26/08/2024
[ፍቅር ተወደደ] የሚለው የኃይለእየሱስ ፈይሳ ዘፈን ላይ ያለች አንዲት ሀረግ ነገር ብክንክን አድርጋ ታስቀኛለች።
"የቆላውም መጥቶ እምዬ ይላታል"
የቆላው😓
Fore new Megazen ande News Service
26/08/2024
[ፍቅር ተወደደ] የሚለው የኃይለእየሱስ ፈይሳ ዘፈን ላይ ያለች አንዲት ሀረግ ነገር ብክንክን አድርጋ ታስቀኛለች።
"የቆላውም መጥቶ እምዬ ይላታል"
የቆላው😓
13/06/2020
┉✽̶»̶̥🌺 #የማይሽር ጠባሳ🌺̶̥✽̶┉
❣:¨·.·¨: ❣
══════❁✿❁ ══════
🌺🌺ክፍል 2
እውነተኛ ታሪክ የምጠቀመው ስም የታሪኩ ባለቤቶች እንዳልሆኑ ልገልፅ እወዳለው
አዲስ አበባ ደረስን ግን የህይወቴ የመጀመርያው ስቃይ እዚህ ጀመር
አዎ ገና ልጅነቴን ሳልጨርስ ጠግቤ ሳልጫወት በእናት እቅፍ ውስጥ እንደ ልጅ ሳልተኛ በልጅነቴ በጨቅላነቴ ገላ የቤት ውስጥ ስራ መስራት ጀመርኩ
አስተምራታለው እኔ እንደ ልጆቼ አድርጌ አሳድጋታለው ብላ ያዘነች መስላ ከወንድሜ የነጠለችኝ አውሬ የስቃይ በር ከፋቼ ነበረች
ትምህርቱ ቀርቶ ምግብ በአግባቡ አሰጠኝም ከልጆችዋ ትራፊ እንዲሁም አጋጣሚ እንግዳ ከመጣ ያ ትራፊ ነበር እንደ ውሻ የኔ ቀለብ
እሱንም ተመስገን ብዬ እመገብ ነበር
መቼም እራብ ድንጋይስ ያስበላ የለ እኔም ያገኘውትን የተሰጠኝን እመገባለው
ከዚህ ባሻገር ግን ያለ አቅሜ ከምሰራው ስራ ባሻገር ድብደባው ከእለት ወደ እለት ይበረታብኝ ነበር
በበአላት ወቅት ለልጆችዋ ልብስ ሲገዛ ለኔ ግን አደለም ልብስ ምግብ እንኳን አላገኝም ነበር አንዳንዴ እንደ ውሻ እቃ ቤት ሁላ ይቆለፍብኛል
ፈጣሪ ሆይ እኔ ጨቅላ ልጅህን አስበኝ እላለው የምጣራው ማንም ስላልነበረኝ
ይህ ስቃይ በረታ የሚያዩ የጎረቤት ሰዎች አንዳንዴ እስዋ በሌለችበት ምግብ ደብቀው ይሰጡኝ ነበር
አዎ ሳይኖራት ቢሆን ማንም ባላዘነባት ነገር ግን ቤትዋ ሙሉ ከመሆኑ ባለፈ ለማንም ይተርፍ ነበር
ይህ ስቃይ የዱላው የእራቡ ከጊዜ ወደ ጊዜ አቅም እያሳጣኝ መጣ
አስታውሳለው አንድ ወቅት በአል ነበር እንደ ተለመደው ምግብ ሰራርታ እኔም ያቅሜን አግዤ ሳበቃ በጣም እራበኝ እስከ ዛሬ ስኖር አንድም ቀን እራበኝ ስጪኝ የሚል ቃል ወቶኝ አያውቅም ነበር ዛሬ ግን አፍ አውጥቼ እራበኝ እባክሽ ምግብ ስጭኝ አልኳት
እስዋ ግን ከለከለችኝ እኔም ከምሞት ብዬ አጠገቤ ያገኘውትን የቡና አሻራ በውሀ በጥብጬ ጭልጥ አድርጌ ጠጣው እራቤንም አስታገስኩ ውስጤ ግን ጥላቻ በእስዋ ላይ አሳደረ
እንዲ እያልኩ 2 አመታት በስቃይ አለፈ
ታድያ አንድ ቀን ዘመድ የሆነችው ሰብለ ሁሌም ስቃዬን ታይ ስለነበር እሷ በሌለችበት መጣች
ቅድስቴ ነይ አንድ ድርጅት አለ ያስተምራሉ እዛም ትቀመጫለሽ የዚህ ቤት ስቃይ ያበቃል ብላ አዛኝ መስላ አታላ አሳልፋ ለሌሎች ሰዎች ሸጠችኝ
ምን አደረኩ በልጅነቴ በየትኛው ሀጥያቴ ነው ምቀጣው
አሁን የተሸጥኩበት ቤት 1 ልጅ ያላት ሴት ነበረች በርግጥ ትምህርቴን ብታስተምረኝም ምግብ ብበላም ግን ሰይጣናዊ ባህሪ ስለነበራት ያለ ምክንያት ትደበድበኝ ነበር
አዎ የሰው ልጅ አደለም ገና በጨቅላነቱ ይቅርና ቢያረጅም በፍቅር ሊያዝ ይገባዋል ማንም ይውለደው ማንም ሁሉም የፈጣሪ ፍጡር ስለሆነ ሊከበር ይገባው ነበር
ይህ ግን ለኔ ህልም ቅዥት እንጂ በእውን የማይሆን ነገር ነው
ትምህርቴን የቀን እየተማርኩ እንደ አቅሜ የቤት ውስጥ ስራ እየሰራው ጎን ለጎን ደግሞ ከ አቅሜ በላይ የሆነ ዱላ እርግጫ እየቻልኩ ኑሮዬን መግፋት ጀመርኩ
ልጅነቴ በአንድ በኩል የሰው ፍቅር ሲሰጠኝ በሌላ በኩል ደግሞ በአስሪዎቼ መጥፎ ነገር ነበር
ሳስበው ዛሬ ላይ አንዳንዴ ቢያስቀኝም ይበልጡኑ ግን አዝናለው
አንድ ወቅት እቺ አሰርዬ እርጉዝ ነበረች እና እኔን ለመምታት ዱላ ይዛ ሰፈር ለሰፈር ታባረኛለች ነገር ግን ሰዎች እርግዝናዋ ከወደቀች መጥፎ እንደሆን እየጮሁ ቁሚ ቁሚ አታስሩጫት ይሉኝ ነበር እኔም ዱላው ላይቀር ለምን እሷስ ትጎዳ ብዬ ቆሜ እመታ ነበር
ነገር ግን አንድ ወቅት ላይ ግን ከትምህርት ቤት መጥቼ ዩንፎርሜን ሳላወልቅ ገና ከበር አውሬ ሆና ጠበቀ
13/06/2020
┉✽̶»̶̥🌺 #የማይሽር ጠባሳ🌺̶̥✽̶┉
❣:¨·.·¨: ❣
══════❁✿❁ ══════
🌺ክፍል አንድ
🌹🌹🌹እውነተኛ ታሪክ
ታሪኬ የሚጀምረው ገና የሁለት ወር ህፃን እያለው እናቴ ለእንጀራ እናቴና ለ አባቴ እኔና ታላቅ ወንድሜን ጥላን የጠፋች እለት ነበር
አዎ ገና የሁለት ወር ጨቅላ እያለው በእንጀራ እናቴ እጅ እድገቴን ጀመርኩ
በርግጥ አባቴ ልጆቹን ወዳጅ ስለነበር እንጀራ እናታችን እኛን ለመጉዳት መንገድ አልነበራትም
ውልደቴም እድገቴም በ ወለጋ ነቀምቴ ነበር አባታችን የራሱ ገቢ ነበረው እናታችን ጥላን ብጠፋም ታላቅ ወንድሜ እጅግ ይወደኝ ስለነበር አንድም ቀን እንድከፋ አይፈልግም ይበልጥ ከአባቴና እንጀራ እናቴ ወንድሜ ይጠብቀኝ ነበር
ከዛ ባሻገር የእርሻ ቦታም ነበረን
አባቴ ከመደበኛ ስራው ባሻገር የእርሻ ቦታውን ዘወትር የመጎብኘት ልምድ ነበረው
ግን ከለታት በአንዱ ቀን ከስራ መልስ ወደ እርሻ ቦታ የመሄድ ልምድ ስላለው እንደ ልማዱ ወደ እርሻ ቦታ አመራ
ነገር ግን የዛሬው የእርሻ ቦታ ጉብኝቱ የህይወቴን ሁለተኛ ምእራፍ ገና በለጋነቴ በጨቅላነቴ እንድጀምር አረጋት
አባቴ በእባብ ተነድፎ በሰዎች እርዳታ እቤት በገባ በ3 ቀን በህይወት አጣነው
ነገር ግን አባቴ ህይወቱ ከማለፉ በፊት ለእንጀራ እናቴ ቃል አስገባት
"ልጆቼን በምድር ሰጥቼሻለው በሰማይ እቀበልሻለው "
ይህ ቃል በልጅነት አእምሮዬ ተፅፎ ቀረ
በወቅቱ ወንድሜ እንጀራ እናቴ ስታለቅስ እሱም አብሮ እያለቀሰ ነበር እኔ ግን ልጅነቴ ምኑም እንዲገባኝ አላደረገም ነበር
እንጀራ እናቴ ከሌላ የወለደቻቸውና በትዳር ላይ የሚገኙ ሁለት ሴት ልጆች ነበርዋት
አባቴ ከሞተ በኃላ ግን እንጀራ እናቴም ጤንነት ስለማይሰማት ልጆችዋ ወሰድዋት ።ይህ 3ኛው ምእራፍ የኔና የወንድሜ ነበር እኔና እኔን በ6 አመት ልዩነት ያለን ወንድሜ ብቻችንን ኦና ቤት ታቅፈን ቀረን
የሚላስ የሚቀመስ በሌለበት ቤት ውስጥ ኑሮአችንን መግፋት ጀመርን
ወንድሜ ከኔ የተሻለ ስለነበር ቀን ቀን ምግብ ፍለጋ ሄዶ ማታ ለሱ ሳይበላ ለኔ ይዞ ይመጣ ነበር
በዚህ ሁኔታ ግን ስላልቻልን ጎረቤት ተጠጋን እሱ በእረኝነት እኔ ደግሞ እንደ ልጅነት ልንኖርበት
አዎ የተጠጋናቸው ሰዎች ያላቸው ስለነበሩ ወንድሜ ለኔ መስዋት በመሆን ደሞዙ የኔ በሳላም በደስታ እዛ ቤት መኖር ብቻ ነበር
እንዲ እንዲ እያልን ለአንድ አመት ኖርን
በመሀል የምንኖርባቸው ሰዎች አዲስ አበባ በትዳር የምትኖር ትልቅ ልጅ ነበራቸው
በተሰብዋን ለመጠየቅ በምትመጣበት ሰአት እኔ አይንዋ ውስጥ ገባው
ስለ እኔ ጠየቀች ሁሉንም ተረዳች አዘነችም ወስዳም እንደምታስተምረኝ ቃል ገባች
ወንድሜም በገጠመኝ እድል ደስተኛ ስለነበር ሳያቅማማ ፈቀደ
እኔም ልጅነቴ እንዳለ ያገኘውት እድል አስደስቶኝ ስለ እኔ መሰዋት የሚሆነውን ወንድሜን ትቼ ወደ አዲስ አበባ ገሰገስኩ...... ታሪኩ እንዲቀጥል ሼር 👍👍
✍ይቀጥላል........ ━━━━━━━✦✿✦━━━━━━━
...........................%.........................
••●◉Join us share
┄┄┉┉✽̶»̶̥🌹✿🌹»̶̥✽̶┉┉
10/05/2020
Mari Tija:
....
ፀሀይዋን ተመልከታት አታምርም ? ጨረቃዋስ ከዋክብቱስ ዛፎቹ ወንዙና ተራራውስ አያምሩም ? ያምራሉ ። እኚ ሁሉ ግን ያልፉሉ አንተ ግን በሞት ከዚህ አለም ብትለይ እንኳን በሰማይ ለዘላለም ትኖራለህ ። ፈጣሪ ፍጥረታትንን ሁሉ በቃሉ በመናገር እና በሀሳብ (በሀልዮ) ሲፈጥር አንተን ግን በእጁ አሽሞንሙኖ ፈጥሮሀል። አንተ ማለት ክርስቶስ እነሆ በደጅ ቆሜ አንኳኳለው ማንም ሚከፍትልኝ ቢኖር ገብቼ እራቴን ከእርሱ ጋር እበላለው ብሎ የተናገረልህ ። ፈጣሪ አለምን ከፈጠረበት ጥበብ ይልቅ አለምን ያዳነበት ጥበቡ ይበልጣል ተብሎ የተነገረልህ ዋጋ የከፈለልህ የመንግስቱ ወራሽ ውድ ልጁ ነህ።
ምን አልባት ዛሬ በተለያየ ሱስ ተይዘህ ይሆናል ምን አልባት ስራ በማጣት ፍቅረኛ በማጣት ትሰቃይ ይሆናል ።ምን አልባት ቤተሰብህ ወገንህ ተስፉ ቆርጦብህ ይሆናል ። ምን አልባት ሞትህን እየተመኘህ ይሆናል። ግን አይዞህ ፈጣሪ በአንተ የጀመረውን ስራ ሳይጨርስ አትሞትም። Never Give Up በቀላሉ ተስፉ አትቁረጥ ። ተመልከት ሰይጣን ተስፉ የለውም ግን ተስፉ አይቆርጥም ። ሰው ግን ተስፉ አለው ግን ተስፉ ይቆርጣል። 1 አምፖል ሽቦው ከረገፈ አያበራም ጠርሙስ ይሆናል ። የሰውም የብርሃን ሽቦው ተስፉ ነው ። ሰው ተስፉ ቢቆርጥብህ እራስህም ተስፉ ብትቆርጥ የፈጠረህ በአንተ ላይ ተስፉ አይቆርጥብህምና አይዞህ ። 1 ጠጠር አንስተህ ተራራ ላይ ብትወረውር ተራራው ምንም አይሆንም ጠጠሩ ተንከባሎ እግሩ ስር ይሆናል ። ያን ጠጠር አንስተህ መስታወት ላይ ብትወረውረው ግን መስታወቱ ይሰባበራል። ጠጠሩን በችግር እንመስለውና ችግር ወዳንተ ሲመጣ እንደ መስታወቱ አትሰባበር እንደ ተራራው በቁጥጥር ስር አውለው ። 1 የተለኮሰ የክብሪት እንጨት ጭድ ላይ ብትጥለው ይቀጣጠላል ። ውሀ ላይ ብትጥለው ግን ውሀው ያጠፉዋል ። የሚያቃጥሉ ነገሮች በህይወትህ ውስጥ ሲከሰቱ እንደ ጭድ አትቀጣጠል እንደ ውሃው አጥፉቸው ። 1 በረዶ ፀሀይ ላይ ብታረገው ይቀልጣል የተቦካ ሲሚንቶ ፀሀይ ላይ ብታረግ ግን ይጠነክራል። እንደ ፀሀይ የከረሩ ችግሮች በህይወትህ ሲያጋጥሙህ እንደ በረዶ አትቅለጥ እንደ ሲሚንቶው ጠንክርባቸው። እህቴ ምን አልባት ለስራ ጉዳይ በተለያየ ሀገር ውስጥ ሆነሽ ይሆናል ያለሽው ።መፈጠርሽ ሴትነትሽም አስጠልቶሽ ይሆናል። ግን ክርስቶስ ወደ አለም ሲመጣ ምድራዊ እናት እንጂ አባት አላስፈለገውም የሴት ልጅ ተብሎ እስኪጠራ ድረስ ማርያም ብቻዋን ነው ያሳደገችው። በኛ ቤተክርስቲያን ህንፃ ቤተክርስቲያኑ ተሰርቶ አለቀ የሚባለው ጉልላቱ ተሰርቶ ሲያልቅ ነው ። ፈጣሪም ፍጥረትን ሁሉ ፈጥሮ ሲጨርስ አዳምን ፈጠረ በመጨረሻም ከጎኑ ሄዋንን ወይም አንቺን የስነ ፍጥረት ጉልላት አርጎ ፈጠረሽ። ስለዚህ እህቴ ክብርት ፍጥረት ነሽና ደስ ይበልሽ።
ስላም እግዚአብሔር በያለንበት ይብዛልን።
መልካም ምሽት ይሁንላችሁ✝
&
30/03/2020
❕❕ቀላል አካብዳለውሁ❗❗❕❕
#ስለበሽታው ደጋግሜ ስነግር አካበድክ/ሽ ለምትሉኝ
አካብዳለው!*,
#ማስክ አድርገህ/ሽ ሲያይህ/ሽ አካበደ😷 ለሚልህ/ሽ
አካብዳለው!**
#ሳኒታይዘር ስጠቀም አታካብድ ለሚልህ/ሽ
አካብዳለው!
#አልጨባበጣም ስትለው/ይ አካበደ/ች ለሚልህ/ሽ
*አካብዳለው!
#አልጠጋጋም ስትለው/ይ አታካብድ/ጂ ለሚልህ/ሽ
አካብዳለው!
ላይ መረጃ ስለጥፍ አታካብድ/ጂ ለሚልህ/ሽ
አካብዳለው!
#23 ሰው ብቻ ነው አታካብድ/ጂ ለሚልህ/ሽ
አካብዳለው!
#ሰው መቼ ሞተ አታካብድ/ጂ ለሚልህ/ሽ
አካብዳለው!
ኑ አብረን እናካብድ! ለሰውም ሆነ ለእራሳቺን ሞት ምክኒያት አንሁን❗❗
27/03/2020
23/03/2020
እኔ ልብህ አይደለሁም ግን ትናፍቀኛለህ😘😘😘😘
እኔ ቤተሰብህ አይደለሁም ግን ስላንተ እጨነቃለሁ😍😍😍😍
እኔ ደምህ አይደለሁም ግን ህመምህ ያመኛል❤️❤️❤️❤️
እኔ ስጋህ አይደለሁም ግን ህመምህን ልጋራህ ዝግጁ ነኝ❤️❤️❤️💛💛💚💚 ምክንያቱም አፈቅርሀለሁ💓💗💖💞
ተጨማሪ ለማግኘት ፔጁን
22/03/2020
Rip Italy 😨😷
22/03/2020
በጣሊያን ዛሬ 5,560 ሰዎች በቫይረሱ የተጠቁ ሲሆን 651 ሰዎች በቫይረሱ ምክንያት ሞተዋል። በአጠቃላይ ጣሊያን 59,138 በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ሲኖሩ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት እስከ ዛሬ በጣሊያን 5,476 ሰው ሞቷል።‼️
አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት ፔጁን
የቴሌግራም መገኛቺን
20/03/2020
ለእሁድዎ!
❤
ድሮ መች ነበረ ዘር መርጦ ጎረቤት
በጥዋቱ በጥንቱ በነ አባብዬ ቤት
እድር ማህበሩ ሲያሰባስብዋቸው
መች ይጠየቅ ነበር የዘር ሀረጋቸው
የአዳም ፍጥረቱ አንድ አይደለም ወይ
ለምን አስር ሆነ የሰው ልጅ ፀባይ
እፁብ ይቅር ብለህ በደላችንን
አንድ አምላክ ነህና
እኛንም አንድ አድርገን
እንድ አድርገን ጌታ !!!
ሸጋ ሸጊቱ ቅዳሚት!💚💛❤
"ናካይታ"💚
👉👉👉👉 #ጆን ትዩብ
🌻 🌻
🌷 🌷
🌷 🌷
19/03/2020
😳የ አይን ፍቅር💖/sight love/
የዓይን ፍቅር /Sight love/ የምንለው አንድን ግለሰብ በተደጋጋሚ በመመልከትና አዕምሮአዊ ስዕል በመሳል የፍቅር ስሜትን ውስጣችን ውስጥ ማዳበር ማለት ነው፡፡
ንቁ የሆነው የአዕምሯችን ክፍል በአካባቢው ያሉ መረጃዎችን የማሰባሰብ ኃይል ያለው ክፍል ነው፡፡
ይህ የአዕምሯችን ክፍል ከአካባቢው ያገኘውን መረጃ የማጠራቀሚያ ቦታ ስለሌለው ወደ ሌላኛውና ንቁ ወዳልሆነው የአዕምሮ ክፍል /the unconscious mind/ መረጃዎችን በሙሉ ያስተላልፋሉ፡፡
ንቁ ያልሆነው የአዕምሯችን ክፍል የተሰጠውን መረጃ እውነት አድርጎ የሚቀበልና ኢ-ምክንያታዊ ስለሆነ ንቁ ከሆነው የአዕምሯችን ክፍል የመጣውን መረጃ በሙሉ ያጠራቅማል፡፡
ከአካባቢያችን ጋር መስተጋብር የሚፈጥረው ንቁ የሆነው የአዕምሯችን ክፍል ስለሆነና በአካባቢያችንም ብዙ ነገሮች ስላሉ ይህ የአዕምሯችን ክፍል የተወሰኑት ላይ ትኩረት በማድረግ ወደ ውስጠኛውና ንቁ ወዳልሆነው የአዕምሯችን ክፍል ይልከዋል፡፡
ወደ ዓይን ፍቅር ስንመጣ አንድ ግለሰብ አንድ የሆነ ሰውን በሚያይበትና ልዩ ሆኖ/ና በሚታይበት ወይም በምትታይበት ጊዜ ንቁ የሆነው የአዕምሯችን ክፍል ትኩረት ሰጥቶ መከታተል ይጀምራል፡፡
ልዩነቱንም ያደንቃል /በተደጋጋሚ መረጃውን ያውጠነጥናል/፡፡
ይህ በሚሆንበት ሰዓት አንድን መረጃ ንቁ ወደሆነው የአዕምሯችን ክፍል በተደጋጋሚ ይልካል፡፡
በዚህ ጊዜ ንቁ ያልሆነው የአዕምሯችን ክፍል በተደጋጋሚ የተሰጠውን መረጃ በመቀበል የታየውን /የታየችውን/ ሰው ምስል ቀርፆ ይይዛል፡፡
በማስታወሻ የአዕምሯችን ማዕከልም ውስጥ ይህ ስዕል በሚገባ ይሳላል፡፡
በተጨማሪም ንቁ የሆነው የአዕምሮ ክፍል ስለፍቅር ወይም ስለወሲብ ወይም በጠቅላላው ስለተቃራኒ ፆታ በሚያስብበት ሰዓት የሚያስበው/የሚያገኘው መረጃ ያን ስዕል ይሆናል፡፡
በመሆኑ ፍቅርን ሲያስብ የሚያስበው በአዕምሮው የሳላትን/የሳለውን ሰው ብቻ ይሆናል፡፡
ታዲያማ ይህ ሰው የዓይን ፍቅር ያዘው ማለት ነው፡፡
➢ በክፍል ሁለት አንዳንድ ገጠመኞች እና መፍትሄዎቹን ይዘን እንቀርባለን!!:
አሪፍ አሪፍ ምክሮችን እና ስለ ፍቅር ምንነት በትኩሱ ለማግኘት ፔጁን
🙏 🙏
በቴሌግራም ተቀላቀሉን
💖 💘
💖 💘
💖 💘