26/05/2026
Addis Ababa University
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
26/05/2026
26/05/2026
AAU Connect Vol. XIV (April 2026) is out now!
This edition, titled “Academic Diplomacy at AAU,” explores how universities are increasingly becoming spaces for global dialogue, collaboration, and international engagement.
From strategic partnerships and research collaboration to alumni impact and knowledge diplomacy, the volume highlights how Addis Ababa University continues to move beyond borders while staying rooted in its Pan-African vision.
Read the latest volume here: https://volume.aau.edu.et/5,3d9c4dd5983b34
17/05/2026
በትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ዘርፍ ሲሰጥ የቆየው የሙያ ብቃት የአሰልጣኞች ስልጠና (ToT) ተጠናቀቀ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የንግድ ሥራ ት/ቤት የሎጀስቲክስ እና ሰፕላይ ቼይን ትምህርት ክፍል ውስጥ በሎጀስቲክስ ዘርፍ ሲሰጥ የቆየው የአሰልጣኞች ስልጠና (ToT) በስኬት ተጠናቋል።
ውጤታማ የገጽ ለገጽ ስልጠና አሰጣጥ ላይ ያተኮረው ይህ የአሰልጣኞች ስልጠና (ToT) ተሳታፊዎች በተግባር ላይ የተመሰረቱ እና ሰልጣኝ-ተኮር የሆኑ ስልጠናዎችን የማቀድ፣የማመቻቸት እና የመገምገም አቅማቸውን እንደሚያጠናክርላቸው ተገልጿል። ተሳታፊወች ያገኙትን ክህሎት በመጠቀም፣ በቀጣዮቹ ሳምንታት በአዲስ አበባና በክልል ማዕከላት ለሚመረጡ 2,000 ሰልጣኞች በጭነት ሎጅስቲክስ ዘርፍ እውቀትን መሰረት ያደረገ ስልጠና የሚሰጡ ይሆናል።
በማጠቃለያ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር ደኤታ ክቡር አቶ ደንጌ ቦሩ፤ ሎጅስቲክስ ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ ያለውን የላቀ ጠቀሜታ አብራርተው፣ ዘርፉ ብቃት ባላቸው ባለሙያዎች መመራት እንዳለበት አስታውሰዋል። አክለውም የሰው ሁብት ልማት እና እውቀትን መሰረት ያደረገ አሰራር በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ቁልፍና ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑን እንዲሁም መሰል
የአቅም ግንባታ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ገልፀዋል።
በስልጠናው ላይ ከተለያዩ የዘርፉ ተቋማት፣ ከክልል ትራንስፖርት ቢሮዎች፣ ከፌደራል ፖሊስ እና ከግል ኦፕሬተሮች የተውጣጡ ባለሙያዎችና የስራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።
Green, Clean and Safe Campuses
Addis Ababa University Research, Innovation And Fairs Week (RIFW 2026)
In partnership with the Ethiopian Artificial Intelligence Institute- የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት and Industrial Parks Development Corporation - Ethiopia
07/05/2026
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ “የአንድ ግጥም አንድ ወግ ምሽት”…
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የባህል ማዕከል ዘወትር ረቡዕ ምሽት የሚካሄደውና ስመ-ጥር የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎችንና መሪዎችን የሚያሳትፈው “የአንድ ግጥም አንድ ወግ” መርሃ-ግብር በ54ኛው ሳምንት ዝግጅቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰውን በክብር እንግድነት አስተናግዷል።
አቶ መስፍን ከተማሪነት ዘመናቸው ጀምሮ እስከ አየር መንገዱ መሪነት የደረሱበትን አነቃቂ የህይወትና የሥራ ልምድ ለታዳሚው አካፍለዋል።
በተጨማሪም ዩኒቨርሲቲው ባለፉት 75 ዓመታት ለተለያዩ ብሔራዊ ተቋማት ብቁና የሰለጠነ የሰው ኃይል በማፍራት ረገድ እየተወጣ ያለውን ከፍተኛ ሚና አድናቆታቸውን ገልጸው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በምርምርና በተለያዩ የልማት መስኮች በጋራ ለመስራት እንዲሁም ዩኒቨርሲቲውን በልዩ ልዩ ዘርፎች ለመደገፍ ዝግጁ መሆኑን አስታውቀዋል።
የዋና ሥራ አስፈፃሚው በፕሮግራሙ ላይ መገኘት ለተማሪዎች ትልቅ መነሳሳትን እንደሚፈጥር እና በዩኒቨርሲቲውና በአየር መንገዱ መካከል ያለው ዘመናዊና ስትራቴጂካዊ ትብብር ይበልጥ እንደሚያጠናክር የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ አረጋግጠዋል።
06/05/2026
ለሦስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የጥናት፣ የምርምር እና የሥራ አውደ ርዕይ ሳምንት ተከፈተ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 7ኛው የምርምርና የሥራ አውደርዕይ ሳምንት "Advancing Education through Research Digitalization Innovation and Industry partnerships" በሚል መሪ ቃል ዛሬ ሚያዝያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በደማቅ የመክፈቻ መርሀ ግብር ተከፍቷል።
የዘንድሮው የምርምር ሳምንት በዩንቨርሲቲው እየተተገበረ ከሚገኘው የ5 አመቱ ስትራቴጂክ እቅድ ጋር የተጣጣመ አላማ ያለው መሆኑን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) የመክፈቻ ንግግር ባደረጉበት ወቅት ገልጸዋል።
አውደ ርዕዩ በአሁኑ ወቅት በሀገር አቀፍ እና በአለም አቀፍ ደረጃ ትኩረት የተሰጠውን የዲጂታላይዜሽን እንቅስቃሴ ለትምህርት ስርዓት፣ ለፈጠራ እና ከኢንዱስትሪዎች ጋር ማስተሳሰር ላይ ያተኮረ የምርምር ሳምንት መሆኑን የዘንድሮው የምርምር ሳምንት ዋና አዘጋጅ የሆነው የትምህርትና ቋንቋዎች ጥናት ኮሌጅ ኤክስኩቲቭ ዲን የቆየአለም ደሴ (ዶ/ር) ጠቁመዋል።
በዕለቱ ከመክፈቻው መርሀ ግብር ጎን ለጎን የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች እና የዪኒቨርሲቲውን ምሁራን ያካተተ በሀገሪቱ የዲጂታላይዜሽን ጉዞ ላይ ያተኮረ ውይይት ተካሂዷል።
በቀጣይ ቀናት በሚኖሩ መርሃ-ግብሮች የተለያዩ ኮሌጆች ምሁራን የተሰሩ የምርምር ውጤቶች የሚቀርቡ ሲሆን የላቀ ግኝት ላገኙ እውቅና የመስጠት መርሃ ግብርም የሚካሄድ ይሆናል።
06/05/2026
Happening Now…
Addis Ababa University Research, Innovation And Fairs Week (RIFW 2026)
In partnership with the Ethiopian Artificial Intelligence Institute- የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት and the Industrial Parks Development Corporation - Ethiopia
ግንባር ቀደም የምርምር ዩኒቨርሲቲ የመሆን ጉዞ…
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን ለመቅረፅ እና ዓለም አቀፋዊ ትብብርን ለማጠናከር የሚያስችሉ በጥናት እና ምርምር የተደገፉ መፍትሄዎችን በማመንጨት፣ ግንባር ቀደም የምርምር ተቋም የመሆን ራዕዩን በተጨባጭ እያረጋገጠ ይገኛል።
ዩኒቨርሲቲው ከተባበሩት መንግሥታት የዓለም የምግብ ፕሮግራም (WFP) እና ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር፣ በመካከለኛ ደረጃ የሚታይ የተመጣጠነ ምግብ እጥረትን ለመከላከል የሚያስችሉ ስልቶችን በኢትዮጵያ የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ውስጥ ለማካተት የሚያስችል ሳይንሳዊ የምርምር ውጤት ይፋ አድርጓል።
ይህም ዩኒቨርሲቲው ከዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር ያለውን ስትራቴጂካዊ ግንኙነት ለማህበረሰብ አገልግሎትና ለዘላቂ ሀገራዊ ልማት ለማዋል ያለውን ከፍተኛ ብቃትና ጽኑ ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው።
24/04/2026
የቻይና-አፍሪካ የምርምር ማዕከልን (China-Africa Research Center) በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለማቋቋም የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈረመ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በቻይና-አፍሪካ ኢንስቲትዩት ትብብር የሚቋቋመው ይህ ማዕከል በቻይና እና በአፍሪካ መካከል ያለውን አካዳሚያዊ ትብብር በማጠናከር፣ የባህል ልውውጥን ለማሳደግ እና የጋራ የምርምር ሥራዎችን ለማከናወን ያለመ ነው።
የማዕከሉ መቋቋም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ለዓመታት የዘለቀ ጠንካራ የንግድ፣ የኢንቨስትመንት እና የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ውጤት መሆኑን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) በስምምነት ስነ-ስርዓቱ ወቅት ገልጸዋል።
የቻይና-አፍሪካ ኢንስቲትዩት ፕሬዝዳንት ክቡር ዬ ሃይሊንግ (Ye Hailing) በበኩላቸው ማዕከሉ በቻይና መንግሥት ከሚደገፉት 25 የቻይና-አፍሪካ ምርምር ማዕከላት መካከል እንዱ መሆኑን ጠቅሰው በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ሁሉን አቀፍ ስትራቴጂካዊ አጋርነትም ይበልጥ እንደሚያጠናክረውም ጠቁመዋል።
Click here to claim your Sponsored Listing.
Location
Category
Contact the school
Telephone
Website
Address
Addis Ababa University
Addis Ababa
1176