 2 ሺህ ገደማ የግል ትምህርት ቤቶች አሉ፡፡ እነዚህ ትምህርት ቤቶች 400 ሺህ የሚጠጉ ተማሪዎችን ያስተናግዳሉ ፤ ይህም ከአጠቃላይ የአዲስ አበባ የተማሪ ሽፋን 43 በመቶውን ይይዛል፡፡
👇🏻👇🏻👇🏻🔔📖🗣👇👇👇
በፍጥነት ለማግኘት እንዲሁም ጠቃሚና ትምህርታዊ መረጃዎችን ለማግኘት አሁኑኑ የቴሌግራም ፣ የፊስቡክ ገፃችንን እና የዩትዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ ወይም በቀጥታ ሊንኩን በመጫን የትምህርት ቤታችን ቤተሰብ ይሁኑ ለሌሎችም ሼር በማድረግ ያጋሩ!
👇👇👇👇👇👇
telegram:
facebook: https://www.facebook.com/DilachenGeneralSecondaryScሽhool
youtube: https://www.youtube.com/channel/UC4-cbnEnqvn-CMr2FHvqzNQ
🙏🙏🙏✍✍✍🙏🙏🙏