Green Africa Times

Green Africa Times Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Green Africa Times, East Africa, Hossana.

በደ/ም/ኢትዮጵያ በሎተሪ ሽፋን የተፈፀመ ሌብነት።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ጤና ቢሮ  ምክትል ኃላፊ የሆኑት አቶ ምትኩ ...
22/08/2026

በደ/ም/ኢትዮጵያ በሎተሪ ሽፋን የተፈፀመ ሌብነት።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ የሆኑት አቶ ምትኩ ታመነ ከኢህአዴግ ሥርዐት ጀምሮ እስካሁኑ ብልፅግና መንግስት ድረስ በተለያዩ የኃለፊነት ቦታዎች ላይ የህዝብ አደራ ተሠጥቷቸው በሥልጣን ካባ የህዝብን ሀብት እየዘረፉ እንደቆዩ ታወቀባቸው።

ግለሠቡ የህዝብን እና የመንግስትን አደራ በታማኝነት መወጣት ስገባው ፤ ይህንን ታላቅ የህዝብ አደራ ወደ ጎን በመተው ከተሾመበት ጊዜ አንስቶ ሌብነቱ እንዳይታወቅበትና እንዳይደረስበት ህዝብንና መንግስትን በተለያዩ ፌክ አካውንት እያደናገረ ሳይነቃበት የህዝብ ሀብት በተለያዬ መንገድ ዘርፎ ስያከማች ቆይቷል።

ይህ ግለሠብ ምንም ከሌለበት በሥልጣን ዘመኑ ዘርፎ ያገኘውን ሀብት ማስቀመጫ ቦታ ቢያጣ በ16 ሚ/ን የኢትዮጵያ ብር #ካሶን የሚባል የጭነት መኪና ገዝቷል።

ገንዘብ ከየት አምጥቶ ገዛ ተብሎ በህዝቡ ዘንድ ጥያቄ እንዳያስነሳበት ወይንም የገንዘቡ ምንጭ ምን እንደሆነ እንዳይነቃበት የፈለገው ይህ ግለሠብ የለመደውን የማደናገሪያ ድራማ በማዘጋጀት በonline የመኪና ሎቶሪ ቆርጬ የካሶን መኪና ዕጣ በሎተሪ ደረሰኞል ብሎ የስርቆቱ ምስጥር እንዳይታወቅበት ከፍተኛ ጥረት በማደረግ ይህንን የመሠለ ምርጥ የመደበቂያ ትወናም ተውኗል።

ዳሩ ግን ከህዝብ የሚደበቅ ነገር የለምና ሎተሪ የተባለው ነገር ድራማ እንደሆነ እና መኪናው የተገዛው በተዘረፈው በመንግስትና በህዝብ ሀብት መሆኑ ተደርሶበታል።

በተጨማሪም ይህ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ከፍተኛ አመራር የሆነው ግለሠብ በክልሉ ጤና ቢሮ አማካኝነት ከሚገነቡ ሆስፒታሎች ፣ ጤና ጣቢዎች እና ሌሎች ግንባታዎች ለይ ግንባታውን ከሚያከናወኑ ድርጅቶች ጋር በመመሳጠር ዘርፎ ባገኘው ሀብት #በአዳማ እና #በቢሾፍቱ አከባቢ የገዛቸውን ዘመናዊ ቤቶችን በተመለከተ በቀጣይ ክፍላችን በዝርዝር የምናቀርበው ይሆናል።

ስለዚህ የክልሉ መንግስት ይህንን መረጃ ወስዶ ጉዳዩን በጥልቀት እንዲመረምርና ውጤቱን ለሀብቱ ባለበት ለሆነው ህዝብ እንዲያሳውቅ አደራ እንላለን።

Via : Inbox

ትኩስ መረጃዎችን ለማገኘት ሁሌም ከእኛ ጋር ይሁኑ !

ሌብነትን በጋራ ታግለን እናስቆማለን!

21/08/2026

የአማራ ክልል የሥራ ቋንቋ ~ ~ ~ ~ ~ አማርኛ
የጋምቤላ ክልል የሥራ ቋንቋ ~ ~ ~ አማርኛ
የደቡብ ምዕራብ ክልል የሥራ ቋንቋ ~ ~ ~ አማርኛ
የቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል የሥራ ቋንቋ ~ ~ ~ አማርኛ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሥራ ቋንቋ ~ ~ ~ ~ አማርኛ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሥራ ቋንቋ ~ ~ ~ አማርኛ
ሀረሪ ክልል የሥራ ቋንቋ ~ ~ ~ በተግባር አማርኛ ፤ በወረቀት ግን አደሬ፣ ኦሮምኛና አማርኛ

የድሬደዋ ከተማ አስተዳደር የሥራ ቋንቋ ~ ~ ~ ~ አማርኛ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሥራ ቋንቋ ~ ~ ~ አማርኛ

የፌድራል ተቋማት የሥራ ቋንቋ ~ ~ ~ ~ ~ አማርኛ
የፌድርሽን ምክር ቤት ስብሰባ ~ ~ ~ ~ ~ አማርኛ
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ~ ~ ~ ~ ~ አማርኛ
የምክክር ኮሚሽኑ ጉባኤ የተካሄደው ~ ~ ~ ~ በአማርኛ
የብልጽግና ጽ/ቤት እና ምክር ቤት ~ ~ ~ ~ ~ አማርኛ

የታላቁ የሀገር መከላከያ ሠራዊት የሥራ ቋንቋ ~ ~ አማርኛ

ሌላው ቀርቶ TPLF እና OLA የሚመክሩት ~ ~ ~ ~ አማርኛ

መሬት ላይ ያለው የአማርኛ ሚና በዚህ ደረጃ ሆኖ እያለ ቋንቋውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቋንቋ አድርጎ ለመሰየም አለመቻል አስገራሚ ነው። የዚህ ምክንያቱ ደግሞ የሀገራችን ኋላቀር የብሽሽቅ ፖለቲካና የተቃርኖ ትርክት ነው።

በእርግጥ አማርኛ ብሄራዊ ቋንቋ ተብሎ ተሰየመም አልተሰየመም የሚቀይረው ነገር የለም። ይሁንና ባለመሰየሙ በኋላቀር የተቃርኖ ትርክት አይምሯቸው የተበረዘ ወገኖች ግን የደስታና የእርካታ ስሜት ይሰማቸዋል። እነሱ እርካታ ይሰማቸው ዘንድም አማርኛ ብሔራዊ ቋንቋ ተብሎ አይሰየምም።

የሆነ ሆኖ አብዝሀኛው ህዝባችንን የሚያግባባ ቢያንስ አንድ ሀገራዊ ቋንቋ መኖሩ መልካም አጋጣሚ ቢሆንም ፤ በጥላቻ እና ኋላቀር የተቃርኖ ትርክት ምክንያት ይሄን በረከት ወደ እርግማን እና ልዩነት ቀይረነዋል።

Via biruk Abegaz

የጨረቃ ቢሮዬን አፅድቁልኝ!! ኦሮሚያ ክልል በራሱ ህገ መንግስት መስረት ራሱ ዋና ከተማው አዳማ ናት! የ1997 ቱን ኢህአዴጋዊ ማጭበርበር ተከትሎ ኢህአዴግ ኦሮሚያዬ ና አዲስ አበባ ኑርልኝ ...
21/08/2026

የጨረቃ ቢሮዬን አፅድቁልኝ!!

ኦሮሚያ ክልል በራሱ ህገ መንግስት መስረት ራሱ ዋና ከተማው አዳማ ናት!

የ1997 ቱን ኢህአዴጋዊ ማጭበርበር ተከትሎ ኢህአዴግ ኦሮሚያዬ ና አዲስ አበባ ኑርልኝ ብላ የክልሉ ዋና መስሪያ ቤቶች በጨረቃ አዱስ አበባ ላይ እንዲሆኑ ተደረገ ከዛም በ8 አመቱ የለውጥ ግዜያት ይሄ የጨረቃ ዋና መስሪያቤቶች ግንባታ ብበዙ ተጧጧፈ!! የኦሮሚያ ቤተ መንግስትን ጨምሮ!

አሁን በምክክሩ የኦሮሚያ ተወካዮች እየጠየቁ ያለው ጨረቃ ቢሮዬን አፅድቁልኝ ነው!

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር በአንድ ወቅት ስለ ህውሃት የጨረቃ ምርጫ ሲናገሩ "ጨረቃ ቤት መስራት ይቻል ይሆናል ነገር ግን ህግ አስክባሪ ሲመጣ እንደሚያፈርሰው ገንቢውም ቤቱም ያውቃሉ " ብለዋል ! ጨረቃዋ ራሱ ታውቃለች የሚል ደግሞ እኛ እንጨምርበት!!

እና የኦሮሚያ ተወካዮች እባካችሁን ጨረቃ ቢሮዬ ካልፀደቀ ሞቼ አትበሉ!!! አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ ተዉልን!

Via Abebe Tolla feyissa

በ አዲስ አበባ ጉዳይ "የጋራ ጥቅም" ሲሉ ፤ የመላው ኢትዮጵያዊ እንዳይመስላችሁ❗ የኦሮሚያ ክልል ከአዲስ አበባ አስተዳደር ጋር ነው። "ልዩ ጥቅም" የሚለው ስለሚያንስ በጋራ እኩል መወሰን ማ...
21/08/2026

በ አዲስ አበባ ጉዳይ "የጋራ ጥቅም" ሲሉ ፤ የመላው ኢትዮጵያዊ እንዳይመስላችሁ❗ የኦሮሚያ ክልል ከአዲስ አበባ አስተዳደር ጋር ነው። "ልዩ ጥቅም" የሚለው ስለሚያንስ በጋራ እኩል መወሰን ማስተዳደርና መካፈልን ህጋዊ ለማድረግ ነው። (ከህግ ውጭ already እየተደረገ ነው)።

ምክክሩ አጣብቂኝ ውስጥ ገብቷልበምክክር ጉባዔው ማብቂያ የኦሮሚያ ክልል ተወካዮች አዲስ ምክረ ሃሳብ እንዲካተትላቸው ያቀረቡት ጥያቄ አጠቃላይ የምክክሩን አጀንዳዎች የማጠቃለያ ጉባዔ አራዝሞታል...
21/08/2026

ምክክሩ አጣብቂኝ ውስጥ ገብቷል

በምክክር ጉባዔው ማብቂያ የኦሮሚያ ክልል ተወካዮች አዲስ ምክረ ሃሳብ እንዲካተትላቸው ያቀረቡት ጥያቄ አጠቃላይ የምክክሩን አጀንዳዎች የማጠቃለያ ጉባዔ አራዝሞታል።

"በተዘጋ ጉዳይ ላይ" ለኦሮሚያ ጥያቄ ተብሎ አሰራሩ ከተጣሰ "ራሳችንን ከምክክሩ እናገላለን" ያሉ የአማራ ክልል ተወካዮች ጉዳዩን በአትኩሮት እየተከታተሉ ነው። የዛሬው ውሎ የጉባዔውን ቀጣይ ዕጣ ፈንታ ይወስናል።

Wazema Radio ዋዜማ ሬዲዮ

የሕዝብ ውሳኔ በፓርቲ አይሻርም!Murtiin Uummataa Paartiin Hin Haqamu!በብሔራዊ ምክክር ሂደት የተገለጸው ውሳኔ ግልጽ ነው፤ አዲስ አበባ ለኦሮሚያ ክልል አልተሰጠችም፣ የኦ...
20/08/2026

የሕዝብ ውሳኔ በፓርቲ አይሻርም!
Murtiin Uummataa Paartiin Hin Haqamu!

በብሔራዊ ምክክር ሂደት የተገለጸው ውሳኔ ግልጽ ነው፤ አዲስ አበባ ለኦሮሚያ ክልል አልተሰጠችም፣ የኦሮሚያ አካል ወይም መቀመጫ እንድትሆንም አልተወሰነም። ይህንን የምክክሩን ውጤት መቀበል ባለመቻል ጉዳዩን ወደ ብልጽግና ፓርቲ ክልላዊ አመራሮች ለማስተላለፍ መሞከር የሕዝብን ድምፅ በፓርቲ ውሳኔ ለመቀየር የሚደረግ አደገኛ ሙከራ ነው። ምክክር ማለት ሕዝብ እስከሚስማማን ድረስ ጥያቄውን ደጋግሞ ማቅረብ አይደለም፤ የተገለጸውን የሕዝብ ፈቃድ ማክበር ነው። በምክክር መድረክ ያልተቀበለን ጥያቄ በፓርቲ አመራሮች በር አዙሮ ለማስገባት መሞከር ምክክሩን ትርጉም አልባ ከማድረግ በላይ የሕዝብ ውሳኔ የማይከበር መሆኑን የሚያሳይ ቀጥተኛ ስጋት ነው። አዲስ አበባ የአንድ ፓርቲ ወይም የአንድ ክልል የፖለቲካ ሽልማት አይደለችም፤ የኢትዮጵያ የፌዴራል ዋና ከተማ ናት። ስለዚህ ከዚህ በኋላ የሚፈተነው የአዲስ አበባ ዕጣ ፈንታ ብቻ አይደለም፤ የሕዝብ ውሳኔ ይከበራል ወይስ በፓርቲ ኃይል ይሻራል? የሚለው መሠረታዊ ጥያቄ ነው።

በብሔራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ውሳኔ ውስጥ ከሁሉም በላይ የወደድኩት አንድ ትልቅ ነገር አለ፤ “እኛ ሕብረ־ብሔራዊ የኢትዮጵያ ሕዝብ” በሚል የተወሰነው ውሳኔ ነው። ይህ ውሳኔ በብሔር፣ በቋንቋና በባህል ብንለያይም የአንድ ሀገር ዜጎችና የአንድ የጋራ ዕጣ ፈንታ ባለቤቶች መሆናችንን የሚያጸና ትልቅ ሀገራዊ ውሳኔ ነው። ልዩነታችን ውበታችን ነው፤ ኢትዮጵያዊነታችን ደግሞ የጋራ ቤታችን ነው።

Murtiin adeemsa Marii Biyyaalessaa keessatti ibsame ifaa dha; Finfinneen Naannoo Oromiyaa hin kennamne, kutaa Oromiyaa yookaan teessoo mootummaa Oromiyaa akka taatus hin murtoofne. Bu'aa marii kana fudhachuu dadhabuun dhimma kana gara hoggantoota naannolee Paartii Badhaadhinaatti dabarsuuf yaaluun sagalee uummataa murtii paartiitiin jijjiiruuf yaalii balaa guddaa qabu dha. Mariin jechuun gaaffii tokko hanga uummanni waan barbaadame irratti walii galutti irra deddeebi'anii dhiyeessuu miti; fedhii uummataa ibsame kabajuu dha. Gaaffii waltajjii marii irratti fudhatama hin arganne karaa biraatiin balbala hoggantoota paartii keessa deebisanii galchuuf yaaluun, mariicha hiika dhabsiisuu qofa osoo hin taane, murtiin uummataa akka hin kabajamne kan agarsiisu sodaachisaa kallattiidha. Finfinneen badhaasa siyaasaa paartii tokkoo yookaan naannoo tokkoo miti; magaalaa mootummaa federaalaa Itoophiyaa ti. Kanaafuu, kana booda wanti qormaata keessa jiru hiree Finfinnee qofa miti; gaaffiin bu'uuraa, “Murtiin uummataa ni kabajamaa moo aangoo paartiitiin ni haqamaa?” jedhu dha.

በትግራይ ክልል እየተፈፀሙ ያሉ የድሮን ጥቃቶችዛሬ ነሐሴ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 5፡00 ሰዓት ላይ በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ ሁለት ቦታዎች ላይ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት 13 ሰዎች ከ...
20/08/2026

በትግራይ ክልል እየተፈፀሙ ያሉ የድሮን ጥቃቶች

ዛሬ ነሐሴ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 5፡00 ሰዓት ላይ በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ ሁለት ቦታዎች ላይ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት 13 ሰዎች ከባድና ቀላል ጉዳት እንደደረሰባቸው የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር አብርሃ ሐጎስ ለዶቼ ቬለ አረጋገጡ። ስለጉዳዩ ከኢትዮጵያ ፌዴራል መንግሥትም ሆነ ከሀገር መከላከያ ሠራዊት የተባላ ነገር የለም።

DW Amharic

  የሆዴን በሆዴ  ያፌን በንጉርጉሮ  እንዳልናገረው ቀኔ  አይደለ ዘንድሮ ( አለማየሁ እሸቴ ነብይ ነበር እንዴ?) ኧረ እንደው ይመኙሻል እረ እንደው ይመኙሻል  በስሜት ቢጓዙ ከየት ያገኙሻል...
20/08/2026



የሆዴን በሆዴ ያፌን በንጉርጉሮ
እንዳልናገረው ቀኔ አይደለ ዘንድሮ

( አለማየሁ እሸቴ ነብይ ነበር እንዴ?)
ኧረ እንደው ይመኙሻል
እረ እንደው ይመኙሻል
በስሜት ቢጓዙ ከየት ያገኙሻል
አዲስ አበባ ቤቴ
አዲስ አበባ ቤቴ
አለማየሁ እሸቴ

አዲስ አበባ፤ በታዩ ደንደኣ ላይ የተሰጠው ፍርድ ጸና።የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ መንግሥት ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በቀድሞ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ደ ኤታ  አቶ ታዬ ደንደኣ ላይ በስ...
20/08/2026

አዲስ አበባ፤ በታዩ ደንደኣ ላይ የተሰጠው ፍርድ ጸና።

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ መንግሥት ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በቀድሞ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ደ ኤታ አቶ ታዬ ደንደኣ ላይ በስር ፍርድ ቤት የተሰጠውን የአራት ዓመታት እስር ፍርድ አጸና።

ትናንት ረቡዕ ነሐሴ 13 ቀን 2018 ዓ.ም. አዲስ አበባ ውስጥ ያስቻለው ፍርድ አቶ ታዬ ያቀረቡትን ይግባኝ ውድቅ በማድረግ ነው ውሳኔውን ያስተላለፈው።
አቶ ታዬ ከዚህ በፊት በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት በቀረበባቸው «ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ የጦር መሳሪያ ይዞ መገኘት» በሚለው ክስ የሰባት ዓመት እስር ከተወሰነባቸው በኋላ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት አቤት ብለው ቅጣቱ ወደ አራት ዓመት እስር ተሻሽሎሏል።

ባለቤታቸው ወ/ሮ ስንታየሁ ዓለማየሁ ለዶቼ ቬለ እንደተናገሩት በዚህም ላይ ቅሬታ የነበራቸው አቶ ታዬ አምስት ነጥቦችን ዘርዝረው ለፌዴራል ሰበር ሰሚ ችሎት አቤት ቢሉም የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ትናንት በዋለው ችሎት ብይኑ ጸንቶባቸዋል። አቶ ታዬ የጦር መሳሪያ ይዘው መገኘታቸውን ከዚህ በፊትም በነበረው የክስ ሂደት አላስተባበሉም ያሉት ባለቤታቸው፤ ከሌላው ዜጋ እኩል የመዳኘት መብት ስለመነፈጋቸውና ካቀረቡት አምስት ተከላካይ ምስክሮች የሁለቱ ቃል ብቻ ተሰምቶ በከፍተኛ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ መሰጠቱንም በቅሬታ ማቅረባቸውን ገልጸዋል።

አቶ ታዬ ትናንት ውሳኔው ከጸናባቸው የክስ ጭብጥ በተጨማሪ አቃቤ ሕግ ይግባኝ በጠየቀበት ሌላው ተጓዳኝ የክስ ጭብጥ ላይ ለጥቅምት 17 2019 ዓ.ም. መቀጠራቸውን መረጃዎች ያስረዳሉ።

"ሕዝብ ይወቅልን‼" ከተመካካሪዎች የተላከ መልዕክት"እኛ በበርካታ ጫና ውስጥ  ሆነን በገባንና በቻልነው  ሁሉ  ጥረት አድርገን ምክክሩን ትናንት ጨርሰናል። ከአሁን በኋላ ከሂደቱ  ውጭ የሚደ...
20/08/2026

"ሕዝብ ይወቅልን‼"

ከተመካካሪዎች የተላከ መልዕክት

"እኛ በበርካታ ጫና ውስጥ ሆነን በገባንና በቻልነው ሁሉ ጥረት አድርገን ምክክሩን ትናንት ጨርሰናል። ከአሁን በኋላ ከሂደቱ ውጭ የሚደረግ የትኛውም ውሳኔ እኛን የማይመለከት፣ እውቅናም የማንሰጠው፣ ህገወጥ ተግባር መሆኑን ሕዝብ ይወቅልን።"

Address

East Africa
Hossana

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Green Africa Times posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share