BC Enlightenment

BC Enlightenment

Share

Academic BC ACADEMIC

19/05/2026

ይህ በ 11/09/2018 ዓም በኦሮሚያ ክልል በፍቸ እና ገብረ ጉራቻ መሀከል አሊደሮ ከተማ ወጣ ብሎ የታጠቁ ወንበዴወች ተኩስ ከፍተው ጎማ መስታውት መተው በማስቆም ታሳፋሪወችን አፍነው ወስደዋል የሚል መልዕክት ደርሶናል።

ሌላው ተሳቢ ጎማ መስታውቱ በጥይት ተመቶ ሾፌሩ ተጎድቷል የሚል መልዕክት አለ ይህ አውቶብስ ከፊት በጥይት እንዴት እንደተመታ ይታያል ከመስትውቱ ባለፈ ዙሪያውን መመታቱን ገልፀውልናል።

ወደ ህዝብ ጥይትን የሚተኩሱ በተደጋጋሚ እገታ ግድያን የሚፈፅሙ ሙሉ ተሳፋሪን አፍነው ስልክ ተደዋውለው ተደራድረው የሚኖሩ ወንበዴወችን ከመስመሩ ማፅዳት አነፍንፎ ይዞ በህግ መቅጣት ባለመቻሉ ያሻቸውን እንዲያደርጉ እድል ፈጥሯል።

ይህ የመንገድ ክፍል የዘራፊ መፈንጫ መሆኑ ይታወቃል 43 ኪሎ ሜትር መንገድ መቆጣጠር አለመቻል ሾፌር ተሳፋሪ እንዲታፈን እንዲገደል እያደረገ ይገኛል መንገዱ በአገልግሎቱ እና በችግሩ ግዝፈት ልክ ጥበቃ እና ትኩረት ሊደረግለት ይገባል።

ፍትህ

17/05/2026

''ከአውሮፓ፣ ከአሜሪካ እየመጡ በኢትዮጵያ እድገት እና ለውጥ እየተደመሙ ነው'' አዲስ አበባ ብቻ ኢትዮጵያ ናትን?

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በተለያዩ ጊዜያት በሚያደርጓቸው ንግግሮች፤ ዓለም በኢትዮጵያ እድገት እና ለውጥ ቢደመምም በርካታ ኢትዮጵያውያን ግን የተሰራውን ስራ በቅጡ ለመገንዘብ እና ለማድነቅ እንደሚያዳግታቸው ሲናገሩ ተደምጠዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትላንት ቅዳሜ ግንቦት 8፤ 2018 በተካሄደ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ ላይ ባደረጉት ንግግርም ይህንኑ አቋማቸውን ደግመውታል።

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ንግግሩን ያደረጉት በአዲስ አበባ ከተማ የተገነባው የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ ምርቃት መርሃ ግብር ላይ እንዳነሱት ከውጭ ሀገራት የሚመጡ ሰዎችን ያስደሰተ ያሉትን የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ዕድገት አንስተዋል።

ኢትዮጵያ 10.2 ፐርሰንት የምታድግ ብቸኛ አገር ናት ያሉ ሲሆን በድፍን አፍሪካ 10.2 ፐርሰንት እድገት የሚያድግ አንድም ሃገር የለም ብለዋል።

አዲስ አበባ ብቻ ኢትዮጵያ ናትን?

ሀሳብዎን ያካፍሉን?

የአርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን አልበም መውጣትን ተከትሎ በተያዙ ግለሰቦች ዙርያ የሚያጠነጥን ዘጋቢ ፊልም እየተሰራ መሆኑ ታወቀ 29/04/2026

የአርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን አልበም መውጣትን ተከትሎ በተያዙ ግለሰቦች ዙርያ የሚያጠነጥን ዘጋቢ ፊልም እየተሰራ መሆኑ ታወቀ (መሠረት ሚድያ)- ከቀናት በፊት ለህዝብ ይፋ የሆነውን የአርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን አልበምን ተከትሎ ሙዚቃውን ሲያዳምጡ ተገኙ የተባሉ ከመቶ በላይ ግለሰቦች እንዲሁም ከአርቲስቱ ጋር ይ.....

29/04/2026

ቤይሩት፤ ሳውድ አረቢያ ውስጥ የሞት ቅጣት የሚጠባበቁ 65 ኢትዮጵያውያን

I ሳውድ አረቢያ ውስጥ ቢያንስ 65 ኢትዮጵያውያን ከአደንዛዥ ዕጽ ጋር በተገናኘ ወንጀል የሞት ቅጣት እንደሚያሰጋቸው ዓለም አቀፉ የሰብአዊ መብቶች ተቆርቋሪ ተቋም ሂውማን ራይትስ ዎች ዐሳወቀ። የሳዑዲ ባለሥልጣናት እስከ ባለፈው ማክሰኞ (ሚያዝያ 13 ቀን፣ 2018 ዓ.ም) ድረስ ሌሎች ሦስት ሰዎችን በስቅላት መቅጣታቸውንም ዛሬ የወጣው ተቋሙ መግለጫ ያመለክታል።

በሂውማን ራይትስ ዎች የስደተኞች እና የፍልሰተኞች መብት ከፍተኛ ተመራማሪ ናዲያ ሐርድማን፦ «ሳውድ አረቢያ በመሠረታዊ የፍርድ ሂደት የመታደም መብት በመንፈግ የኃይል ጥቃት ላልቀላቀለ ወንጀል በሞት ለመቅጣት መዘጋጀቷ ለፍልሰተኞች መብት እና ሕይወት ክብር ያለመስጠትን ያንጸባርቃል» ብለዋል።
ባለሙያዋ የሳውድ አረቢያ አጋሮች «ጊዜው ከማለፉ በፊት» በአፋጣኝ ጣልቃ እንዲገቡም ጠይቀዋል። ሂውማን ራይትስ ዎች ሳውድ አረቢያ አሲር ግዛት በሚገኘው ካሚስ ሙሻይት እስር ቤት ስለሚገኙት ሦስት ታሳሪዎች መረጃ ያላቸውን ሦስት ሰዎች ስለጉዳዩ መጠየቁን አመልክቷል።

ሦስቱም እስረኞች በቅርቡ ሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ጦርነት በነበረበት ወቅት የተሰደዱ መሆናቸውን ገልጿል። የሰብአዊ መብት ይዞታይ አደገኛ በነበረበት በዚያን ወቅት በአስቸጋሪው የስደት መስመር በየመን በኩል ወደ ሳውዲ የገቡ መሆናቸውንም አመልክቷል። ገንዘብ ለማግኘትም ከየመን ወደ ሳውዲ ጫት መውሰዳቻውንም ከመረጃ ሰጪዎቹ ተረድቷል።

ሆኖም ሳውዲ ውስጥ ጫት በወንጀል እንደሚያስጠይቅ እንደማያውቁም ጠቅሷል። ከታሠሩ አንስቶ በአግባቡ ፍርድ ቤት እንዳልቀረቡ፤ በቀረቡበት አጋጣሚም አስተርጓሚ እንዳልነበራቸውና የተላለፈባቸውን ፍርድ ምንነት እንዳልተረዱም ዘርዝሯል።

ሆኖም በፀጥታ ኃይሎች መደብደባቸውና ምንነቱን ያልተረዱት ሰነድ ላይ እንዲፈረሙ መገደዳቸውንም አስታውቋል። ሂውማን ራይትስ ዎች የሚመለከታቸው መንግሥታት ሳውድ አረቢያ የሞት ቅጣቱን እንድታነሳ ግፊት እንዲያደርጉም አሳስቧል።

ዘገባው የዶይቼ ቬለ ነው

24/04/2026
11/04/2026

እንኳን ለትንሣኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ

25/02/2026

Once upon a time, in Delhi, there was a big problem—cobras. These snakes were dangerous, and many people were afraid to walk the streets. The city officials, wanting to keep everyone safe, came up with a plan: they announced that anyone who brought a dead cobra would be rewarded with money.
At first, people were happy. They went out hunting cobras, catching many, and collecting the rewards. The city seemed safer, and everyone was pleased.
But soon, something strange happened. Some clever people saw an opportunity. They started breeding cobras in secret, hoping to catch them later and get the reward. As the days went by, more and more cobras appeared in the city, not fewer.
One day, the officials realized what was happening. The program had backfired! Instead of reducing the snake problem, it had made it worse. The cobras multiplied, and the city became even more dangerous.
Seeing this, the officials decided to stop the reward program. But by then, the cobra breeders had released their snakes into the wild, and the city was filled with even more dangerous snakes.
The story teaches us an important lesson: sometimes, even good intentions can lead to unexpected problems if we're not careful. It's always important to think ahead and consider what might happen before making big decisions.

05/01/2026

ሰበር የእ~ገታ ዜና ‼️
በዚህ ጉዳይ ፋኖ እጁ የለበትም ‼️
ታህሳስ 27/2018 ዓ.ም ከአዲስ አበባ መነሻቸውን አድርገው ወደ ደብረ ማርቆስ ከተማ በfm bus ሲሔዱ የነበሩ 40 ተሳፋሪዎች በኦሮሚያ ክልል አሊዶሮ ላይ መታ~ገታቸ`ው ተረጋግጧል እስከ አሁን 7 የደብረ ማርቆስ ከተማ ነዋሪዎች በስም ተለይተዋል።

በተሽከርካሪው ላይ የነበሩት መንገደኞች ፣ የደንበጫ ፣ አማኑኤል፣ደብረ ኤልያስና ጅጋ አካባቢ ተዎላጆች ለገና በዓል ወደ ቤተሰቦቻቸው እየሔዱ ባሉበት መታገታቸው አሁን የደረሰን መረጃ ያረጋግጣል።
Bahir Dar Wikileaks - BW

Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Category

Telephone

Website

Address


Addis Ababa