13/04/2026
Tegbareid Polytechnic College
As a technical and vocational school our main objective is producing middle level technicians who ar
Addis Ababa Tegbare-id Poly Technique College was established in 1942 as a Technical School. Since then, the college has been offering vocational trainings mainly for technical occupations. Tegbare-id is currently regarded as one of the top polytechnic colleges. Currently, the college offers vocational trainings in twelve different occupational fields, including Information and Communication Techn
13/04/2026
12/04/2026
12/04/2026
11/04/2026
እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን!
የትንሣኤ በዓል በክርስቲያኖች ዘንድ ልዩ ቦታ ያለው በዓል ነው። ሞት የተሻረበትና ሕይወት ዋስትና ያገኘበት ነው። ከሞት ባሻገር ሕይወት፣ ከመቃብር ባሻገር ትንሣኤ መኖሩ የታወጀበት ነው። ሞት መጨረሻ መቃብር መዳረሻ አለመሆናቸው የተረጋገጠበት ነው። በአዳም ምክንያት ወደ ምድር የወረደው ሰው፣ በክርስቶስ ምክንያት ወደላይ የወጣበት ነው።
የዘንድሮውን ትንሣኤ የምናከብረው ሀገራችን ኢትዮጵያ በሚያልፍ ፈተና ውስጥ እንዳለች እያሰብን ነው። መንገዳችን ረጅም፣ ጉዟችን ፈታኝ መሆኑን እናውቃለን። ብርሃን እንዳናይ የሚጋርዱ፣ በጥልቁ ጨለማ ጠፍተን እንድንቀር አሥረው ለመያዝ የሚሞክሩ ወጥመዶች ብዙ ናቸው። ወደ ተስፋ ምድር እንዳንሻገር የሚጎትቱ ሰበቦች ሞልተዋል። ዳሩ ግን ከሕማማቱ ወዲያ ትንሣኤ፣ ከዕንቅፋቱ ባሻገር ስኬት እንደሚጠብቀን አምነን እንታገላለን።
በትንሣኤው ዋዜማ - ርግጠኞች፣ ተስፈኞች፣ ተስፋ ቆራጮች፣ ወሬኞች፣ ተስፋ አስቆራጮች፣ ተጠራጣሪዎች ነበሩ። ርግጠኞቹ የሕማማቱ ፈተና እንደሚያልፍ ርግጠኞች ነበሩ። የዕለተ ስቅለት መከራ፣ለዕለተ ትንሣኤ ዋዜማ ለመሆኑ ርግጠኞች ነበሩ። የድንጋዩ በር፣ የበሩ ማኅተም እና የመቃብሩ ጠባቂዎች ትንሣኤውን እንደማያስቀሩት ርግጠኞች ነበሩ። የሚናፈሰው ወሬ እና የሚሠራጨው አሉባልታ እድሜው አጭር መሆኑን ርግጠኞች ነበሩ። ርግጠኞችም ስለሆኑ መሥዋዕትነትን ለመክፈል ዝግጁዎች ነበሩ። እውነቱን ለመመስከር ቆራጦች ነበሩ። በመስቀሉ ሥር ለመገኘት ደፋሮች ነበሩ።
ተስፈኞቹ የርግጠኞቹን ያህል ሳያዩ የሚያምኑ አልነበሩም። ግን አንዳች መልካም ነገር ይጠብቁ ነበር። የተሰጠውን ትምህርት፣ የተደረገውን ተአምራት ሰምተዋል፤ አይተዋል፤ አንዳች ነገርም ጠብቀዋል። ነገር ግን ተገቢውን መሥዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁዎች አልነበሩም። እውነትን ለመድፈር ቆራጦች አልነበሩም። ሐሰቱን ለመጋፈጥ ዐቅም አላገኙም። ቢያንስ ግን አንደበታቸውን ከክፉ ከልክለዋል።
ተጠራጣሪዎች አጥር ላይ የነበሩ ናቸው። በጥብርያዶስ ይበላሉ፣ በጎልጎታ ይክዳሉ። በሆሳዕና ይዘምራሉ፣ በሊቶስጥራ ይሸሻሉ፡፡ ተአምር ለማየት ይመጣሉ፣መከራ ለማየት ይሳቀቃሉ፡፡ ከደስታው አውጡልኝ፣ ከመከራው ጦመኛ ነኝ የሚሉ ናቸው።
ተስፋ ቆራጮች በሚያዩትና በሚሰሙት ቶሎ የሚወሰዱ ናቸው። በእውነትና በሐሰት፣ በፍርሃትና በጽናት መካከል ያለው ድንበር የጠፋባቸው ናቸው። ሕማማቱ ሲመጣ በቶሎ ወደ ትዝታ ገቡ። ሁሉንም ነገር የትናንት ታሪክ ብቻ አድርገው ወሰዱት። ሁሉንም ነገር “ልጡ የተራሰ፣ መቃብሩ የተማሰ” አድርገው ቆጠሩት። ከግራ ከቀኝ የሚሰሙት አሉባልታ፣ ከፊት ከኋላ የሚመጣው ጫጫታ፤ ከወዲህ ከወዲያ የሚማጣው እሳት፣ ከዚህም ከዚያም የሚያዩት መዓት አስፈራቸው። ነገን አስረሳቸው። በዚህ የተነሣ ተስፋ ቆርጠው ወደ ኋላ ተመለሱ።
ወሬኞች ድሮም ወሬ ስቧቸው የመጡ ናቸው። ምን አለ ምን ተባለ ብለው የተሰባሰቡ ናቸው። የሰሙትንም ያልሰሙትንም፤ የሚያውቁትንም የማያውቁትንም፤ እውነቱንም ሐሰቱንም እያደባለቁ ኢየሩሳሌምን በወሬ ሞሏት። ቢያንስ ከትንሣኤው 15 ዓመት በኋላ ወንጌሉን የጻፈው ማቴዎስ፣ እስከዚያ ዘመን ድረስ ወሬው ብዙ ተቀባይ እንደነበረው ገልጧል።
ተስፋ አስቆራጮች ዓላማቸው ሰውን ሁሉ ከትንሣኤ መንገድ ማራቅ ነበር። እነርሱም አይሄዱ፣ ሰውም አያስኬዱ። ከመጀመሪያው አልተቀበሉትም፤ በኋላም አልፈለጉትም። ብዙ ሰዎች እንደተከተሉት ሲያውቁ ደግሞ ቅናት አቃጠላቸው፤ ክፋት አንገበገባቸው። ክርስቶስን ከሰሱ፤ ራሳቸው ምስክር ሆኑ፤ በመጨረሻም ራሳቸው ፈረዱ። መቃብሩን ዘጉ፤ ጠባቂ አስቀመጡ። በማኅተም አሸጉ። ነገር፣ ያለቀና የተቆረጠ መሰላቸው።
የትንሣኤ በዓል የእነዚህን ሁሉ እውነተኛ ማንነት የገለጠ ነው። ርግጠኞች የቆራጥነታቸው ውጤት በትንሣኤ አገኙ። ተስፈኞች እንዲህ ለሚያልፍ ጊዜ ባለመጽናታቸው አዘኑ። ተስፋ ቆራጮች አሻግሮ ማየት አቅቷቸው ከቦታቸው በመጥፋታቸው ተፀፀቱ። ወሬኞች በትንሣኤው እውነት የተነሣ ያ ሁሉ ወሬ እንደ ናቡከደነፆር ሐውልት ሲፈረካከስ አዩት። ተስፋ አስቆራጮች የገደሉት ክርስቶስ ሲነሣ፣ የዘጉት መቃብር ሲከፈት፣ ያተሙት ማኅተም ሲቀደድ፣ የመደቧቸው ጠባቂዎች ሲሸሹ በዓይናቸው በብረቱ አዩ። ትንሣኤው የሚነገር ሐቅ፣ የሚታይ እውነት ሆነ። ተጠራጣሪዎች ግን አሁንም አጥራቸው ላይ ሆነው ከግራም ከቀኝም ሳይሆኑ ቀሩ።
የኢትዮጵያችንም ነገር እንዲሁ ነው። በኢትዮጵያ ለውጥ ርግጠኞች የሆኑት ዋጋ ይከፍላሉ፤ ርግጠኝነትን ፈርተው ተስፈኞች የሆኑት ቢያንስ አንደበታቸውን ከክፉ ይጠብቃሉ፡፡ ተስፋ ቆራጮች ነገን ማየት ስለሚሳናቸው መንገዳቸውን ይቀይራሉ፡፡ ወሬኞች አውርቶ አዳሪዎች በመሆናቸው የወሬ እንጀራ ይጋግራሉ። ተስፋ አስቆራጮች “ወተቱን አጥቁረው፣ ማሩን አምርረው” የዋሖችን አታለሏቸው፡፡ ተጠራጣሪዎች አንዴ ትኩስ አንዴ ቀዝቃዛ ሲሆኑ፣ ለብ ብለው ቀሩ።
ኢትዮጵያችን ግን ትንሣኤዋን እያየች ነው። መግነዙን ፈትታዋለች፣ መቃብሩን ከፍታዋለች፤ ማኅተሙን ቀዳዋለች። ወሬኞች ከመቃብር ጠባቂዎች ጋር ተማክረው የሚያወሩትን ወሬ የምትሰማበት ጆሮ የላትም። ትንሣኤዋን አይለውጠውምና። እሷ ከዚህ በኋላ የምትጠብቀው ዕርገትን ነው። የምትጓዘው ኃይል እንደሚወርድላት አረጋግጣ ነው። ወደኋላ መመለስ የለም። ሕማማት አልፏል፤ዓርብም አልፏል፤ ቅዳሜም አልፏል። ትንሣኤ መጥቷል። በትንሣኤ ሌሊት የተኙ አልሰሙ ይሆናል። በተስፋ አስቆራጮች ተታለው የሄዱ ዜናው አልደረሳቸው ይሆናል። ትንሣኤ ግን እውን ሆኗል።
ከቻላችሁ አጥር ላይ ያላችሁ ውረዱ። ተስፈኞች ርግጠኞች ሁኑ። ተጠራጣሪዎች እመኑ። ወሬኞች ከአፍ ወደ መዳፍ ተለወጡ። ምክንያቱም - ኢትዮጵያ ወደ ትንሣኤ ተቃርባለች።
የኢትዮጵያ ትንሣኤ ከሚበሰርባቸው ምዕራፎች አንዱ ግንቦት ላይ የሚካሄደው ምርጫ ነው። ትንሣኤን ያለ ሕማማት እንደማናስበው ሁሉ ዴሞክራሲንም ከውጣ ውረድ ነጥሎ ማየት አይቻልም። በዓለም ላይ በደልዳላ መንገድ ተጉዞ ዴሞክራሲን የገነባ ሀገር የለም። ዴሞክራሲና ብልጽግና ያለ ጽናት አይሳኩም። ከእኛ በፊት ዐመጻውን በትዕግሥት የመከቱ ተሻግረዋል፤ ሑካታውን በጽናት ያለፉ አሳክተዋል። ብንመኝም ፈተናውን አናስቀርም፤ መጽናት ግን እንችላለን። ከድህነት መውጫው ብርታታችን፣ ወደ ዴሞክራሲ መድረሻችው ትዕግሥታችን እንደሆነ አምነን ለኢትዮጵያ ትንሣኤ በሙሉ ልባችን እንትጋ!!
በድጋሚ መልካም የትንሣኤ በዓል ይሁንልን።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ሚያዝያ 03 ቀን 2018 ዓ.ም
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
09/04/2026
"ተረጂነትን በራስ አቅም መተካት የሉዓላዊነትና የክብር መገለጫ ነው" ወይዘሮ ዘለቃሽ ባህሩ
🇪🇹 ሚያዝያ 1/2018 ዓ.ም 🇪🇹
ኢትዮጵያ በታሪኳ ለዜጎች የሚቀርብ ሰብአዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈንና የውጭ ዕርዳታ ጥገኝነትን ለመቀነስ የሚያስችሉ ጠንካራ እርምጃዎችን እየወሰደች ትገኛለች።
መንግሥት "ተረጂነትን በራስ አቅም መተካት" የሚለውን ሀገራዊ ጥሪ ይፋ ማድረጉን ተከትሎ የፌዴራልና የክልል ተቋማት ይህንን ዓላማ ከግብ ለማድረስ የየራሳቸውን ድርሻ እንዲወጡ አቅጣጫ ተቀምጧል።
ይህም ዜጎች በችግር ጊዜ እርስ በርስ የሚደጋገፉበትን ባህል ከማሳደጉ ባለፈ ሀገራዊ ሉዓላዊነትን በኢኮኖሚ ነፃነት ለማረጋገጥ የሚደረግ ትልቅ እንቅስቃሴ ነው።
የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮም ይህንን ሀገራዊ ጥሪና የብሔራዊ የአደጋ ስጋት ፖሊሲን ውጤታማ ለማድረግ የአደጋ ስጋት ምክር ቤት አባል በመሆን በንቃት እየተሳተፈ ይገኛል።
ቢሮው በተሰጠው ኃላፊነት መሠረት የፋይናንስ ዘላቂነትን ለማስፈንና ሰብአዊ ድጋፍን በሀገር ውስጥ አቅም ለመሸፈን የሚያስችሉ ተግባራትን በአመራሩና በሠራተኛው አማካኝነት እያከናወነ ይገኛል።
የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ዘለቃሽ ባህሩ እንደገለጹት ቢሮው ተረጂነትን ዜሮ ለማድረግ የተቀመጠውን ሀገራዊ አቅጣጫ ለመተግበር የሠራተኛውን ተሳትፎ መሠረት ያደረገ ንቅናቄ እያደረገ ነው።
ኃላፊዋ አክለውም ይሄው የሰብአዊ ድጋፍ ሥራ በዘፈቀደ የሚከናወን ሳይሆን በሀገር ደረጃ በራስ አቅም ሰብአዊ ድጋፍን ለማረጋገጥ ተዘጋጅቶ በጸደቀው ደንብ ቁጥር 191/2017 መሠረት ተቋሙ የአደጋ ስጋት ምክር ቤት አባል በመሆኑ የተጣለበትን ኃላፊነት እየተወጣ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
በዚሁ ሕጋዊ ማዕቀፍና በተሰጠው አቅጣጫ መሠረት በቢሮው የሚገኙ 240 የሚጠጉ ሠራተኞችና 7 የሥራ አመራሮች ለወገኔ ደራሽ እኔው ነኝ በሚል መንፈስ ከተጣራ ደመወዛቸው ላይ 0.5 በመቶ በፈቃደኝነት እንዲቆረጥ በማድረግ በየወሩ አስተዋጽኦ እያደረጉ ይገኛሉ።
ይህ የሠራተኞች ቁርጠኝነት በ2018 በጀት ዓመት ለሥራ ማስኬጃ ከተመደበው በጀት ከተቀነሰው አንድ በመቶ ጋር ተዳምሮ ከጥር አንድ 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን ባለው ሂደት በአጠቃላይ አንድ ሚሊዮን 489 ሺ 722 ብር በላይ ለሰብአዊ ድጋፍ ማሰባሰብ ተችሏል።
ይህም ቢሮው "እኔ ለወገኔ ምን አደረግኩ?" የሚለውን የዜግነት ግዴታ ከሕጋዊ ኃላፊነት ጋር በማቀናጀት የተወጣበት ተግባር መሆኑን ኃላፊዋ አብራርተዋል።
እንደ ወይዘሮ ዘለቃሽ ገለጻ ይህ ንቅናቄ ከገንዘብ ድጋፉ ባለፈ ትልቅ የሞራልና የክብር ትርጉም አለው። "ልመናና ተረጂነት ክብርን የሚያሳጣና ነው" ያሉት ኃላፊዋ በተለይም ምግብን መለመን ትልቅ ውርደት መሆኑንና ኢትዮጵያ ያላትን ሰፊ የተፈጥሮ ጸጋና ወጣት የሰው ኃይል ተጠቅማ ይህንን ታሪክ መቀየር እንዳለባት አሳስበዋል።
ሠራተኛውና አመራሩ ይህንን የተቀደሰ ዓላማ ተረድቶ ካለው ውስን ገቢ ላይ በደስታና በፈቃደኝነት ድጋፍ ማድረጉ ለሥራው ስኬታማነትና ለተረጂነት አስተሳሰብ መክሰም ትልቅ መሠረት ሆኗል።
ቢሮው በቀጣይም ተቋማዊ ተልዕኮውን ከማሳካት ባሻገር መሰል ማህበራዊና ሰብአዊ ኃላፊነቶችን የመወጣት ሥራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
በተቋሙ የተጀመረው ይህ የተቀናጀ የድጋፍ አሰባሰብ ሂደት፣ ሌሎች ተቋማትም የራሳቸውን አሻራ እንዲያሳርፉና ተረጂነትን በራስ አቅም ለመተካት የሚደረገውን ሀገራዊ ጥረት እንዲያግዙ ጥሪ ቀርቧል።
ባጠቃላይ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ አመራሮችና ሠራተኞች ያሳዩት ቁርጠኝነት ተረጂነትን በዘላቂነት ለመቅረፍ የሚደረገው ጉዞ በጠንካራ መሠረት ላይ መሆኑን ያሳያል።
በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተው የደመወዝ መዋጮና የመንግሥት በጀትን ለሰብአዊ ዓላማ የማዋል ልምድ የዜጎችን እርስ በርስ የመረዳዳት እሴት ከማጎልበት ባለፈ ለሀገር ሉዓላዊነት መጠናከር ትልቅ አምድ ነው።
ይህ ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ በመቀጠል ኢትዮጵያን ከዕርዳታ ጠባቂነት ወደ ራስ መቻል የምታደርገውን ሽግግር እንደሚያፋጥነው ይታመናል።
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
👉 Tiktok
https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8y9L28EOubG&_r=1
👉Facebook
https://www.facebook.com/addisababatvetbureau
👉Telegram
https://t.me/AABOLS
👉YouTube
https://youtube.com/?si=t9ZklwKzGx9rRyXf
👉website
https://aabols.gov.et
👉ለቅሬታ፣ አስተያየትና ጥቆማ
https://complain.aabols.gov.et
👉ለነፃ የስልክ ጥሪ
6524
08/04/2026
"በ2022 በድጅታል የበለፀገ ብቁና ተወዳዳሪ ለመሆን እየተጋ የሚገኝ አንጋፋው ኮሌጃችን ተግባረዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ራዕዩን በማሳካት ላይ ይገኛል ።"
Click here to claim your Sponsored Listing.
Location
Category
Contact the school
Telephone
Website
Address
Mexico Square
Addis Ababa
251
Opening Hours
| Monday | 02:30 - 23:30 |
| Tuesday | 02:30 - 23:30 |
| Wednesday | 02:30 - 23:30 |
| Thursday | 02:30 - 23:30 |
| Friday | 02:30 - 23:30 |