Xogaha khaldan ama Misinformation qaabkee ayay ufaafaan, yaase abuura? Muuqaalkan kooban wuxuu kaacaawinayaa inaad fahanto Misinformation waxa uu yahay iyo sida uu ufaafo:
Digital Literacy Ethiopia - DLE
ዲጅታል፡ሊትሬሲ፡ኢትዮጵያ የኢትዮጵያውያን ወጣቶችን የዲጅታል ሚድያ ሊትሬሲ ማሳደግን ያለመ ነው፤
ዲጅታል፡ሊትሬሲ፡ኢትዮጵያ (DLE)
ዲጅታል፡ሊትሬሲ፡ኢትዮጵያ የኢትዮጵያውያን ወጣቶችን የዲጅታል ሚድያ ሊትሬሲ ማሳደግን ያለመ ነው፤ ግባችን የተሳሳቱ እና ሐሰተኛ መረጃዎች በበዙባት ዓለም ኢትዮጵያውያን ወጣቶች ደሕንነታቸውን ባስጠበቀ እና ኃላፊነት በተሞላ መንገድ ዲጅታሉን ዓለም መጠቀም የሚያስላቸውን እውቀት እና ክሕሎት ማስጨበጥ ነው።
Malasocotaa in Baraha-bulshadu ay leeyihiin cilmi gooni ah oo layidhaa Digital Literacy? Muuqaalkan kagabogo cilmigaas iyo faa’iidadiisa
18/03/2024
Kusoodhawow bogan cusub ee Digital Literacy Ethiopia (DLE), oo aad kahelidoonto cashiro iyo macluumaad laxidhiidha Aaladaha cusub ama Baraha-bulshada:
Bogan ayaa waxa aad kahelidoontaa xogo kaacaawiya inaad fahanto waxyeelada Baraha-bulshada iyo sida aad ugabadbaadi karto, sidoo kale waxaad bogan kahelidoontaa cashiro kaacaawinaya inaad aqoon uyeelato habka ugu haboon ee loo isticmaalo Aalada cusub.
Hadii aad ubaahantahay inaad fahan uyeelato qaabka ay Baraha-bulshadu ushaqeeyaan ee kaaqarsoon ama aana kuumuuqan, dhibaatooyinka ay bulshada gaadhsiiyaan iyo cilmiga kaacaawin kara inaad fahan buuxa kahesho, kuxidhnaw bogan oo qayb ka ah cilmibaadhis ama daraasad aqooneed.
Digital Literacy Ethiopia (DLE)
08/03/2024
በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨ የተዛባ መረጃ ሰለባ ከመሆን መዳን
ዛሬ ላይ የትኛውም የበይነመረብ ግንኙነት ያለው ሰው ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት መመልከት ይችላል። በማህበራዊ አውታረመረቦች ውስጥ የሚጋሩ ልጥፎች ከአብዛኞቹ የሐቅ አረጋጋጮች እና አወያዮች በበለጠ ፍጥነት ሊሰራጩ ይችላሉ፤ ብዙ ጊዜ የማይገመቱ የእውነት፣ የውሸት፣ ከአውድ ውጪ የሆኑ እና ቀጥተኛ ፕሮፓጋንዳ የተደባለቀባቸው ናቸው። ቀጣዮቹን 6 ጥንቃቄዎች በመውሰድ ግን ከተዛባ መረጃ ሰለባነት ራስዎን እና በዙሪያዎ ያሉ ሰዎችን መታደግ ይችላሉ፡፡
1. የተዛባው መረጃ ማንን እንደሚጠቅም ያጢኑ፤ በደረስዎ መረጃ ዙሪያ ግራ የሚያጋቡ መረጃዎችን በማሰራጨት ማን እንደሚጠቅም ቆም ብለው ያስቡ ፤ ከደረስዎ መረጃ ጋር በተያያዘ በየአካባቢው የሚነገሩ ልዩ ልዩ ትርክቶችን ፈትሹ።
2. የትኛውንም መረጃ ረጋ ብለው ያንብቡ፣ያድምጡ፣ ይመልከቱ፡-የማጋሪያ ቁልፉን(Share Button) ከመጫንዎ በፊት ትክክለኛነቱን እስካላረጋገጡ ድረስ የትኛውም መረጃ የተሳሳተ ሊሆን እንደሚችል ያስቡ ፡፡
3. የመረጃውን ትክክለኛ ምንጭ ያጣሩ፣ ሁሌም ‘ቫሪፋይድ’ ስለሆኑ ብቻ የመረጃ ምንጮችን አይመኑ፤ ያስታውሱ አንድ አካውንት ቫሪፋይድ መሆኑ ብቻ አሁን እርስዎ ጋር ላደረሰው መረጃ እውነተኛነት ማረጋገጫ አይሆንም፡፡ ብዙ ቫሪፋይድ አካውንቶች የተዛቡ መረጃዎችን ሲያጋሩ ተስተውለዋል፡፡
4. የታመኑ የመረጃ ምንጮች ስብስብ ይኑርዎት፦ አንድን የደረስዎትን መረጃ የተዛባ መሆን አለመሆኑን ለመለየት ሊያጣሩባቸው የሚችሉ እና የቀደመ የመረጃ ፍሰታቸውን የሚያምኗቸውን የመረጃ ምንጮች ዝርዝር ያዘጋጁ፤ እያንዳንዱን መረጃም እውነተኝነት ለማጣራት ይጠቀሙባቸዋል፡፡
5. የሰመትን የዘና ዘገባ ሌሎች በምን አግባብ እንደዘገቡት ይመልከቱ፤ አንድን ሁነት ወይም ግለሰብ እና ቡድን አስመልክቶ የሰመትን ዜና ከአንድምንጭ ብቻ ተቀብለው ለሌሎች ከማጋራትዎ ቀድሞ ሊሎች የመረጃ ምንጮች በምን መንገድ መረጃውን እንዳጋሩት ይመልከቱ፤ ያነጻጽሩ እና እውነታው ላይ ይድረሱበት፡፡
6. የሐቅ ማረጋገጫ ድረገጾችን ይጎብኙ፣ አሊያም የሚጠቀሙበት የማHበራዊ ሚድያ መተግበሪያ የሐቅ ማረጋገጫ ካለው ይጠቀሙ፡፡ በሚጠቀሙበት ማHበራዊ ሚድያ ላይ የተቀመጡ ማስጠንቀቂያዎችንም ልብ ብለው ይመልከቱ!
ይህ ጽሑፍ Heather kelly ዋሽንግተን ፖስት ላይ ካሰፈረችው የተወሰደ ነው፡፡
06/03/2024
የተዛቡ እና የተሳሳቱ መረጃዎች በኢትዮጵያን ወጣቶች ላይ የጋረጡት የመከፋፈል ጫና
ሕብረ ብሔራዊነት እና ብዝሃነት መሰረት ላይ የተመሰረችው ኢትዮጵያ ዛሬ ዛሬ ላይ የተዛቡ እና የተሳሳቱ መረጃዎች በዜጎቿ በተለይም በወጣቶቿ ላይ የመከፋፈል አደጋ ይዘው ብቅ ካሉ ሰነባብተዋል። የዲጅታል መሰረተልማቶች መስፋፋትን ተከትሎ በማህበራዊ ሚዲያ ስልተ ቀመር ያስከተለው የሳሳ የግለሰቦች ጥምረት ብቻ ሳይሆን የሀገሪቷ ማህበራዊ ትስስርም ትልቅ ስጋት ውስጥ ገብቷል።
የብዝሃነት ገጽታ በኢትዮጵያ
ኢትዮጵያ ከ80 በላይ ብሄረሰቦች የሚኖሩባት ሲሆን በርካታ ቋንቋዎች፣ ኃይማኖቶች እና ባህሎች የያዘች መልከ ብዙ አገር ነች። እንዲህ ያለ ብዝሃነት ደግሞ የባህላዊ ብልጽግናዋ ምንጭ ቢሆንም ዜጎቿን በተለይም ወጣቶቿን ላበጣጠሩ የተሳሳቱ እና የተዛቡ መረጃ መስፋፋት ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል።
የተዛባ መረጃ(Misinformation) እና የተሳሳተ መረጃ (Disinformation)
በሁለቱ መረጃዎች መካከል ያለውን ልዩነት መገንዘብ አስፈላጊ ነው። የተዛባ መረጃ የሚያመለክተው ያለጎጂ ዓላማ የሚሰራጭን ሀሰተኛ ወይም የተሳሳተ መረጃ ነው፣ ብዙ ጊዜ ካለማስተዋል ወይም ከማጣራት የተነሳ ይሰራጫል። በአንፃሩ የተሳሳተ መረጃ ሆን ተብሎ ተዘጋጅቶ የሚሰራጨው የህዝብን አስተያየት ለማታለል እና ለፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ጥቅም ለማዋል በማሰብ ነው።
በኢትዮጵያ ወጣቶች ላይ ያለው ተፅዕኖ
በተለይ በማህበራዊ ድረ-ገጾች ላይ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ላይ የሚገኙት የኢትዮጵያ ወጣቶች ለተዛባ መረጃ እና ለተሳሳተ መረጃ እየተጋለጡ እና እየተጎዱ ነው። ይህ ደግሞ ስር ሰድዶ የጎሳ ግጭቶችን ሊቀሰቅስ እና የሀይማኖት ልዩነቶችን በማባባስ ወደ ማሕበራዊ ግጭት የማምራት አዝማሚያው በተደጋጋሚ ታይቷል። ወጣቶች፣ በአዳጊ ዘመናቸው፣ በተለይም ለሌሎች ቡድኖች ያላቸውን አመለካከትና ድርጊት ሊቀርጽ ለሚችሉ ከፋፋይ ትርክቶች ተጋላጭ ናቸው።
የማህበራዊ ሚዲያ ስልተ-ቀመር(Algorithm) ሚና
የማህበራዊ ሚዲያ ስልተ ቀመሮች ወሳኝ ሚና ይጫወታሉ። እነዚህ ስልተ ቀመሮች ለተጠቃሚዎች ከፍላጎታቸው እና ከቀድሞ ግንኙነታቸው ጋር የሚጣጣም ይዘት በማሳየት ተሳትፎን ለመጨመር በማለም የተነደፉ እና በጥቅም ላይ የሚውሉባቸው ናቸው። ይህ ማለት ደግሞ ብዙውን ጊዜ ተጠቃሚዎች ጠባብ የመረጃ ዥረት ይመገባሉ ማለት ነው ፣ ይህም ነባር እምነቶችን እና ጭፍን ጥላቻን የሚያጠናክሩ ትርክቶችን የማስተጋባት ዕድልን ይፈጥራል። በኢትዮጵያ ሁኔታ እነዚህ ስልተ ቀመሮች ከፋፋይ ይዘትን በማጉላት በተለያዩ ቡድኖች መካከል ያለውን አለመግባባትና ጥላቻ የበለጠ እንዲስፋፋ ያደርጋሉ።
ፈተናውን መሻገር
በኢትዮጵያ ውስጥ የተዛቡ መረጃዎችን እና የተሳሳቱ መረጃዎችን መዋጋት ዘርፈ ብዙ ጥረት ይጠይቃል። ወጣቶችን ስለ ሚዲያ ማንበብ፣ ሂሳዊ አስተሳሰብ( Critical Thinking)ን ማበረታታት እና ባህላዊ ግንዛቤን ማሳደግ ቁልፍ ስልቶች ናቸው። በተጨማሪም የማህበራዊ ሚዲያ ኩባንያዎች ጎጂ ይዘት እንዳይጨምር ለመከላከል እና የበለጠ የተለያየ እና ትክክለኛ የመረጃ ውክልናን ለማስተዋወቅ ስልተ ቀመሮቻቸውን እንዲያጠሩ በየደረጃው ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ማሳሰብ አለባቸው።
ለማጠቃለል ያህል፣ የተሳሳቱ መረጃዎችና የተዛቡ መረጃዎች ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ሆነው ሳለ፣ ተጽኖአቸው በጥልቅ የሚስተዋለው እንደ ኢትዮጵያ ባሉ የወጣት ዜጎቻቸው ቁጥር ከሕዝብ ብዛታቸው ውስጥ አብዛኛውን በሚይዝባቸው ታዳጊ አገራት ውስጥ ነው። እነዚህን ተግዳሮቶች መፍታት በህዝቦቿ መካከል አንድነትና መግባባት እንዲፈጠር፣ የሀገሪቱ ብዝሃነት ከመበዝበዝ ይልቅ እንዲከበር ለማድረግ ወሳኝ ነው።
ለተዛቡ መረጃዎች ተጋላጭ ስለሚያደርጉን ስነልቦናዊ ምክንያቶች ማወቅ ይሻሉ? እንግዲያው ይሕ ቀጣይ ቪድዮ ምላሽ ይዟል!
01/03/2024
ዲጅታል ሊትሬሲ በዘመናዊው ዓለም ውስጥ ከዲጅታል ቴክኖሎጂ ጋር የተያያዘ ሁሉን አቀፍ
እውቀት ማለት ነው። ታዲያ እርስዎ ይህን ጽንሰ ሐሳብ ምን ያሕል ተረድተውታል? ይህንን አጭር
መጠይቅ ይሙሉ እና የመረዳትዎን ደረጃ ይመዝኑ!
QUIZ: ስለ ዲጅታል ሊትሬሲ ምን ያሕል ተገንዝበዋል? መግቢያ፡ ዲጅታል ሊትሬሲ በዘመናዊው ዓለም ውስጥ ከዲጅታል ቴክኖሎጂ ጋር የተያያዘ ሁሉን አቀፍእውቀት ማለት ነው። ታዲያ እርስዎ ይህን ጽንሰ ሐሳብ ምን ያሕል ተረድተውታል? ይህንን አጭ...
28/02/2024
25/02/2024
በዚህ ዘመን በ"አንላይን’’ ላይ የሚሰራጬ (ለሠዎች የሚጋሩ) እና የሚፈበርኩ መረጃዎችን እውነተኛነት ማጣራት ለዘርፉ ባለሙያዎች ሳይቀር በጣም ከባድ ሆኗል።
ዲጅታል ሊትሬሲ ኢትዮጵያ(DLE) ከሐሰተኛ ዜናዎች ጋር ተያያዥና ተዛማጅ የሆኑ ቃላትና ፅንስ ሐሳቦችን በማፍታታት እና ተደራሽ በማድረግ ሰለ ሐሰተኛ መረጃ ምንነት እና ስርጭት ገንቢ ግንዛቤ በመፍጠር ዜጎች የተዛባ መረጃ(Misinformation)፣ የተሳሳተ መረጃን(DisInformation) እና የሐሰት ዜናን(Fake News) መለየት እንዲችሉ ይሰራል።
ስለ የተዛባ መረጃ(Misinformation)፣ የተሳሳተ መረጃ(DisInformation) እና የሐሰት ዜና(Fake News) ጥልቅ ግንዛቤ ማዳበር ስንችል እንዲህ ያሉ መረጃዎች እና ዜናዎች በዲጅታሉ ዓለም ውስጥም ሆነ በማሕበራዊ ሕይወታችን በሚገጥሙን ወቅት በቀላሉ መለየት እና ራሳችንን እና ወሳኔያችንን ከመረጃው ሰለባነት እንታደጋለን፤ ብሎም ጓደኞቻችንሁ እና ቤተሰቦቻችን ሐሰተኛ ዜናን እንዳያሰራጩ ግንዛቤን መፍጠር ይቻለናል።
በእርግጥ በተዛባ መረጃ(Misinformation)፣ በተሳሳተ መረጃ(DisInformation) እና በሐሰት ዜና(Fake News) መካከል ያለዉ ልዩነት ምንድ ነው ?
ሁላችንም የሐሰት ዜና(Fake News) ሲባል በአንድም ይሁን በሌላ አጋጣሚ ሰምተናል። ነገር ግን በትክክል ትርጉሙ ምን ማለት እንደሆነ እናውቅ ይሆን? በተሳሳተ መረጃ(DisInformation) እና በሐሰት ዜና(Fake News) መካከል ያለዉን ልዩነት ጠንቅቀን ተረድተንስ ይሆን?
ዲጅታል ሊትሬሲ ኢትዮጵያ(DLE) እነዚህን እንዲሁም ተያያዥ እና ተዛማጅ ቃላትን መበየን የምችልበት እውቀት እና ክሕሎት ሊያጋራን ዝግጁ ነው።
1. የተዛባ መረጃ(Misinformation)፡ የተዛባ መረጃ አንድን መረጃ እውነተኘቱን እና የምንጩን ሕጋዊነት እና የቀደመ ተሞክሮ ሳያጣሩ ከግለሰቦች ፍላጎት እና መሻት ጋር ስለገጠመ ብቻ የሚጋራ መረጃ ሲሆን ሆን ብሎ ሌሎችን የማሳሳት አጀንዳ እና ሴራ ግን የሌለው ነው። መረጃው ትክክል ነው ብለዉ በሚያስቡ ሰዎች አማካይነት ይሰራጫል።
2. የተሳሳተ መረጃ(DisInformation)፦ ሆን ተብሎ ሌሎችን ለማሳሳት ወይም ወገንተኛነትን የሚያሳይ መረጃ ሲሆን የመረጃውን ተቀባይ ማሕበረሰብ ሊያሳስት እንዲችል ተደርጎ በተቀነባበረ የቅጥፈት ትርክት፣ በፈጠራ እውነት ወይም ፕሮፖጋንዳ አማካይነት የሚሰራጭ ነው :: በሌላ አገላለጽ የተሳሳተ መረጃን በአንድ ሰዉ ወይም ቡድን አማካኝነት የተሳሳተ መሆኑን እያውቁ ሆን ብለው ለማሳሳት በቀጥታ " ኦን ላይን" አማካኝነት የሚሰራጭ ነው። በአጠቃላይ ሰዎች ይህንን የሚያደርጉት ለራሳቸው ዓላማቸው ሲሆን አብዛኛውን ጊዜ ይህንን የሚያደርጉት በሰዎች ላይ የራሳቸውን አመለካከትና ተፅዕኖ ለመፍጠር ነው።
3. የሐሰት ዜና(Fake News)፦ ሆን ተብሎ የተነደፈ ፣ አማላይና ሳቢ፣ ስሜትን በሚነካ መልኩ የሚቀርብ ሲሆን አሳሳች ወይም ሙሉ በተቀነባበረ መረጃ የተሞላና ከዋና ዋና የዜና ምንጮች ጋር በጣም በሚመሳስል መልኩ የሚዘጋጅ ነው። ከተሳሳተ መረጃ(DisInformation) የሚለየው የመደበኛ ዜና ቅርጽ እንዲኖረው የሚደረግ በመሆኑ ነው። የተሳሳተ መረጃን የሚያሰራጩ የመረጃ ድህረ-ገፆችን ዋቢ (ምንጩ) ያደረገ ዜና ነው። እነዚህ ድረ-ገጾችም የሐሰተኛ መረጃዎች ጥርቅም ሲሆኑ ታማኝ የዜና ምንጭ መስለው ነው ዜናዎቹን የሚያቀርቡት።
ታዲያ እንዲህ ያሉ መረጃዎች ስርጭት አካል ከመሆን ራሳችንን መጠበቅ የምንችለው እንዴት ይሆን?
ከዲጅታል ሊትሬሲ ኢትዮጵያ ጋር ሲቆዩ በዚህ ረገድ በቂ መረጃ ያገኛሉ!
በዚሕች በየቀኑ በምትቀያየር ዲጅታል ዓለም ውስጥ መረጃ በነጠላ ሕይወታችን ውስጥ ያለው ዋጋ ከቶውኑ የሚያጠያይቅ አይደለም።
እርስዎስ ስለ Misinformation (የተዛባ መረጃ) ምን ያሕል ያውቃሉ? ይሕ አጭር ቪድዮ ጥሩ ግንዛቤ እንዲያዳብሩ ያግዝዎታል።
ስለ Misinformation (የተዛባ መረጃ) የበለጠ ለማወቅ ካሹ ይህን ማስፈንጠርያ ይከተሉ፤ https://library.uaf.edu/topics/misinformation
በዲጂታል በተገነባ ማህበረሰብ ውስጥ ለመኖርና ለመማር በዲጂታል ሊትሬሲ ብቁ ሆኖ መገኘት የግድ ነው ።
የዲጂታል ሊትሬሲ ሃሳብ ተገቢውን ትኩረት ማግኘት የቻለው ባለፉት አስር አመታት ውስጥ ነው። መጀመሪያ ላይ ዲጂታል ሊትሬሲ ላይ የነበረው ግንዛቤ ኮምፒዩተርና ኢንተርኔትን ለመጠቀም እንደሚያስፈልግ ክህሎት ተደርጐ ነው።
ዲጅታል ሊትሬሲ የህይወት ክህሎት በመሆኑ የስራ እድል ማግኛ ብቻ ተደርጐ መወሰድ የለበትም :: ከዛ ይልቅ ሌሎች በህይወት ውስጥ ያሉ እጅግ ጠቃሚ ነገሮችን ማግኛ መንገድ ተደርጐ መታየት እንዳለበት ዩኔስኮ እና መሰል ተቋማት አበክረው፡ይገልጻሉ።
ዲጂታል ሊትሬሲ፡ሁሉን አቀፍ በሆነ ሁኔታ አንድ ሰዉ በ ዲጂታል ማኅበረሰብ ውስጥ ለመኖር ፣ ለመማርና ለመስራት በጣም አስፈላጊ ክሕሎት እንደሆነም ይገለፃል።
በዚህ ምጥን ቪድዪም የዚህን፡ገዛፋ ክሕሎት ዳራ እና አስፈላጊነት እንቃኛለን!
ከዲጅታል፡ሊትሬሲ፡ኢትዮጵያ (DLE) ጋር በመሆን በቂ መረጃ ያግኙ፤ ኑ አብረን ተጨባጭ ለውጥ እንፍጠር!!
Click here to claim your Sponsored Listing.
Location
Category
Website
Address
Addis Ababa