02/10/2019
ብሩሕ ኢትዮጵያ
(የለውጥ አሻራ)
ወደ እድገትና ብልፅግና የሚደረግ ጉዞ የተቃና ይሆን ዘንድ እውቀት እጅግ አስፈላጊው ስንቅ ነው።
ሀገራችን ላቀደችውና ላለመችው የእድገት ግብ፣ የእውቀት ማእከል በሆነው ትምህርት ቤት የሚገኙ ተማሪዎችን በማነቃቃትና ለታላቅ አላማ በማዘጋጀት ሒደት ላይ ታላቅ ርብርብ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
ተቋማችን ብሩሕ ኢትዮጵያም ይህንን አላማ ለመደገፍ በሚል በአዳማ ከተማ የሚገኙ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን የመሸለምና የማነቃቃት እቅድ አንግቧል።
በዚህም መሰረት በ8ኛ፣ በ10ኛ እና በ12ኛ ክፍል ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ የአዳማ ከተማ ምርጥ ተማሪዎች ታላላቅ ኡለሞች፣ ዳኢዎች፣ ወላጆች እና ምሁራን በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ ለመሸለም ዝግጅቱን አጠናቋል።
ስለዚህም:–
1. ለ8ኛ ክፍል … 90 እና ከ90 በላይ
2. ለ10ኛ ክፍል … 4 እና ከ4 በላይ
3. ለ12ኛ ክፍል … 450 እና ከ450 በላይ ያመጣችሁ በአዳማ ከተማ እና በአካባቢው የምትገኙ ተማሪዎች ከስር በተጠቀሱት አድራሻዎች መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
ውጤት ስታሳውቁ:–
1. ሙሉ ስም…
2. ፆታ…
3. የት/ት ቤት ስም
4. ውጤት ከማስረጃ ጋር (ፎቶ) እና ትራንስክሪፕት
5. ስልክ ቁጥር
መረጃዎችን በማጠናቀር
በስልክ: #+251911723051
. #+251986584282
#+251953913935
በኢሜይል: .com
.com
በቴሌግራም: #
. #
እንድትመዘገቡ እንጠይቃለን።
17/09/2019
16/09/2019
14/09/2019
03/09/2019
28/08/2019
24/08/2019
22/08/2019
17/08/2019