09/03/2026
እውነትም እንቁላል ቀስ በቀስ በእግሯ ትሄዳለች።🙊🐣🐤🐔
Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Reader is Leadar, College & University, Addis abeba, Addis Ababa.
09/03/2026
እውነትም እንቁላል ቀስ በቀስ በእግሯ ትሄዳለች።🙊🐣🐤🐔
27/02/2026
01/02/2026
መልዕክተኛው ስነ ስለ ድንቋ አርቲስት ሳያት ደሚሴ ማንም የማያውቀውን ትልቅ ምስጢር አጋርቷል. ስነ እንደሚለው, ሳያት ማንም እንዲያውቅባት ሳትፈልግ በድብቅ ከ300,000 ብር በላይ ለተቸገሩ ወገኖች ድጋፍ አድርጋለች. ስነ ስለ ሳያት ደግነት ሲናገር "አንድ ቀን በትልቅ ሚዲያ ላይ ስለ ደግነትሽ እመሰክራለሁ" ብሎ ቃል ገብቶላት የነበረ ሲሆን, አሁን ያንን ቃሉን በመፈጸሙ ትልቅ ደስታ እንደሚሰማው ገልጿል. በመካከላቸው ስላለው የፍቅር ወሬም ሲናገር, ግንኙነታቸው በንጹህ ጓደኝነትና በመከባበር ላይ የተመሰረተ መሆኑን በግልጽ አስታውቋል. ሳያት ውበቷ ከውጭ ብቻ ሳይሆን ከውስጥም የሆነ, ለብዙዎች አርአያ የምትሆን ድንቅ የኢትዮጵያ ልጅ ናት. ለካስ እውነተኛ ውበት ማለት በድብቅ የሚደረግ ደግነት ነው. ሳያት ደሚሴ ደግሞ የዚህ ውበት ተምሳሌት ናት!
28/12/2025
የቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም አመሠራረት በአጭሩ!
ከአዲስ አበባ በስተምሥራቅ 461 ኪ/ሜ. ርቀት ላይ በምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ጋራ ሙለታ የሚገኝ ቤተ ክርስቲያን ነው፡፡
ከ40 ዓመታት ስደት በኋላ አንበሣ ውድም ወደ አኵሱም ሲመለስና የንዋያተ ቅዱሳት ቆጠራ ሲደረግ ታቦተ ቅዱስ ገብርኤል በዝዋይ መቅረቱ ታወቀ፡፡ ከኤርትራ ደብረ ሲና ማርያም የመጡና አባ ሌዊ የተባሉ አባት ታቦቱን ለማምጣት ከንጉሡ አስፈቅደው ወደ ዝዋይ መጡ፡፡
አባ ሌዊ ከሰባት ቀን ሱባኤ በኋላ ታቦተ ቅዱስ ገብርኤልን ይዘው ወደ አኵሱም ሲጓዙ ቅዱስ ገብርኤል ተገልጦ “እኔ ወደማሳይህ ቦታ ታቦቱን ይዘህ ሂድ” አላቸው፡፡ አባ ሌዊም ታቦቱን ይዘው ተከተሉት፡፡ በመጨረሻም ቁልቢ ደረሱ፡፡ ለአባ ሌዊም የተፈቀደላቸው ቦታ ይሄ መሆኑን ታቦቱም በኋላ ዘመን ለሕዝቡ ድንቅ ሥራ እንደሚሠራ ቅዱስ ገብርኤል ነግሯቸው ተሠወረ፡፡ አባ ሌዊ በቦታው ለ130 ዓመታት ያህል አገልግለው በንጉሥ ግርማ ሥዩም ዘመነ መንግሥተ ታኅሳስ 14 ቀን ዐርፈዋል፡፡
ግራኝ አሕመድ ኢትዮጵያን ሲወርር ብዙ ካህናት ከሰሜን ኢትዮጵያ ታቦታትንና ንዋያተ ቅዱሳትን ይዘው ሲጓዙ ቁልቢ ደረሱ፡፡ መልአከ ገነት መብረቁ፣ መምህር የማነ አብ፣ አባ ተከስተ ሥሉስ የተባሉ ካህናት ከተነጠፈ ድንጋይ ላይ የተጻፈ ነገር ያገኛሉ፡፡ ጽሑፉም ታቦተ ቅዱስ ገብርኤል በሥዉር መቀመጡን፣ ልዩ ልዩ ተአምራት እንደሚፈጸምበት፣ ወደ ፊትም ታላቅ ቤተ መቅደስ እንደሚሠራበት፣ እንዴት አባ ሌዊ ታቦቱን ወደዚህ ቦታ እንዳመጡት የሚገልጽ ነበር፡፡ እነርሱም ይህን ታሪክ ይዘውት በነበረው መጽሐፈ ቀሌሜንጦስ ሕዳግ ላይ ጻፉት፡፡ ወደ ዝዋይ ደሴት ሲደርሱም መጽሐፉን በዚያ አኖሩት፡፡
የመቃኞው ሥራ በ1883 ዓ.ም ተጀምሮ ፍጻሜ አግኝቶ ቅዳሴ ቤቱ የተከበረው ሐምሌ 19 ቀን 1884 ዓ.ም ነው፡፡ በዚሁ ዕለት የዋናው ቤተ ክርስቲያን ሕንጻ ሥራ የመሠረቱ ድንጋይ ተጥሎ ታኅሳስ 19 ቀን 1888 ዓ.ም የቤተ ክርስቲያኑ ሥራ ተፈጽሞ በአቡነ ማትያስ ተባረከ፡፡ ቦታውን ከባለ አባቶች የገዙት በአርባ የቁም ከብት ነው፡፡ ራስ መኰንን መጋቢት ዘጠኝ ቀን 1889 ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ ሲሄዱ እዚህ ቦታ ላይ በድንገት ስለታመሙ በዕለቱ ሥጋወደሙ ተቀብለውበታል፡፡ በመጀመርያ ሲተከል በገጠር ቤተ ክርስቲያን ሥሪት ሲሆን በኋላ ግን በስእለት ሰማኢነቱ በመላ ኢትዮጵያ እየታወቀ ስለ መጣ ደብር ሆኗል፡፡
የቅዱስ ገብርኤል ምልጃና በረከት አይለየን!!
(ምንጭ፡ የቤተ ክርሰቲያን መረጃዎች- በዲ/ን ዳንኤል ክብረት፤ Saints and Monastries in Ethiopia, by Kesis Kefyalew Merahi)
#እናት ዓለም ድንግል ለድንግል ማርያም ትላ ተስዮ ይዤ ልሄድ ነው ።
#የሳምንት ሰዉ አንሁን ሁሉም በተረጋጋ በዕዉቀት መሄድ አለበት
ድድብ በሉ ( ነገሮችን እስከወዳኛዉ ታገሱ
#ማንም አልሰማም (ከማለት ለህልሜ እከወዳኛዉ እፀናለሁ
ብቻ ቃል ይገላል ቃል ያድናል አፋችን እናመጣ መናገር ተገቢ አደለም ዋጋ ያስከፍላል ።
#ሸላሚዎችም ደድብ እያለ የገባን ሸልሞ አለባበስ ብቻ ማየት ተገቢ አደለም ቅጠል ለብሶ የመጣን አባሮ ሴት ሆኗ የወንድ ልብስ ለብሳ መረብ በራቀት አፅም ያስገባ የሽልማት ማዕከል ነው ።
ብቻ እንመካከር የሳምንት ሻሩክ (እዩኝ እዩኝ ከዛ ደብቁኝ ደብቁኝ ይመጣል ።
06/12/2025
06/12/2025
ዲማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም/ደብረ ድማህ\
ዲማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም በምስራቅ ጎጃም ዞን በእነማይ ወረዳ ከብቸና ከተማ 28 ኪ/ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ የገዳሙ መጠሪያ ስም ደብረ ዲማህ ሲሆን ትርጓሜውም ራስ ወይም ጭንቅላት ማለት ነው ፡፡
የዲማ ቅድስ ጊዮርጊስ ገዳም የተመሠረተው በአጼ አምደ ጽዮን ዘመነ መንግሥት በ1297 ዓ.ም ነው። በአፄ ይሥሃቅ ዘመነ መንግሥት ጀምሮ ደግሞ ገዳም ሆኖ ስፍትና ክብር ተጨምሮለት መኖር እንደጀመረ የታሪክ ድርሳናት ይናገራሉ ፡፡
ዲማን የመሰረቱት አባት አባ በኪሞስ ሲሆኑ ተከስተ ብርሃን የተባለው ስም የተሰጣቸውም በጎጃም እየተዘዋወሩ ወንጌልን በመስበክ እየጠመቁ ሳለ አንድ ቀን ከአማንያን ብዛት የተነሳ የማጥመቅን ስራ ሳይጨርሱ ጀንበር ስትጠልቅባቸው አምላክን በመለመን ብርሃን ወርዶላቸው ስራአተ ጥምቀቱን ፈጽመው እንደሄዱ ታሪክ ይነገራል ፡፡
ይህ ገዳም በውስጡ በረካታ ጥንታዊ ቅርሶችን የያዘ ሳሆን ከእነዚህም የንጉሥ ተክለሃይማኖት ጦር፤ እና የራስ መኰንን ካባ ከብዙ በጥቂቶቹ የሚጠቀሱ ናቸው።ከዚህ በተጨማሪ በመጻሕፍት ትርጓሜ ቤት የሚታወቅ ሲሆን በረካታ የትርጓሜ መምህራን የፈለቁበት ታላቅ ገዳም ነው።
@ሀብታሙ ሲሳይ