LDI

LDI

Share

Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from LDI, Addis Ababa.

Livestock Development Institute is an Institute established by The Council of Ministers Regulation No. 506/2014 to conduct research, capacity building and counseling services on animal genetic improvement and product processing activities.

Photos from LDI's post 26/08/2025

The Livestock Development Institute (LDI) held a productive discussion today with representatives from SNV, a Dutch development organization. The meeting's primary focus was to establish a clear path forward for a new partnership. The two parties are collaborating on an initiative that will focus on capacity building within the livestock sector. This partnership aims to leverage SNV's extensive experience in sustainable development to strengthen the LDI's programs and expertise. The discussion concluded with a mutual agreement on the next steps to officially begin the partnership.

26/06/2025

የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ማኔጀመንት ከሥራ ዘርፎች፣ ከመሪ ሥራ አስፈጻሚዎች እና ሥራ አስፈጻሚዎች ጋር በመሆን የ2017 የዕቅድ ክንውን አፈጻጸም ግምገማ ሪፖርት ላይ ውይይት አካሄደ፡፡ በተጨማሪም በ2018 ጠቋሚ ዕቅድ ዙሪያ ተወያይቶ የ2018 ዕቅድን በማስቀመጥ ለትግበራው አቅጣጫ ተሰጥቷል፡፡

Photos from LDI's post 04/01/2025

የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ድጋፍ ለሚሹ 40 የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ነዋሪዎች ማዕድ አጋራ

ኢንስቲትዩቱ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 በተቋሙ ዙሪያ ለሚገኙና ድጋፍ ለሚሹ 40 ነዋሪዎች በ50 ሺ ብር ወጪ 4 ኩንታል ዱቄት ዛሬ ድጋፍ አድርጓል።

ድጋፉን ለወረዳው አፈጉባኤ መንግሥቱ መዳልቾ
ያስረከቡት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አሥራት ጤራ (ዶ/ር) እንደገሉፁት በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን አነሳሽነት የተጀመረውን ማህበራዊ ኃላፊነት ለመወጣት እየሰራ ነው ብለዋል።

ማህበራዊ ድጋፍ ኃላፊነቱን በክረምትና በጋ በጎ አድራጎት አጠናክሮ ከመቀጠል ባሻገር ከወረዳውና በከተማ አስተዳደሩ አርሶአደርና ግብርና ልማት ኮሚሽን ጋር በቅንጅት የሌማት ትሩፋቱን በሙያ እና በግብዓት ድጋፍ እያደረገ መሆኑንም ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።

እንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ካሁን በፊት ለሁለት ቤተሰቦች የመኖሪያ ቤት ከተሟላ የቤት ቁሳቁስ ጋር ከማስረከብ ጀምሮ በየዓመቱ በተለያዩ አውደ በዓላት ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን ዶ/ር አስራት አስታውሰዋል።

በመጨረሻም ዋና ዳይሬክተሩ ለክርስትና እምነት ተከታዮች የገና በዓል የሰለም፣ የፍቅርና የመተሳሰብ ይሆን ዘንድ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

Photos from LDI's post 31/12/2024

የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ለ56ኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን የአዳቃይ ቴክኒሽያኖች አስመረቀ!
==========================================
የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ከምግብ ሥራዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም ጋር በመተባበር ለ56ኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን 141 (ወ 126፣ ሴ 15) ከተለያዩ ክልሎች የተውጣጡ የእንስሳት አዳቃይ ቴክኒሽያኖችን ዛሬ ታህሳስ 22 ቀን 2017 ዓ.ም የተከበሩ እንግዶች፣ ለሥልጠናው ልዩ አስተዋጽዎና ድጋፍ ያደረጉ እና የኢንስቲትዩቱ ማኔጅመንት እና ሠራተኞች በተገኙበት በይፋ አስመርቋል፡፡

በግብርና ሚኒስቴር የእንስሳት ዘርፍ ሚኒስተር ዴኤታ የሆኑት ክቡር ዶክተር ፍቅሩ ረጋሳ(ፒኤችዲ) እና የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ዶክተር አስራት ጤራ(ፒኤችዲ) ተመራቂዎቹን እንኳን ደስ አላችሁ በማለት ለተመራቂዎቹ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ክቡር ዶክተር ፍቅሩ ረጋሳ(ፒኤችዲ) በምረቃው ሥነ ሥርዓት ላይ ባስተላለፉት መልዕክት በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን በተነደፈው የሌማት ትሩፋት ስኬት የእንስሳትን ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በግንባር ቀደምትነት ዝርያ ማሻሻል ወሳኝ ሥራ መሆኑን በመጥቀስ ይህን የእንስሳት ዝርያና ለማሻሻል ደግሞ የአዳቃይ ቴክኒሽያኖች ከፍተኛ ሚና የሚጫወቱ መሆኑን በመጥቀስ መንግስት ከፍተኛ ኃላፊን የጣለባቸው መሆኑን በመጥቀስ ተመራቂ ሠልጣኞች ወደመጡበት ተመልሰው ይህን ሀገራዊ ኃላፊነት በብቃት እና ጥራት እንዲወጡ የሥራ መመሪያ ሰጥተዋቸዋል፡፡

በመቀጠልም የክብር እንግዳው ክቡር ዶክተር ፍቅሩ ረጋሳ (ፒኤችዲ) አጭር የሥራ ጉብኝት አድርገው የዕለቱ ፕሮግራም ተጠቃሏል፡፡

እልኢ ታህሳስ 22 ቀን 2017 ዓ.ም

Photos from LDI's post 12/12/2024

‹‹እንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት በንብ እርባታ ቴክኖሎጂ ሞዴል የስልጠና ማዕከል እንዲሆን እንሰራለን›› አዉራሪስ ጌታቸዉ(ዶ/ር)

ታህሳስ 03/2017 ዓ.ም እ/ል/ኢ አዲስ አበባ

እንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ከ CRS (Catholic Relief Service) ዓለም አቀፍ የበጎ አድራጊ ድርጅት ዝርያን ለማሻሻል የእናት ንብ እርባታ እና የማር ምርት ጥራት(Queen rearing and Honey quality) በሚል ርዕስ ዙሪያ በዘርፉ ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት ዶ/ር ሮበርት ኦውን (Dr. Robert Owen) ተሰጥቷል፡፡ ሰልጣኞች ከእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ሁለቱንም ማዕከላት ጨምሮ፤ ከግብርና ሚኒስቴር፤ ከኢትዮጵያ ንብ ሀብት ማህበር፤ ከአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፤ አናቢዎች (ከአዲስ አበባ፤ ቢሾፍቱ፤ ሰበታ) እና ማር አቀነባባሪዎች መሳተፋቸው ታውቋል፡፡

CRS ዓለም አቀፍ ድርጅት (Farmers to Farmers Program) በእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በዘርፉ የሚያጋጥማቸውን የእዉቀትና ክህሎት ክፍተት በስልጠና በመሙላት እንዲሁም ችግር ፈቺ ምርምር እንዲሰራ፤ ለባለድርሻ አካላት ስልጠና እንዲሰጥ እና የቴክኒክ ድጋፍ እንዲያደርግ አስፈላጊዉን ድጋፍ ለመስጠት የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ (memorandum of understanding) ተፈራርመዋል፡፡

የተቋሙ የእንስሳት ምርትና መኖ ማቀነባበርና ጥራት ምርምር ዶ/ር አዉራሪስ ጌታቸዉ እንደገለፁት ተቋሙ ለሙከራ ያህል 10 የንብ መንጋ በዘመናዊ ቀፎ ጅማሮ መኖሩን ገልጸው በቀጣይ እስከ 30 የንብ ቀፎ ለማድረስ እና በሆለታ ማዕከልም ተጨማሪ የንብ እርባታ ጣቢያ እንደሚቋቋም ተናግረዋል፡፡

አክለውም ኢትዮጵያ ሀገራችን 7 ሚሊዮን የንብ ቀፎ ቢኖራት ከ90 በመቶ በላይ በባህላዊ ቀፎ የሚመረት በመሆኑ እና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ባለመሆኑ አጥጋቢ ምርት እያገኘች አይደለም ብለዋል፡፡ ዘርፉን የማዘመን ሥራ በሚፈለገው ደረጃ ባለመስራታችን ሀገሪቱ በዓመት 500,000 ቶን ማር የማምረት አቅም ቢኖራትም እያመረትን ያለነው ከ147,000 ቶን ማር ያልበለጠ ነው፡፡

Photos from LDI's post 11/12/2024

የእንስሳት ልማት እንስቲትዩት፤ሆለታ ማዕከል(ሆ/እ/ል/ማ) ከ 40.000-45.000 የድርቆሽ ሳር ቦንዳ ለማገኘት እየሰራ ይገኛል
በ2017 ዓ.ም ማዕከሉ ከ40-45 ሺህ የድርቆሽ ሳር ቦንዳ ለማገኘት አቅዶ እየሰራ እንደሚገኝ የማዕከሉ ስራ አስኪያጅ ሙሉጌታ ተስፋዬ ገልጸዋል።
ለሳሩ ማከማቻ የሚሆን ሃያ(20) ሃያ(20) ሽህ የሚይዙ ሁለት መጋዝኖች ተዘጋጅቷል።
ስራዉ በአጠቃላይ ከ 80 በላይ ዜጎች ግዜያዊ የስራ እድል መፍጠር እንደተቻለም አክለዋል፡፡
በ2016 ዓ.ም 58,409 የድርቆሽ ሳር ቦንዳ ተሰብስቦ እንደ ነበርም ጠቅሰው የዘንድሮ ምርት ግን የከብቶች ብዛት መጨመርን ተከትሎ ይመረት ከነበረዉ ምርት እንደቀነሰ ጠቅሷል።
የሳር አጨዳ እና መሰብሰቡ ስራ በአጠቃላይ ከ 80 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ግዜያዊ የስራ እድል መፍጠር ተችሏል፡፡
ማዕከሉ በተጨማሪም የድርቆሽ ሳር ከማምረት ባሻገር የተቀነባበረ የእንስሳት መኖ እንደ አስፈላጊነቱ ለጥጃ፤ ለኮርማ እና ለወተት ላሞች በ ራሱ መኖ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ እያመረተ ለዋና መስሪያ ቤት ኮርማዎች ፤ ለቢሾፍቱ እንስሳት ልማት ማዕከል የወተት ላሞች እና ክልሎች እንደሚያከፋፍል እና ፋብሪካዉ በቀን እስከ 150 ኩንታል የማምረት አቅም አለው።

Photos from LDI's post 10/12/2024

ኢትዮ-ቻይና የኢኮኖሚ ንግድ ወደ ላቀ እድገት የሚያሸጋግር ልምድ ልውውጥ ተደረገ
በእንስሳት ልማት እንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አሥራት ጤራ(ፒኤችዲ)ና አመራሮች እንድሁም የመካከለኛ አፍሪካ ቀጠና ስራ ሀላፊ ው ሊያዓንቢን(Ms Wu Lianbin) እና ሊዩ ያጅናን(Mr Liu Yajnan) ጋር የሁለቱ ሀገራት የንግድ ልውውጥ(import-export) ያሉት እድሎችና እንቅፋቶች በተለይ በተቋማችን እየተሰራ ባለው የቄራዎች ጥራት እና ደረጃ የማሳደግ ፡እንዲሁም ወደ ቻይና የሚላኩ ምርቶች ብዛታቸውና ጥራታቸውን ጠብቆ በተለይ የስጋ ምርት ወደ ቻይና ተልኮ ለሀገሪቱ የዉጭ ምንዛሬውን ማሳደግ በሚቻልበት ዙሪያ ተዋያይቷል።
በዚህ አመት ብቻ ኢትዮጵያ ከቻይና ወደ 435.95ሚ ዶላር በላይ ስጋን ጨምሮ ከተለያዩ ሸቀጣ ሸቀጦች አግኝታለች። የሀገሪቱ የስጋ መላክ ሙሉ አቅሟ 200,000 ስጋ ቶን ብሆንም በአሁኑ ወቅት ግን 22,000ስጋ ቶን ስጋ ብቻ መላክ እንደተቻለ ስሆን የመላክ አቅሟን ለማሳደግ እየተሰራ ይገኛል።

06/12/2024

የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት አመራሮች እና ሠራተኞች ለ19ኛ ጊዜ "አገራዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት' በሚል መሪ ቃል የብሔር ብሔረሰቦችእና ሕዝቦች በዓል በደማቅ ሁኔታ አክብሯል።

በበዓሉ ለዕለቱ በተዘጋጀው ሰነድ ላይ የግንዛቤ ማሰጨበጫና ውይይት ተካሂዷል።

01/12/2022

በግብርና ሚኒስቴር የሌማት ትሩፋት ፕሮግራም ላይ ማብራሪያ ተሰጠ
===================================

ሀገራችን በአረንጓዴ አሻራ ላይ እያካሄደች ያለችውን ውጤት በማስፋት በበጋ ሥንዴ ልማት አለምን ያስደመመ እመርታ እያስመዘገበች ትገኛለች፡፡ ከነዚህ ሁለት ትላልቅ ሥራዎች የተገኙ ልምዶች፣ ተሞክሮዎች እና ውጤቶች በመነሳት የእንስሳት ሀብታችንን በዕቅድና መርሃ-ግብር በመመራት በአግባቡ ለሕዝባችን ጠቃሚ ለማድረግ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ዶክተር አብይ አህመድ የሌማት ትሩፋት ፕሮግራም (የወተት፣ ዶሮና ማር ማሻሻያ ፕሮግራም) በሚል አነሳሽነት በግብርና ሚኒስቴር ፕሮግራም እና መርሃ-ግብር ተቀርጾ እና አቅጣጫ ተሰጥቶ ወደ ሥራ ስለመገባቱ የግብርና ሚኒስቴር እንስሳት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶክተር ፍቅሩ ረጋሳ እና የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ክቡር ዶክተር አስራት ጤራ በፋና ቴሌቪዥን ቀርበው ማብራሪያ ሰጡ፡፡
የሌማት ትሩፋት በዋናነት አራት ዓላማዎች ያሉት ሲሆን እነሱም፡-
1. በአልሚ ምግቦች/Proteinous/ ምግብና ሥነ-ምግብ እራስን በመቻል ማዕዳችን እንዲሞላ ማድረግ፣
2. ለሀገር ውስጥም ሆነ ለውጪ ሀገር ለገበያ እንዲቀርብ በማድረግ በውጪ ምንዛሪ ከውጪ ሀገር የሚገባውን የእንስሳት ተዋጽኦ በማስቀረት በሀገር ምርት መተካት፣
3. የእንስሳት ተዋጽኦን ለውጪ ገበያ በማቅረብ የውጪ ምንዛሪ ግኝትን ማሳደግ እና
4. ለማህበረሰባችን/ዜጎቻችን የሥራ ዕድል መፍጠር ነው፡፡
ልክ ለአረንጓዴ አሻራና ለበጋ ስንዴ ስኬት ያበረከትነውን አስተዋጽዎ ለሌማት ትሩፋት ፕሮግራም ስኬት ተመሳሳይ አስተጽዎ በማድረግ ሀገራችንን እናሳድግ!

Photos from LDI's post 25/11/2022

ትምህርታቸውን በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ላሻሻሉ ሠራተኞች እውቅና ተሰጠ
=====================================
የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ማኔጅመንት እና ሠራተኞች በጋራ 2 በሁለተኛ ዲግሪ እና 1 በሶስተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ላሻሻሉ የኢንስቲትዩቱ ሠረተኞች የእንኳን ደስ አላችሁ ፕሮግራም በማዘጋጀት ዛሬ ህዳር 16 ቀን 2015 ዓ.ም አከበረ፡፡ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬከተር ዶ/ር አስራት ጤራ ዶ/ር ዳንኤል ደምሴ በሁለተኛ ዲግሪ(MVSC)፣ አቶ ዳኜ ሙሉነህ (MSC) በሁለተኛ ዲግሪ እና ዶ/ር ከፈለኝ ስዩም (PHD) በሶስተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ላሻሻሉ ሠረተኞች እንኳን ደስ አላችሁ በማለት አድናቆታቸውን በመግለጽ ሌሎች ሠራተኞችም ይህንኑ አርዓያ እንዲከተሉ አደራ ብለዋል፡፡

Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Telephone

Website

Address


Addis Ababa

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00