11/05/2026
Mayor's Legacy Goal
በብዙ ልፋት ውስጥ ጥቃቅን ጉድለቶች ቢኖሩም በርካታ መልካም ውጤቶች ግን እየተመዘገቡ ነው። ዋናው እኔ/አንቺ/አንተ በጎ አስተዋጽኦ ይኑረን፤ አመስጋኝ እንሁን። ያኔ የጎደለውን እንሞላለን።
11/05/2026
Mayor's Legacy Goal
11/05/2026
የለውጥ ዓመታት ትሩፋቶች በአዲስ አበባ
(ማንንም ያልዘነጋ የልማት ጉዞ)
*************************
የአዲስ አበባ ልማት ሁለንተናዊ ነው ስንል በህንጻዎች ብዛት፣ በመሰረተ ልማት ዝርጋታ ሽፋን፣ በከተማ ውበት እና ሌሎች አካላዊ ለውጦች ላይ ብቻ የተንጠለጠለ አይደለም ማለታችን ነው። እነዚህ ልማቶችም ቢሆኑ የመጡት ከተማዋን ለነዋሪዎቿ ለኑሮ ምቹ፣ ለእይታ ማራኪ፣ ዓለማቀፍ ተወዳዳሪና ዘመናዊ ለማድረግ ነው።
ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ የልማቱ ተጠቃሚነት ላይ በጾታ፣ በማንነት፣ በሐይማኖት፣ በኢኮኖሚ ደረጃ፣ ወዘተ ተለይቶ የሚዘነጋ እንዳይኖር ህግና ስርዓቱ በጥብቅ ዲስፕሊን እየተተገበረ ይገኛል።
የከተማዋ ልማት ሙሉ በሙሉ ለሰው የታለመ በመሆኑ ሰው ተኮር ልማት እንለዋለን። በዚህ ውስጥ ታዲያ በተለያየ ምክንያት ከተጠቃሚነት ሊጎድሉ ለሚችሉት የተለያዩ ኢኒሸቲቮች እየተቀረጹ ተጠቃሚ እንዲሆኑና ወደ ኋላ እንዳይቀሩ እየተደረገ ይገኛል።
አንዱ ማሳያ ጎዳና ለወደቁ፣ በወሲብ ንግድ ለተሳተፉና ለከፍተኛ ችግር ለተጋለጡ ሴቶች የተነደፈው የተጠቃሚነት ስትራቴጂ ነው። ራሱን የቻለ እነዚህ ሴቶች ካሉበት የህይወት እክል የሚያገግሙበትና በክህሎት ዳብረው ደግሞ ለነገያቸው በልበ ሙሉነት የሚቆሙበትን አቅም የሚያገኙበት ተቋም ተመስርቷል። የተቋሙም ስራ ምን ያህል ለከፋ ችግር የተጋለጡ ሴት እህቶቻችንን ከልማቱ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ማሳያ ነው።
ይህ ሴቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰሩ ካሉት ስራዎች አንዱ እንጂ በርካታ ኢኒሸቲቮችን ማንሳት ይቻላል።
በመሆኑም ሴቶችም ለተጠቃሚነታቸው እየሰራ ላለ ፓርቲና አመራር በነቂስ አደባባይ ወጥተው ድጋፋቸውን መግለጻቸው ባለውለታን ያልዘነጋ እርምጃ ሆኗል። የሁላችንም ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
09/05/2026
የለውጥ ዓመታት ትሩፋቶች ለአዲስ አበባ
(ያልተቋረጠ የለውጥና የስኬት ጉዞ)
*****************************
በሀገራችን በመሪዎች ወቅት ጠብቆ የማባበያ ቃል ለህዝቡ መግባትና በልማት ስም የመሰረት ድንጋይ ማኖር የተለመደ ነበር። የተፈለገው ወቅት ሲያልፍ ቃልም ሆነ የተቀመጠው የመሰረት ድንጋይ ይረሳል።
በሌላ በኩል ለልማት ዓላማ ለማዋል በማቀድ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ ለመሰብሰብ የነበረው ቁርጠኝነት አናሳ በመሆኑ የነበሩ ውስን ልማቶችም የሌሎችን እጅ ማየት ላይ የተንጠለጠሉ ናቸው።
ባለፉት ጥቂት ዓመታት ግን ይህን አዙሪት የሚቀይር እይታና ትግበራ እውን በመሆኑ በማያቋርጥ የለውጥና የስኬት መንገድ ላይ መገኘት ተችሏል።
ለስኬቱ አንዱ ምክንያት በአመለካከትም ሆነ በተግባር ከጥገኝነት ተላቅቆ በራስ አቅምና ሀብት ላይ እምነት ማሳደር መቻሉ ነው። ሌላው ጉዳይ ደግሞ ያለን ሀብት አሟጦ ለልማትና ለህዝብ ጥቅም በሚሆን መልኩ መምራት መቻል ነው።
በርግጥ ለውጡና ስኬቱ ያለ ተግዳሮት የተረጋገጠ ሳይሆን ጥቂት ባለራዕይ መሪዎች ባሳዩት ጥበብና ቁርጠኝነት ፈተናዎችን ተቋቁሞ የተረጋገጠ ነው።
ዛሬ በአዲስ አበባ ፕሮጀክቶችን አጠናቅቆ ለአገልግሎት ማብቃት የየዕለት ተግባር ሆኗል። ዛሬ አንድ ፕሮጀክት ለአገልግሎት ክፍት ሲሆን ነገ ደግሞ የትኛው ነው? ብሎ መጠበቅ የተለመደ ሆኗል። ቀንና ሌሊት ሰርተው ቃላቸውን የሚጠብቁ መሪዎቻችንን በጽናት እንደግፋለን።
08/05/2026
07/05/2026
የለውጥ ዓመታት ትሩፋቶች በአዲስ አበባ
(በተገኘ እድል ሁሉ ለሰው እረፍትና ደስታ መኖር!!)
****************************************
በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የታየው ሰው ተኮር ለውጥ፡-
- ህጻናት ከተዘጉ ቤቶች ወጥተው ባማሩ ቦታዎችና ተቋማት እየተጫወቱ እንዲማሩ፤ በዚህም ብሩህ የእድገት ጅማሮ እንዲኖራቸው
- ታዳጊዎችና ወጣቶች በየትምህርት ቤቱ የምግብና ቁሳቁስ ድጋፍ እንዲያገኙ፤ በዚህም ትምህርታቸው ላይ አተኩረው መልካም ዜጋ እንዲሆኑ
- ወጣት ሴቶች ከጎዳና እና ከወሲብ ንግድ እንዲወጡ፤ በዚህም ከተበላሸ ህይወት ተላቅቀው ራሳቸውን እንዲችሉ
- እናቶች ከጉስቁልና ወጥተው በተመቻቸ ሁኔታ ሥራ እንዲሰሩ፤ በዚህም ለራሳቸውና ለቤታቸው ጌጥ እንዲሆኑ
- ምግብ ማግኘት የሚቸገሩ አረጋዊያን የምገባ አገልግሎት እንዲያገኙ፤ በዚህም በኋለኛው እድሜያቸው ደስ እንዲላቸው
- አቅመ ደካሞችና የሀገር ባለውለታዎች ዘመናዊ መኖሪያ ቤት እንዲያገኙ፤ በዚህም የተረሱት እንዲታወሱ በማድረግ
የብዙዎች ሰቆቃ አብቅቷል፣ የብዙዎች እንባ ታብሷል፣ የብዙዎች ተስፋ ለምልሟል፣ የብዙዎች ህይወት ተለውጧል.....
ይህንን ሰብዓዊ ለውጥ መሪ በመሆን ብቻ ማሳካት አይቻልም።
ይህንን ለውጥ ማምጣት የሚቻለው ያገኙትን የመሪነት እድል ለሰዎች እረፍት እና ደስታ ለመኖር በመወሰን ነው!!
06/05/2026
የለውጥ ዓመታት ትሩፋቶች በአዲስ አበባ
(ከውበት ባሻገር)
**************
በከተማ ልማት ትኩረት ከሚሹና ከሚሰራባቸው ጉዳዮች አንዱ ከተማው በምሽት በቂ ብርሃን እንዲያገኝ ማድረግ ነው። ይህ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው። በዋናነት ነዋሪዎች ደህንነታቸው ተጠብቆ ያለገደብ ይንቀሳቀሱ ዘንድ ይረዳል። የከተማ የንግድ እንቅስቃሴም በቀን ሳይገደብ በምሽትም ጭምር መከናወን እንዲችል በቂ ብርሃን ማግኘት ወሳኝ ነው።
ከተሞቻችን ውብ እንዲሆኑም የተለያየ ቅርጽና ቀለም ያላቸው መብራቶች በእጅጉ ያስፈልጉናል።
ያው እኛ ጋር ሲሆን ቃላት እየመረጡ መቃወም የሚቀናቸው ስላሉ እንጂ ብዙ የዓለም ከተሞች አንዱ መገለጫ በቂ፣ ደማቅና ውብ መብራቶች ናቸው። የሌላ ሀገር ከተማ አምሮና ደምቆ ሲታይ ፕሮፋይላቸው ላይ የሚያስቀምጡ የራሳቸው ሲሆን ደግሞ የሚቃወሙ እና የሚተቹ የስነ-ልቦና ችግር ያለባቸው ሰዎች ያስገርማሉ።
በርግጥ አንድ ነገር ገብቶናል። ከውበት ባሻገር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው ደማቅና ውብ መብራት ለከተማችን ያስፈልገናል። መሪዎቻችንም ለጭፍን ተቋውሞ ቦታ የላቸውም ምክንያቱም ምን እየሰሩ እንዳሉ ጠንቅቀው የተረዱ ናቸው።
ልማቱ ይቀጥላል፣ የእኛም ድጋፍ ለመሪዎቻችን ተጠናክሮ ይቀጥላል።
05/05/2026
የለውጥ ዓመታት ትሩፋቶች በአዲስ አበባ
(ቃላቸውን የሚተገብሩትን እንምረጥ)
*****************************
የተናገሩትን የሚኖሩ፣ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ 24/7 በትጋት የሚሰሩ፣ በታማኝነት እጃቸውን ያነጹ፣ ህዝብን በእኩል የሚያዩ፣ ለትውልዱ አርዓያ የሆኑ መሪ ማግኘት ለህዝቡ በረከትና እድል ነው።
04/05/2026
የሀገር ግንባታ በሁሉም ዘርፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!