እቅበተ ተዋሕዶ

እቅበተ ተዋሕዶ ነገረ ቤተ ክርስቲያንና ኦርቶዶክሳዊ ዕይታዎች ይቀርቡበታል።

18/09/2026

በነገራችን ላይ ለሴቶች የምንዝር ጌጥን ያስተማረው ሰይጣን አዛዝኤል ይባላል። መጽ ሄኖ፣ 2፥4 ግቡና አንብቡት ።
ምድረ ውሉደ አዛዝኤል። ቤ/ያንን የማታውቃት ምድረ መንጋ ሁሉ ከፈለግህ ፈንዳ። ማፈሪያዎች።

18/09/2026

የከተማ ኩብኩባዎችና የቆላ ቄሶች፣ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን በካልቾ ብለው ለአልቦ ድንግልናው ጎረምሳ ሁሉ ምሥጢረ ተክሊል እንደሚፈጽሙ አስረግጨ እነግርሃለው። ብር ካለህ ድንግልናህንም በኮታ ይመልሱልሃል።🤣

18/09/2026

አጠገብህ ያለውን ሰው ነካ አድርገውና "መንፈሰ ትውዝፍት" የቤተ ክርስቲያን ጠላት፣ የአጋንንት ግብራቸው፣ የኦርቶዶክሳዊ ሰው የሥነ ምግባር ጸር ነው በለው።

18/09/2026

ሰላም ለሙጋቤ ፓፕስቲክ💋ወልፒስቲከ፣
አግርር ለፍትዎትከ ወጾረ ምንዝር እም መንጋከ፣
ግበር ዘንተ፣ ከመ አዋጅከ ወበከመ ነቢብከ።😂

18/09/2026

የእውቀት አክፍሎተኛ መንጋው መዝገበ ቃላቶች የሞሉት "ቀንታችሁ ነው፣ ምቀኞች....ፓራራም፣ ፓፓ " የሚል አሸንክታብ ነው።
ወይኔ በላቸው😎ትውልዱ ይህን ያህል መምከኑን በትክክል ያወቅነው አሁን ነው።

18/09/2026

መንጋው ግን ምን በልቶ ግን እንዲህ የደነቆረው? ለካ የሳጋቱራ እንጀራ ልቡንም አእምሮውንም አደንዞታል። ስለ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር እና ቀኖና ቤተ ክርስቲያን እየሞገትን፣የባልቴት ወሬ ይነዛል። ወዮ 😂

 #ጾረ ዝሙት በቤተ መቅደስ እየተዋወቀ ነው።🙈***በተከበረው ቤተ መቅደስ ጾረ ዝሙትን ማስተዋወቅ ይባላል ? እንዴትስ ተው የሚል ተፈሪ አባት ተከባሪ ሊቅ ይጠፋል ?  እውነተኛ ምእመን ይህን...
18/09/2026

#ጾረ ዝሙት በቤተ መቅደስ እየተዋወቀ ነው።🙈
***
በተከበረው ቤተ መቅደስ ጾረ ዝሙትን ማስተዋወቅ ይባላል ? እንዴትስ ተው የሚል ተፈሪ አባት ተከባሪ ሊቅ ይጠፋል ? እውነተኛ ምእመን ይህን አሕዛባዊ ሥርዓት አያለማምድም እንኳንስ ራሱን መ/ር ነኝ ብሎ የሾመ ። ያሳፍራል በጣም። ቤተ መቅደሱን የፊልም መቅረጫ ያደረጉ አካላት ትውልዱ እንዲህ መረን እንዲለቅ አድርገዋልና ዋጋቸውን ያገኛሉ።

#ቤተ መቅደስ ምእመናን ከእግዚአብሔር ጋር የሚገናኙበት ፣ለድኅነተ ዓለም ምሥጢራት የሚፈሙበት የጸጋ ግምጃ ቤት እንጂ፣ ሁሉት ጎረምሶች እየገቡ #ፍትዎተ ሥጋን በዓይን የሚያሳዩበት አይደለም ። ነውር የነውር ጥግ ነው እየተፈጸመ ያለው።

መከራችን ያነሰን ይመስልን፣ እናውቃለን የሚሉ ተረፈ አይሁድ፣ ቸርነቱ የጠብቃን እንጂ የፈጣሪን የቁጣ እሳት ሊያዘንቡብን እየተለማመዱ ነው። በቃችሁ ሊባሉ ይገባል። ቤተ መቅደስ ክብር ነው።
በቃችሁ አቁሙ።
መከራ ሰልችቶናል።

18/09/2026

ለአጽዕኖተ ነገር ደግመን እንናገር፣ ስለ ሮዳስ የቤተ ክርስቲያን የመከራ ችንካርነት፡- በማስረጃ ያቀረብነው ጽሑፍ፣ተደራሲያኑ የእውቀት አክፍሎተኛው መንጋ ሳይሆን አዋቂዎች ናቸው። እንከባበር ጎበዝ !

🚯ሮዳስ እንደስሙ፣  #የቤተ ክርስቲያን የመከራ  #ችንካር ሁኖ ተከስቷል። 🥺[ይህን የጻፍነው ለእውቀት አክፍሎተኛው መንጋ፣ ሳይሆን ለአዋቂዎች ነው። ] ----***---ሮዳስ ጌታችን መድኃኒታ...
18/09/2026

🚯ሮዳስ እንደስሙ፣ #የቤተ ክርስቲያን የመከራ #ችንካር ሁኖ ተከስቷል። 🥺
[ይህን የጻፍነው ለእውቀት አክፍሎተኛው መንጋ፣ ሳይሆን ለአዋቂዎች ነው። ]
----***---
ሮዳስ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ ዓርብ ከተቸነከረባቸው ከ5ቱ ቅንዋተ መስቀል (ችንካሮች) መከካል አንዱ ነው። ሮዳስ የሚባለው ችንካር ጌታችን መድኃታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን በሥልጣኑ ለዘላለሙ ያጠፋው ዘንድ በፈቃዱ ሞትን ሲቀበል፣ ወገቡን አጣብቆ እንዲይዘው አይሁድ ከመስቀሉ ጋር የተቸነከሩበት ችንካር ስም ነው።

የዛሬው ሮዳስም #ከቤተ ክርስቲያንን #ችንካሮች መካከል መሆኑን በግልጽ አሳይቷል። ይህ ሰው በሥነ ከዋክብት እና የሕዋ ሳይንስ ምርምር ሰበብ ብዙ ተፋልሶ ያለባቸው ሐሰተኛ ት/ቶችን ያስተላልፋል። ይህም ብቻ ሳይሆን አስቀድመው በሊቃውንት የታወቁ የተሰፈሩ ት/ቶችን ሳይቀር በመቀሸብ የራሱ አዲስ ግኝት አስመስሎ ሲያወራ ትንሽ እንኳን ሐፍረት የለውም። ይህን ደጋግሞ አሳይቷል። ተከታዩ መንጋ ግን #የእውቀት #አክፍሎተኛ ስለሆነ ምንም ሊል አይችልም። መንጋው አደገኛ ድንዛዜ ውስጥ ስለሚገኝ በሌለው እውቀት ይሞግት ዘንድም ጥንተ ተፈጥሮው አይፈቅድለተም።

ልጁ ይህን የመንጋውን ጥልቅ ድንዛዜ ስለሚያውቅ በተገቢው ሁኔታ ያለው ክፍተት ተጠቅሞ እንቶፈንቶ እየጻፈ ቀፍሎበታል። ከዚህም ችግር የለብንም። "ወደሽ ከተደፋሽ ቢረግጡሽ አይክፋሽ" ነውና መንጋውን መቀፈል መብቱ ነው።

ዋናው ነገር አብዝተን ልጁን የምንቃወመው ግን አሁን ጋብቻውን ሰበብ አድርጎ ከፍተኛ የሥርዓተ ቤ/ያን ጥሰት እና ያልተገባ ኢ ኦርቶዶክሳዊ ልምምድን እያስገባ ነው። ይህን ባዕድ ልምምድ ወደ ትውልዱ ለማስረጽ የሄደበትን ርቀት የከፋ ነው። ከዚያም ሲያልፍ በቤ/ያን መከራ ጊዜ የማታገኘው መስሎ አድኃሪ የመለካዊነት ብቃት ላይ የደረሰ አደገኛ ሰው መሆኑ ግን ሊታወቅ ይገባል።

በዝርዝር ላብራራ፡-
***
1. ልጁ #ጾረ ዝሙት በቤተ መቅደስ እያስተዋወቀ ነው።🙈
በተከበረው ቤተ መቅደስ ጾረ ዝሙትን ማስተዋወቅ ምን ይባላል ? እንዴትስ ተው የሚል ተፈሪ አባት ተከባሪ ሊቅ ይጠፋል ? እውነተኛ ምእመን ይህን አሕዛባዊ ሥርዓት አያለማምድም እንኳንስ ራሱን መ/ር ነኝ ብሎ የሾመ ። ያሳፍራል በጣም። ቤተ መቅደሱን የፊልም መቅረጫ ያደረጉ አካላት ትውልዱ እንዲህ መረን እንዲለቅ አድርገዋልና ዋጋቸውን ያገኛሉ።

#ቤተ መቅደስ ምእመናን ከእግዚአብሔር ጋር የሚገናኙበት ፣ ለድኅነተ ዓለም ምሥጢራት የሚፈሙበት የጸጋ ግምጃ ቤት እንጂ፣ ሁሉት ጎረምሶች እየገቡ #ፍትዎተ ሥጋን በዓይን የሚያሳዩበት አይደለም ። ነውር የነውር ጥግ ነው እየተፈጸመ ያለው።

መከራችን ያነሰን ይመስልን፣ እናውቃለን የሚሉ ተረፈ አይሁድ፣ ቸርነቱ ጠብቃን እንጂ የፈጣሪን የቁጣ እሳት ሊያዘንቡብን እየተለማመዱ ነው። በቃችሁ ሊባሉ ይገባል። ቤተ መቅደስ ክብር ነው።

ይች ልጅ ተምራ ቢሆን ኖሮ #በየትኛው ቀኖና እና ኦርቶዶክሳዊ ሥርዓት ነው ሴት ልጅ ቤተ መቅደስ ገብታ ትርጓሜው ቀርቶ ቁጥር እንኳን የምትቀጽለው ? ለመንጋው የሚሰጠው ትርጉምስ ምንድን ነው ? መ/ር ነኝ ከሚል አንድ ሰውስ ይህን ማድረግ ይገባ ነበር ወይ ?

3. #ራስን ማምለክ የቀደመው ተርእዮ ‼️
አንድ ሰው ግላዊ ሕይዎቱን ሲከውን ለሌሎች ፈተና ሊሆን በማይችል መንገድ መፈጸም አለበት። ይህ ልጅ ግን ሁሉን እወቁልኝ ብሎ ዐደባባይ ማስጣቱ ለራሱም ሆነ ለባለቤቱ ትርጉሙ ምንድን ነው ? በአጭሩ ልጁ ቀድሞ የተጣባው የጸና የተርዕዮ(እታይ ባይነት) በሽታው ሲጸናበት ይህ አድርጓል። ራሱን ላይ የከፋ ፈተና ጋብዟል። መውጫውን ይስጠው ።

4. #የምንዝር ጌጥ የቀደማት የትዳር አጋር ‼️
እጮኛየ ናት ብሎ በሚዲያ ያስተዋወቃት ልጅ በምንዝር ጌጥ ያበደች፣ በትውፍዝት አሽንክታብ የቀለጠች ፍጹም ዓለማዊት ሴት እንጂ እንደተባለው በቤ/ያን ሥርዓት ያደረገች በጭራሽ አትመስልም። መላ ሰውነቷን ለተመለከተ ሰውነቷ ላይ ያልሰፈረ የቀረ የፋብሪካ ምርት ያለ አያስብልም። ምን መልዕክት ነው ማስተላለፍ የተፈለገው ? የምንዝር ጌጥን እውቅና ማሰጠት ? ወይስ የቤ/ያን መ/ራን ፣ካህናት አገልጋዮች ሚስቶች በምንዝር ጌጥ ያበዱ ቢሆኑ ችግር የለውም ማስባል ? የልጅቷ አጠቃላይ የትውዝፍት አለባበስና ምንዝር ጌጥ ምኑስ ያንጻልና ነው ማስተዋወቅ የተፈለገው ?

5. #የተደበቀው ስውር መለካዊነቱስ ? ‼️
ይህ ልጅ በቤተ ክርስቲያን መከራ ወቅት፡- አብያተ ክርስቲያናት ሲነዱ፣ ምእመናን በቤተ መቅደሱ ሲቃጠሉ፣ ካህናቱ ሲሰየፉ ትንፍሽ ሲል አትሰማው። ይህንን ስውር መለካዊነቱን ብዙ ሰው አይረዳውም። ካቶሎካዊው ሄኖክ ኃይሌ እና ሮዳስን.... የመሰሉ የውስጥ እሾሆች ዋና ዓላማቸው ቤተ ክርስቲያንን መኖሪያ ማድረግ እንጂ ለቤተ ክርስቲያን መኖር አይደለም። ሲበዛ መለካዊ ነው። ይህ ሰው ከሰርጉ ዜና ቅንጣቷን ታክል እንኳን የምእመናን እልቂት አያሳስበውም። የሚበላባት ቤ/ያን በዓላዊያን ስትበላ ትዝ አትለውም። ይህን ጉዳይ ሌላ ጊዜ በዝርዝር አሳያችኋለው።

🙏ማሳረጊያ‼️
1. ከላይ በጠቀስኳናቸው መሠረታዊ ችግሮች ምክንያት ሮዳስ የዛሬዋ #ቤተ ክርስቲያን #የመከራ ችንካር ሁኖ ተከስቷል።
{ ቤተ ክርስቲያን የምትሻው በአስተምህሮም በኑሮውም ቅድስናዋን የሚገልጥላት፣ ቀኖናዋን የሚያስጠብቅላት፣ ሥርዓቷን የሚያሰምርላት እንጂ በአገልጋይነት ስም ተጠግቶ ጎኗን የሚወጋት ችንካር አትፈልግም። }

2. #በዚህ ደረጃ የምንሞግተው ሰውን ከመጥላት ፣ወይም ጅል መንጋዎች እንደሚሉት "ምቀኞች ሆነን ሳይሆን" ከቤ/ያን የሚበልጥብን አንድም አካል ሰለሌለ ነው። ሰዎች ከቤ/ያን በላይ ይሆኑ ዘንድ አስተምህሮ የለንም። ያስተማረውን መኖር የማይችልን የመሰለ የቤ/ያን ጠላት የለም። መኖር ባይችልም እንኳን በዐደባባይ ለምእመናን ፈተና ሆኖ ሲከስት ግን ልንታገሰው ርህራሄ የለንም።

3. ከላይ #ላነሳናቸው መሠረታዊ የሙግት ጭብጦች መልስ ያለውና የልጁን ስህተት አለመሆን እሞግታለው የሚል ካለ በጨዋ ደንብ መልስ ይስጥበት ። መከራከር ይችላል። ካልሆነ ዝም ማለትም ያስከብራል እንጂ በማያውቁት በመንጋነት ብቻ መዘላበድ አያስፈልም።
[ በተረፈ መልካም ትዳር እንዲሆንለት ሞኞታችን ነው ]
አበቃው 👀
እቅበተ ተዋሕዶ

15/09/2026

ደጉን ምእመን ጭፍን መንጋ ያረገው የተሐድሶ መንፈስ ነው። በጋሻውን ተከትሎ ዘጭ እንቦጭ ሲል የኖረው፣ ዛሬም በዚያው መንገድ ስሁታኑን ተከትሎ እየነጎደ ነው። ርቱዕ ት/ት ስንነግረውም ትችት ይመስለዋል።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when እቅበተ ተዋሕዶ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share