26/02/2026
የትምህርት አስፈላጊነትና ግብን በተመለከተ የነእፓ ፕሮግራም በአጭሩ እንደሚከተለው ተቀምጧል።
የሰለጠነ የሰው ኃይል ለአገር ኢኮኖሚ (ግብርና፣ ኢንዱስትሪና አገልግሎት) መሠረት በመሆኑ ዜጎች በየደረጃቸው ስልጠና እንዲያገኙ ማድረግ
ትምህርት ዜጎች ሰብአዊ መብታቸውን እንዲያውቁ፣ ለሕግ የበላይነት እንዲገዙ እና በሥነ-ምግባር የታነጹ እንዲሆኑ በማድረግ በየጊዜው መንግስት ለይ ጥያቄ የሚያነሳ ቡድን ወደ ጨካ እንዳይገባ ለመከላከል የሚያስችል ይሆናል።
ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ፣ የኢትዮጵያን ታሪክና ባህላዊ እሴቶች ያገናዘበና አካታች የትምህርት ፖሊሲ ይቀረጻል።
2. ዋና ዋና የትግበራ አቅጣጫዎች
ዋና ዋና ተግባራት
ተወዳዳሪ ትውልድ መፍጠር፦
ወቅታዊ ዕድሎችን መጠቀም የሚችልና በምክንያታዊነት ላይ የተመሰረተ የትምህርት ሥርዓት መዘርጋት።
ጥራትና ተደራሽነት፦
የትምህርት ሥርዓቱን ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተወዳዳሪነት ማሳደግ።
የደረጃዎች ማሻሻያ፦
ከቅድመ መደበኛ እስከ ከፍተኛ ትምህርት እንዲሁም የቴክኒክና ሙያ ትምህርትን አሰጣጥ ማሻሻል።
ከኢኮኖሚ ጋር ማስተሳሰር፦
ከፍተኛ ትምህርት ከአገሪቱ ምጣኔ ሀብታዊ ዕድገትና ፍላጎት ጋር በተጣጣመ መልኩ እንዲቀረጽ ማድረግ።
ለመምህራን ትኩረት መስጠት፦
መምህራን በህብረተሰቡ ዘንድ የሚገባቸውን ክብር እንዲያገኙ ልዩ ድጋፍና ማበረታቻ ማድረግና መምህርነት የሚገባውን ክብር በማግኘት ዜጎች መርጠው መምህር እንዲሆኑ በሚያስችል መልኩ የመምህራንን ደምወዝ እና ጥቅማ ጥቅም ከፍ ማድረግ
የሥነ-ዜጋ ትምህርት፦
የሥነ-ምግባርና የዜግነት ትምህርት ከመደበኛው ትምህርት ጋር ተቀናጅቶ እንዲሰጥና በተለያዩ የስልጠና መድረኮች ለዜጎች በማዳረስ ዜጎች መብትና ግዴታቸውን እንዲያውቁ ማድረግ።
3. ልዩ ትኩረት የሚሰጣቸው ጉዳዮች
STEM፦ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና ሂሳብ (STEM) ትምህርቶች ልዩ ትኩረት ይሰጣቸዋል።
መሠረታዊ ትምህርት፦
ዜጎች ቢያንስ የዐሥር ዓመት መሠረታዊ ትምህርት እንዲያገኙ የመንግሥትና የቤተሰብ ግዴታ እንዲሆን ማድረግ።
ቴክኖሎጂ፦
ትምህርትን በቴክኖሎጂ የታገዘና ዘመናዊ ማድረግ።የትምህርት አስፈላጊነትና ግብን በተመለከተ የነእፓ ፕሮግራም በአጭሩ እንደሚከተለው ተቀምጧል።
የሰለጠነ የሰው ኃይል ለአገር ኢኮኖሚ (ግብርና፣ ኢንዱስትሪና አገልግሎት) መሠረት በመሆኑ ዜጎች በየደረጃቸው ስልጠና እንዲያገኙ ማድረግ
ትምህርት ዜጎች ሰብአዊ መብታቸውን እንዲያውቁ፣ ለሕግ የበላይነት እንዲገዙ እና በሥነ-ምግባር የታነጹ እንዲሆኑ በማድረግ በየጊዜው መንግስት ለይ ጥያቄ የሚያነሳ ቡድን ወደ ጨካ እንዳይገባ ለመከላከል የሚያስችል ይሆናል።
ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ፣ የኢትዮጵያን ታሪክና ባህላዊ እሴቶች ያገናዘበና አካታች የትምህርት ፖሊሲ ይቀረጻል።
2. ዋና ዋና የትግበራ አቅጣጫዎች
ዋና ዋና ተግባራት
ተወዳዳሪ ትውልድ መፍጠር፦
ወቅታዊ ዕድሎችን መጠቀም የሚችልና በምክንያታዊነት ላይ የተመሰረተ የትምህርት ሥርዓት መዘርጋት።
ጥራትና ተደራሽነት፦
የትምህርት ሥርዓቱን ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተወዳዳሪነት ማሳደግ።
የደረጃዎች ማሻሻያ፦
ከቅድመ መደበኛ እስከ ከፍተኛ ትምህርት እንዲሁም የቴክኒክና ሙያ ትምህርትን አሰጣጥ ማሻሻል።
ከኢኮኖሚ ጋር ማስተሳሰር፦
ከፍተኛ ትምህርት ከአገሪቱ ምጣኔ ሀብታዊ ዕድገትና ፍላጎት ጋር በተጣጣመ መልኩ እንዲቀረጽ ማድረግ።
ለመምህራን ትኩረት መስጠት፦
መምህራን በህብረተሰቡ ዘንድ የሚገባቸውን ክብር እንዲያገኙ ልዩ ድጋፍና ማበረታቻ ማድረግና መምህርነት...
03/02/2026
ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስትራቴጂውን ይፋ አደረገ!!
!!
በመርሀ ግብሩ ላይ የመክፈቻ መልእክት ያስተላለፉት የፓርቲው የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ሲሳይ ነጋሽ በግንቦት ወር 2018 ይካሄዳል ተብሎ በሚጠበቀው 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ውጤታማ ለመሆን ነእፓ ከፍተኛ ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆኑን ገልጸው፣ ለምርጫው የሚያስፈልጉ ዝግጅቶችን በተቀናጀ መልኩ ለማከናወን "የምርጫ ስትራቴጂው" መዘጋጅቱን አመልክተዋል።
አቶ ሲሳይ የምርጫ ስትራቴጂው ዋና ዓላማ ነእፓ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በክልል ምክር ቤቶች በቂ ወንበር እንዲያሸንፍ ማስቻል መሆኑን ገልጸዋል።
አቶ ሲሳይ የምርጫ ስትራቴጂው በርካታ ጉዳዮችን ታሳቢ አድርጎ የተዘጋጀ እንደሆነ ጠቅሰው፣ በሀገራችን የተለያዩ አካባቢዎች የቀጠለው የእርስ በእርስ ግጭት፣ በዜጎች ላይ የሚፈጸሙ ኢ-ሰብአዊ በደሎች፣ የመንግስት ተቋማት ብልሹ አሰራር፣ ሙስና፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጠበበ የመጣው የፖለቲካ ምህዳር፣ ልጓም ያጣው የዋጋ ንረት፣ ኑሮ ውድነት፣ ስራ አጥነት፣ የሀገራችን የማክሮ ኢኮኖሚ መዛነፍ፣ የዲፕሎማሲ እና የውጭ ግንኙነት እንዲሁም በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል እየተባባሰ የመጣው የጦርነት ስጋት እና ሌሎች ቁልፍ ሀገራዊ ጉዳዮች ታሳቢ መደረጋቸውን አውስተዋል።
ስትራቴጂው ከላይ ከተዘረዘሩ ሀገራዊ ጉዳዮች ጎን ለጎን፣ የነእፓ አባላት እና መላ ኢትዮጵያውያን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ ያላቸውን አስተያየት፣ ግንዛቤ፣ ስጋት እና ተስፋ ከግምት ውስጥ ያስገባ ይሆን ዘንድ የህዝብ አስተያየት መሰብሰቢያ የዳሰሳ ጥናት በማካሄድ፣ የጥናቱ ግኝት በሰነዱ ውስጥ እንዲካተት የተደረገ መሆኑን እና፣ ከምርጫ በፊት፣ በምርጫ ወቅት እና ከምርጫ በኃላ የሚከናወኑ ተግባራት በዝርዝር መካተታቸውን ኃላፊው አመልክተዋል።
የምርጫ ስትራቴጂውን በተሳካ ሁኔታ ተግባራዊ ለማድረግ ከፍተኛ የገንዘብ፣ የሰው ኃይል፣ የሎጂስቲክስ፣ የቁሳቁስ እና የቴክኖሎጂ ግብአት እንደሚያስፈልግ የገለጹት አቶ ሲሳይ፣ እነዚህን ግብአቶች በተለይም ከአባላት እና ደጋፊዎች ለማሰባሰብ ከፍተኛ ጥረት ማድረግ እንደሚያስፈልግ አመልክተው፣ በተለያየ ደረጃ የሚገኙ የፓርቲው አመራሮች፣ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር የሚገኙ አባላት፣ የፓርቲው ልዩ ልዩ አደረጃጀቶች እና የስራ ክፍሎች የምርጫ ስትራቴጂውን መሰረት በማድረግ፣ ነእፓ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤታማ ይሆን ዘንድ አስፈላጊውን እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
በመቀጠል የነእፓ የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ነቢሀ መሀመድ የምርጫ ስትራቴጂውን ዝርዝር ለመድረኩ አቅርበዋል። ወ/ሮ ነቢሀ ስትራቴጂው አራት ክፍሎች እና 50 ገጾች ያሉት ሰፊ ሰነድ መሆኑን ገልጸው፣ የሰነዱን ዋና ዋና ይዘቶች ለታዳሚዎች አብራርተዋል።
ወ/ሮ ነቢሀ የምርጫ ስትራቴጂው ጥልቅ ድርጅታዊ እና ሀገራዊ ትንተና በማካሄድ የሚነሳ መሆኑን አመልክተው ድርጅታዊ ጠንካራ ጎኖች (Strengths)፣ ውስንነቶች (Limitations)፣ መልካም አጋጣሚዎች (Opportunities) እና ስጋቶች (Threats) “SLOT” በመባል በሚታወቀው የትንተና ዘዴ እንዲሁም ሀገራዊ ሁኔታዎች ትንታኔ በ “PESTEL” የትንተና ስልት መዘጋጀታቸውን ጠቅሰዋል። በሀገራዊ ትንተናው ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ፣ የቴክኖሎጂ፣ አካባቢያዊ እንዲሁም የምርጫ ህግ ማእቀፎች እና ተያያዥ አስተዳደራዊ ጉዳዮች እንደተዳሰሱ ወ/ሮ ነቢሀ ገልጸዋል።
በፖለቲካ ጉዳዮች ትንተና ከተዳሰሱ ጉዳዮች መካከል በሀገራችን የሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች ቁመና ሲሆን፣ በዚህ ክፍል በተለይ የገዢው ፓርቲ አሁናዊ ሁኔታ በስፋት መዳሰሱ ተመልክቷል። ነእፓ በምርጫ ቅስቀሳቅ ወቅት የተፎካካሪ ፓርቲዎችን ጠንካራ እና ደካማ ጎኖች ታሳቢ ያደረገ የምርጫ ቅስቀሳ እንደሚያደርግ ተገልጿል።
ነእፓ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ 100 የፓርላማ ወንበር እና በክልሎች በድምሩ 200 ወንበር ለማሸነፍ እንደሚሰራ ያስታወቁት ወ/ሮ ነቢሀ እነዚህን ግቦች ለማሳካት ፓርቲው የሚከተላቸውን አስር ልዩ ልዩ የምርጫ ቅስቀሳ ስልቶች በዝርዝር ያስረዱ ሲሆን፣ ከምርጫ ስትራቴጂው በተጨማሪ ነእፓ የእጩ ምልመላ እና የምርጫ ስነምግባር መመሪያ ማዘጋጀቱን አመልክተዋል።
ወ/ሮ ነቢሀ ከተለመደው “የምርጫ ማኒፌስቶ” ውጪ “የምርጫ ስትራቴጂ” አዘጋጅቶ በምርጫ መሳተፍ በሀገራችን ያልተለመደ መሆኑን ጠቅሰው፣ የምርጫ ስትራቴጂ አንድ የፖለቲካ ፓርቲ በምርጫ የሚሳተፍባቸውን ስልቶች እና ማሳካት የሚሻቸውን ግቦች ለአባላት፣ ለደጋፊዎች እና በአጠቃላይ ለዜጎች (ለመራጮች) ለማስረዳት እጅግ አስፈላጊ ሰነድ መሆኑን ገልጸዋል።
ወ/ሮ ነቢሀ ከጥቂት ሳምንታት በኃላ የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ የ7ኛ ጠቅላላ ምርጫ “ማኒፊስቶ” ለህዝብ ይፋ እንደሚሆን በመግለጽ መልእክታቸውን አሳርገዋል።
የምርጫ ስትራቴጂውን መግለጫ/ማብራሪያ በማስከተል የፓርቲው ሊቀመንበር እና የብሄራዊ ምርጫ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት ከጋዜጠኞች ለተነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያ እና ምልሽ ሰጥተዋል።
በፕረስ ኮንፈረንሱ ላይ የነእፓ አባላት፣ የፓርቲው የክልል እና የብሄራዊ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና ልዩ ልዩ የሚዲያ ተቋማት ተገኝተዋል።
ብዕር ያሸንፋል
ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ
ጥር 26፣ 2018
24/01/2026
ነእፓ የምርጫ ስትራቴጂ
********************
ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያዘጋጀው የምርጫ ስትራቴጂ ሰነድ በቅርቡ ይፋ ይደረጋል።
ሰነዱ በ7ኛው ጠቅላላ የነእፓን የምርጫ ተሳትፎ ሂደት፣ የምርጫ ቅስቀሳ ስልቶች፣ የሁኔታዎች ትንተና፣ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በክልል ምክር ቤቶች ለማሸነፍ ያቀደው ግብ እና ሌሎች ከምርጫው ጋር የተያያዙ ዝርዝር ተግባራት እና ግቦችን አካቷል።
የምርጫ ስትራቴጂው በቅርቡ በሚዘጋጀው የፕረንስ ኮንፈረስ ይፋ ይሆናል።
ስለ ስትራቴጂው ይዘት በቀጣይ ተጨማሪ መረጃ እንሰጣለን።
መጪው ዘመን የነጻነት እና የእኩልነት ነው።
ብዕር በእርግጥም ያሸንፋል
ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ
ብሄራዊ ምርጫ አስተባባሪ ኮሚቴ
28/12/2025
የማሀበራዊ ዘርፍ ተሳተፎ
ታህሳስ 19/ 2018
ጦራ
በዛሬው እላት የላንፉሮ ምርጫ ክልል የነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ፅ/ቤት አመራርና አባላት ከሰባት አመት በላይ ተሞ ቤት የቀረውን መምህር መሀመድ ሱሩርን በመዘየርና ሞተር ለመግዛት በፓርቲው አባላት 5000 አካውንት ገቢ አድርገዋል። ፓርቲው ከፖለቲካዊ ተሳትፎ ባሻገር በማህበራዊ ዘርፉም ተሳትፎ በማድረግ የታመሙትን በመጠያቅ ፣ ደም በመለገስ፣ ለተቸገሩት በመድረስ ስራ የሚሳተፍ ህዝባዊ ፓርቲ ነው።
28/12/2025
ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ እጩ ምልመላ እና ምዝገባ ሂደት
1 ቅድመ እጩ አመልካቾች ማሟላት የሚገባቸው
1.1 ቅድመ እጩ ማሟላት የሚገባቸው ግዴታዎች
የቅድመ እጩ አመልካቾች የሚከተሉትን መመዘኛዎች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል፣
› ዜግነት ኢትዮጲያዊ፣
› በምዝገባ ዕለት እድሜ 21 ዓመት ወይም ከዚያ በላይ መሆን፣
› በህግ ወይም በፍርድ ቤት የመምረጥና የመመረጥ መብት አለመገፈፍ፣
› የአባልነት መዋጮ እና ሌሎች የአባልነት ግዴታዎችን መወጣት፣
› በፓርቲው ውስጥ በዲሲፕሊን ጉዳይ የጥፋተኝነት ውሳኔ ያልተወሰነበት፣
› በሚወዳደሩበት የምርጫ ክልል የተወለዱ፣ ወይም በምርጫ ክልሉ ውስጥ ቢያንስ አንድ ዓመት የኖሩ ወይም ለሁለት ዓመት የሰሩ፣
› ዳኛ፣ ዓቃቤ ሕግ፣ የመከላከያ ሰራዊት፣ ፖሊስ እና የጸጥታ ሃይል አባል፣ የደህንነት ሰራተኛ፣ እና የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰራተኛ የሆነ/የሆነች በቅድመ እጩነት ለመመዝገብ ካሉበት ኃላፊነት መልቀቅ።
1.2 ተጨማሪ መስፈርቶች
ቅድመ እጩ አመልካቾች የሚከተሉት የግል እና ማህበራዊ ብቃቶች ቢኖሯቸው ይመረጣል፣
• የፓርቲውን ዓላማ ከግብ ለማድረስ በቁርጠኘነት መታገል፣
• ማህበረሰብን በሚጠቅሙ ልዩ ልዩ እንቅስቃሴዎች በንቃት መሳተፍ፣
• በህዝብ ዘንድ ተቀባይነትና ተደማጭነት መኖር፣ በትጋት እና ታታሪነት መታወቅ፣
• ለምርጫ ቅስቀሳ የሚያስፈልገውን ወጪ በሙሉ ወይም በከፊል መሸፈን እንዲሁም ታዛቢዎች መመደብ መቻል፣
• የብሄር፣ የኃይማኖት፣ የጾታ ብዝሀነትን ማክበር፣ በውይይት ማመን፣ የሌሎችን ሀሳብ ማክበር፣ የማስተባበር፣ የመምራት አቅምና ችሎታ።
ማስታወሻ፡ አመልካቾች ከላይ የተዘረዘሩ የግል ብቃት እና ማህበራዊ ተሳትፎ ለማረጋገጥ ከተለያዩ አካላት ያገኙትን የተሳትፎ ወይም የእውቅና የምስክር ወረቀት ከቅድመ እጩ ማመልከቻ ጋር አባሪ አድርገው ሊያቀርቡ ይችላሉ።
2 ማህበራዊ ድጋፍን በተግባር ስለማሳየት
ቅድመ እጩ አመልካቾች ፓርቲውን ወክሎ በእጩነት ቢቀርቡ ማህበራዊ መሰረት እንዳላቸው ለማሳየት፣ ለምርጫ ቅስቀሳ እና ለምርጫ ታዛቢነት በቂ የሰው ኃይል እንዳላቸው ለማረጋገጥ የሚከተሉትን ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።
1. ፡ ቅድመ እጩ አመልካቾች በሚወዳደሩበት አካባቢ ያላቸውን ቅቡልነት እና ድጋፍ ለማሳየት አዲስ የነእፓ አባላት ማፍራት ይኖርባቸዋል። በዚሁ መሰረት ቅድመ እጩ አመልካቾች እጩ ሆነው ቢመረጡ፡ 1) የተወካዮች ምክር ቤት አመልካቾች ቢያንስ አስር አባላት፣ የክልል ምክር ቤት አመልካቾች ቢያንስ አምስት አባላት ለማፍራት መስማማት ይኖርባቸዋል።
2. ፡ ቅድመ እጩ አመልካቾች እጩ ሆነው ቢመረጡ በምርጫ ቅስቀሳ ሊሳተፉ የሚችሉ እና በምርጫ ቀን በአንድ ምርጫ ጣቢያ ቢያንስ ሁለት ታዛቢ ማቅረብ እንደሚችሉ ማረጋገጥ አለባቸው። በዚሁ መሰረት የህዝብ ተወካዮችም ሆነ የክልል ምክር ቤት ቅድመ እጩ አመልካቾች በምርጫ ቅስቀሳ እና በታዛቢነት ሊሰሩ የሚችሉ ቢያንስ 25 ሰዎች ዝርዝር እና መረጃ ለማቅረብ መስማማት ይኖርባቸዋል።
3 ብዝሀነት እና አካታችነትን ታሳቢ ያደረገ የእጩ ምልመላ
ኢትዮጵያ የተለያዩ ማንነቶች ያሉባት፣ ብዝሀ ባህል፣ ብዝሀ እምነት፣ ብዝሀ ቋንቋ ሀገር ነች። አካታችነት የነእፓ ድርጅታዊ መርህዎ ነው። ይህንኑ መሰረት በማድረግ የፓርቲው የእጩ ምልመላ ሂደት የኃይማኖት፣ የቋንቋ፣ የባህል ወዘተ ብዝሀነትን ያከበረ ይሆናል። ሴት፣ ወጣት እና አካል ጉዳተኛ ቅድመ እጩ አመልካቾች ቅድሚያ ይሰጣቸዋል።
4 የትምህርት ደረጃ
እጅግ ፈጣን፣ ተለዋዋጭ እና ውስብስብ በሆነው የ21ኛው ክፍለ ዘመን አካባቢያዊ፣ ክልላዊ፣ ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎችን በቅጡ ለመረዳት፣ የመፍትሄ ሀሳቦችን ለማመንጨት እና በፖሊሲ ቀረጻ ሂደት በንቃት ለመሳተፍ በቂ የትምህርት ዝግጅት እና በተግባር የተፈተነ የስራ እና የህይወት ተሞክሮ ያስፈልጋል። በዚሁ መሰረት ቅድመ እጩ አመልካቶች ቢያንስ የመጀመሪያ ዲግሪ ቢኖራቸው ይመረጣል። ይሁን እንጂ ይህንን የትምህርት ደረጃ ማሟላት የማይችሉ ነገር ግን በሌሎች መመዘኛዎች ብቁ ተወዳዳሪ የሆኑ እጩዎች በልዩ ሁኔታ ይስተናገዳሉ።
5 ዜጎች እጩዎቻቸውን እንዲመርጡ እድል ስለመስጠት
ነእፓ የተሻለ የህዝብ ተቀባይነት እና አቅም ያላቸውን እጩዎች ማቅረብ ይችል ዘንድ ዜጎች እጩዎቻቸውን እንዲጠቁሙ እድል ይሰጣል። ዜጎች እጩዎቻቸውን እንዲጠቁሙ እድል መስጠት፣ የተሻለ አቅም እና የህዝብ ተቀባይነት ያላቸውን እጩዎች ከማግኘት ባሻገር፣ ዜጎች በምርጫው ሂደት በንቃት እንዲሳተፉ እና የሂደቱ ባለቤት እንዲሆኑ ያደርጋል። በዚህ መሰረት ታዋቂ ግለሰቦች፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን፣ ተመራማሪዎች፣ የማህበረሰብ አንቂዎች፣ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ የንግድ ማህበረሰብ አባላት፣ ማህበራዊ ተቋማት መሪዎች፣ የጤና ባለሙያዎች፣ የኃይማኖት መምህራን ወይም በሌሎች መስኮች ተጽእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ሊጠቆሙ ይችላሉ። ነእፓ ዜጎች እጩዎቻቸውን እንዲጠቁሙ ይፋዊ ጥሪ ያቀርባል።
6 የቅድመ እጩ ምዝገባ ክፍያ
በቅድመ እጩነት መመዝገብ የሚሹ አመልካቾች የማይመለስ የቅድመ እጩ ምዝገባ ክፍያ መፈጸም ይጠበቅባቸዋል። የቅድመ እጩ ምዝገባ ክፍያ ፓርቲው ከምርጫ ጋር በተያያዘ ለሚያወጣው ወጪ የሚውል ይሆናል። የቅድመ እጩ ምዝገባ ክፍያ መጠን አካባቢ ሁኔታን ታሳቢ በማድረግ በነእፓ የክልል ቅርንጫፎች ይወሰናል።
ምንጫ፡ ነእፓ እጩ ምልመላ መመሪያ ቁጥር 045/2018
ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ
ታህሳስ 2018
15/12/2025
ነእፓ አፓረንትሽፕ ፕሮግራም (FEP apprenticeship programs)
በፖለቲካ ሳይንስ እና ተቀራራቢ የትምህር ዘርፎች የመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርታቸውን በማጠናቀቅ ላይ ለሚገኙ ተማሪዎች።
15/12/2025
የነእፓ ድርጅታዊ መርሆዎች
1. የሀገርን እና የህዝብ ሰላምና ደህንነት መጠበቅ፣ በህዝቦች መካከል ሰላማዊ ግንኙነት እንዲኖር የድርሻን መወጣት
2. ማንኛውም የፓርቲው እንቅስቃሴ ለሰላማዊ የትግል ስልት ተገዢ መሆኑን ማረጋገጥ
3. የግለሰብ እና የቡድን መብቶችን እንዲሁም የብሄር፣ የቋንቋ፣ የአመለካከት፣ የኃይማኖት ወዘተ ብዝሃነትን ማክበር
4. ለህግ የበላይነት መገዛት፣ የፓርቲውን መተዳደሪያ ደንብ እና ሌሎች መመሪያዎችን ማክበር እና እንዲከበሩ ማድረግ
5. ውስጠ ድርጅት ዴሞክራሲን ማስፈን፣ ኃላፊነትን በግልጽነት እና ተጠያቂነት መወጣት
6. የፓርቲው አባላት እና አመራሮች በአመለካከትም ሆነ በተግባር ሚዛናዊ እና ምክንያታዊ መሆን
7. በፓርቲው ውስጥ ሃሳብን በነፃነት የማንሸራሸር መብት እንደተጠበቀ ሆኖ ለብዙሃን ውሳኔ ተገዥ መሆን
8. በፓርቲው ውስጥ በሚደረጉ ውይይቶች በተጨባጭ መረጃ ላይ የተመሰረተ አቋም ማራመድ
9. የፓርቲውን የበላይ አካላት ውሳኔዎች ማክበር
10. በፓርቲው ውስጥ በተለያየ ደረጃ የሚሰጡ ኃላፊነቶች ብቃትን መሰረት ያደረጉ እንዲሆኑ ማድረግ።
ምንጭ፡
ነእፓ መተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ 4
04/12/2025
የምርጫ ምልክታችን!!
*****************
በኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ጥያቄ መሰረት ነእፓ የ7ኛ ጠቅላላ ምርጫ የምርጫ ምልክቱን ለቦርዱ አሳውቋል።
ብዕር!!
የእውቀት፣ የጥበብ፣ የብርሀን ምልክቱ፣
የስልጣኔ መሰረቱ፣
ብዕር የነእፓ መለያ ሆኖ ቀጥሏል።
ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ
ህዳር 2018
01/10/2025
ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ የስልጤ ዞን ቅርንጫፍ በሀገራችን እግር ኳስ ባለታሪክ የነበረው ወንድማችን ሳዳት ጀማል ህልፈት የተሰማውን እጅግ ጥልቅ ሀዘን ገለፀ
==================================
ወንድም ሳዳት ጀማል በኢትዮጵያ እግር ኳስ ባለታሪክ ነው። በተለይም ብሔራዊ ቡድናችንን በግብ ጠባቂነት; በሴቶች ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝነት እና በስልጤ ዞን የታዳጊዎች እግር ኳስ ፕሮጀክት (ሳዳትና ከማል የታዳጊዎች ፕሮጀክት) ከወንድም ከማል አህመድ ጋር በመተባበር መስርቶ ማሰልጠን ሀገሩን ያገለገለባቸው ጥቂት አብነቶች ናቸው። በተለያዩ ጥልፍልፍ የፖለቲካ ችግሮች ምክንያት በሁለት እግሩ ቆሞ መሄድ ባቃተው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ የነበሩትን ጥልፍልፍ ችግሮች ተቋቁመው አሻራቸውን ካሳረፉ ዜጎቻችን አንዱ በነበረው ወንድማችን ሞት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለፅን ለቤተሰቦቹ ለወዳጅ ዘመዶቹና ለመላው የሀገራችን ህዝብ ባጠቃላይ እንዲሁም ለእግር ኳስ ቤተሰቡ በተለይ መፅናናትን; ለወንድማችን ዘላለማዊ የሰላም ረፍትን (ጀነትን) እንመኛለን!!
20/09/2025
የወራቤ ከተማችን ከፍታ የሁላችንም ከፍታ ነውና ለዕድገቷ የሁላችንም ርብርብ ይገባታል። ህዝባችን የሚመራው ታማኝና እውነተኛ መሪ ካገኘ ተዓምር መስራት እንደሚችል በተደጋጋሚ አሳይቷል። የዛሬውም የዚሁ ነፀብራቅ ነው።
15/09/2025
የሀገራችን ኩራትና ብሔራዊ ኃብታችን የሆናችሁት ብርቅዬዎቹ የሀይረንዚ ልዩ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ልጆቻችን በ2017 ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ያስመዘገባችሁት ውጤት በእናንተና በታታሪ መምህራኑ እንዲሁም በት/ቤቱ የመማር ማስተማር አመራርነት (Instructional leadership) ብቃት ከነበረን መተማመን አኳያ የሚገርመን ባይሆንም እንደተለመደው ሀገራችንንና ህዝባችንን ከፍ ስላደረጋችሁ አላህ ከፍ ያድርጋችሁ ብሎ መመረቅ እና የደስታ መግለጫና ምስጋና ስለሚገባችሁ እንኳን ደስ ኣላችሁ!!!; እንኳን ደስ ኣለን!!!❤️❤️❤️
በዚህ አጋጣሚ በሀገራችን የትምህርት ስርዓት ላይ ከፖሊሲና ቀረፃና ስትራተጂ ዕይታ ጀምሮ ያለው ዘርፈ ብዙና እጅግ ውስብስብ የሆነ አሳሳቢ የትምህርት ጥራት ችግሮች መፍትሄ ትምህርት መር ብሔራዊ ስትራቴጂን በአማራጭነት እንዲታይም እናሳስባለን!!!