02/06/2026
#ባሉበት፤
--------------------------------------
በunified መሶብ አማካኝነት በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን በተመለከተ ዝርዝር ገለጻና እና ውይይት ለማድረግ እቅድ ተይዟል።
ስለሆነም በዚህ አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ የሚደረገው ገለጻ እና ውይይት ላይ የተቋሙ የበላይ ኃላፊ እና ሬጅስትራር ኃላፊ አርብ፣ ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጠዋት 3:00 ሰዓት በትምህርት ሚኒስቴር መሰብሰቢያ አዳራሽ እንድትገኙ በጥብቅ እያሳወቅን ስብሰባው ላይ መገኘት የማይችሉ ሀላፊዎች ተወካይ መላክ እንዳለባቸው እናሳስባለን፡፡
የኢፊዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት Www. neta.gov.et ይከታተሉ::
29/05/2026
የፀና ቃል፤ የላቀ እመርታ!”በትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ እና የአቻ ግመታ ዘርፍ የተገኙ ስኬቶች
--------------------------------------------------------------------------------------
** የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ እና የአቻ ግመታ መመሪያ፤
** ስታንዳርዶች፤
** ጋይድላይኖች እና
** ቼክሌስቶች
** ከውጭ ሀገር ለተገኙ የትምህርት ማስረጃዎች የአቻ ግመታ፤
** ከሀገር ውጥ የተገኙ የትምህርት ማስረጃዎችን ትክክለኛነት ማረጋገጥ፤
** ደረጃ መስጠት፣ የኮርስ ለኮርስ ግምገማ ማከናወን እና የውጤት ቅየራ (Grade conversion) አገልግሎት፤
** የፕሮግራም አግባብነትን በማረጋገጥ፤እና
** የትምህርት ማስረጃ አቻ ግመታ እና ማረጋገጫ አገልግሎትን ዲጂታላይዝ ማድረግ፡፡
** የቀረበ የትምህርት ማስረጃ ይረጋገጥልን ጥያቄ 120,837፤
** የተረጋገጠ የትምህርት ማስረጃ 95,367
** የቀረበ የአቻ ግመታ ጥያቄ 16215
** የተሰራ የአቻ ግመታ 15367
** የቀረበ የትምህርት ማስረጃ ይረጋገጥልን ጥያቄ 5260፤
** የተረጋገጠ የትምህርት ማስረጃ 4834
** የቀረበ የአቻ ግመታ ጥያቄ 1168
** የተሰራ የአቻ ግመታ 1016
** የቀረበ የትምህርት ማስረጃ ይረጋገጥልን ጥያቄ 79,544፤
** የተረጋገጠ የትምህርት ማስረጃ 73,790
** የመንግስት ሰራተኞች የትምህርት ማስረጃ የማረጋገጥ ስራን በተመለከተ ለትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ ስራ በለማው ሶፍትዌር ላይ ለ14ቱም ክልሎች የሲቪል ሰርቪስ የበላይ ኃላፊዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል።
የኢፊዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት Www. neta.gov.et ይከታተሉ::
28/05/2026
በከፍተኛ የቴክኒክና ሙያ ትምህርት የክትትልና ቁጥጥር ዘርፍ የተገኙ ስኬቶች
“የፀና ቃል፤ የላቀ እመርታ!”
--------------------------------------------------------------------------
** የከፍተኛና ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት የክትትልና ቁጥጥር መመሪያ ፤
** የከፍተኛና ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት ተማሪዎችን መረጃ አያያዝና አላላክ ማንዋል ፤እና
** 11 ቼክሊስቶች
** ለሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የብቁ እጩ የመውጫ ፈተና ተፈታኞች መስፈርት ሰርኩላር ተላልፏል፤
** በፌደራል መንግስት ወይም በውጭ ሀገር ባለሃብት ወይም በሀገር ዉስጥ በፌደራል ደረጃ ለመሰማራት የተቋቋሙ ወይም በውጭ ሀገር ህግ ተቋቁሙው ስልጠና በሚሰጡ 20 የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ላይ የክትትልና ቁጥጥር ተከናውኗል፡፡ በተገኙ የስነስርዓት ጥሰቶችን ላይ ለተቋማቱ ግብረመልስ ተሰጥቷል፤ የተሰጠውንም ግብረ መልስ የስራና ክህሎት ሚኒስቴር እንዲያውቀው ተደርጓል፤
** ከባለስልጣኑ ፈቃድ ባገኙ 390 የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ በሰነድ እና በአካል በተቋማቱ በመገኘት የክትትልና ቁጥጥር ስራዎች ተከናውነዋል፤
** በዳግም ምዝገባ ስርዓት ውስጥ ያልገቡና በተደጋጋሚ መስፈርቱን አሟልተው ከከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ እንዲወጡ ቢጠየቁ ተግባራዊ ያላደረጉ 52 ተቋማት ላይ ህግዊ የእርምት እርምጃ እንዲወስዱ ለሚመለከታቸው አካላት የማሳወቅ ስራ ተከናውኗል፤
** በባለስልጣኑ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ የሚወሰዱ የማስተካከያ የእርምት እርምጃዎችን በሙሉ ትምህርት ሚኒስቴር እንዲያውቀው ተደርጓል፤እና
** የተማሪዎች መረጃ ማደራጀት፣ አያያዝ፣ አጠባበቅና አላላክ ከፍቶቶችን፤ ፈቃድ ሲስጣቸው የነበሩ ግብአቶችን ማጓደል፤ ፈቃድ ባለገኙበት ካምፓስ ማስተማር፤ፈቃድ ባለገኙበት ትምህርት መስክና መርሃ ግብር ማስተማር፤ከተፈቀደላቸው ቁጥር ተማሪዎችን መቀበል፣ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ መስፈርት የማያሟሉ ተማሪዎችን መዝግቦ ማስተማር እና ማስመረቅ፤ የመውጫ ፈተና ለመፈተን ብቁ ያልሆኑ ተፍታኞችን ማቅረብ እና የተፈቀደላቸው ስርዓተ ትምህርት ተግባራዊ አለማድረግ በተገኘባቸው ግኝቶች እና በዳግም ምዝገባ ስርዓት ውስጥ ያልገቡ ተቋማት ላይ እንደየ ግኝቱ የጽሁፍ ማስጠንቀቂ፤ለተከታታይ ሁለት ዓመት አዲስ ተማሪ እንዳይቀበሉ፤ ለተከታታይ 4 ዓመት በተቀጡበት የትምህርት መስክ ፈቃድ እንዳይጠይቁ፤ የትምህርት መስኩን ፣ካምፓሱን እና ተቋሙ እንዲዘጉ የማስተካክያ እርምት እርምጃ ተወስዷል፡፡
** ከባለስልጣኑ ፈቃድ ላገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በክትትልና ቁጥጥር መመሪያ፤ የአሰራር ስርዓቶች፤በአጋጠሙ ተግዳሮቶ እና እየተወሰዱ ባሉ የማስተካክያ እርምት እርምጃዎች እና የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ 3 ጊዜ የግንዛቤ ማስጨባጫ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
** የከፍተኛ ትምህርት መውጫ ፈተና ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ በየሲሚስተሩ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በጋራ በመሆን ለሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የብቁ እጩ የመውጫ ፈተና ተፈታኞች መስፈርት እና የተማሪዎችን መረጃዎች የሚያቀርቡበት አግባብ ላይ የግንዛቤ ማስጨባጫ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
** በፌደራል መንግስት ወይም በውጭ ሀገር ባለሃብት ወይም በሀገር ዉስጥ በፌደራል ደረጃ ለመሰማራት የተቋቋሙ ወይም በውጭ ሀገር ህግ ተቋቁሙው ስልጠና የሚሰጡ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት በክትትልና ቁጥጥር መመሪያና አሰራር ስርዓቶች ላይ የግንዛቤ ማስጨባጫ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
የኢፊዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት Www. neta.gov.et ይከታተሉ::
26/05/2026
የኢፊዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለ1447ኛው ለዒዳ አል አደሃ/አረፋ በዓል እንኳን በሠላም አደረሳችሁ እያለ፤ በዓሉ የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅር እና የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ መልካም ምኞቱን ይገልጻል፡፡
ኢድ ሙባረክ-EID MUBARAK !!!
የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
2018 ዓ.ም.
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት Www. neta.gov.et ይከታተሉ::
26/05/2026
በጥራት ኦዲት ዘርፍ የተገኙ ስኬቶች “የፀና ቃል፤ የላቀ እመርታ!”
-----------------------------------------------------------------
** የከፍተኛ ትምህርትና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና የአካዳሚክ ጥራት ኦዲት መመሪያ፤
** የከፍተኛ ትምህርት የአካዳሚክ ጥራት ኦዲት ስታንዳርድ እና ውጤት አመላካች፤
** የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና የአካዳሚክ ጥራት ኦዲት ስታንዳርድ እና ውጤት አመላካች፤እና
** ከ 8 በላይ የአሠራር ስርዓት ሰነዶች ተዘጋጅተዋል፡፡
** በአዲሱ የጥራት ኦዲት አስራና የሕግ ማህቀፍ እንዲሁም የ ADRI model መሠረት በ 13 የትምህርትና ስልጠተና ተቋማት ላይ የአካዳሚክ ጥራት ኦዲት ተከናውኗል፡፡
** ለ 26 የከፍተኛና የቴክኒክና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት በአዲሱ የሕግና የአሰራር ስርዓት እንዲሁም ADRI model ላይ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጥቷል፤እና
** ለግለግምገማ የተቋቋሙ 17 አብይ ኮሚቴዎችና ከ 5ዐ በላይ ንሁስ ኮሚቴዎች በበይነ መረብ የማማከርና ድጋፍ የመስጠት ተሠርቷል ፡፡
የኢፊዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት Www. neta.gov.et ይከታተሉ::
25/05/2026
“የፀና ቃል፤ የላቀ እመርታ!”
በአጠቃላይ ትምህርት የኢንስፔክሽንና ቁጥጥር ዘርፍ የተገኙ ስኬቶች
-------------------------------------------------------------------
** የአጠቃላይ ትምህርት የኢንስፔክሽን ሀገራዊ ማእቀፍ መመሪያ፣መረጃ መሰብሰቢያ እና ቼክሌስት ከባለሥልጣኑ የብሔራዊ የብቃት ማእቀፍ የሥራ ክፍል ጋር በመሆን እየተሰራ ይገኛል፤ እና
** የዓለም አቀፍ ፣የማህበረሰብ እና የበጎ አድራጎት ትምህርት ቤቶች የክትትልና የቁጥጥር መመሪያ በሥራ ክፍሉ ተገምግሞ እንዲጸድቅና ሥራ ላይ እንዲውል ህጋዊ አግባብነቱ እየታየ ይገኛል፡፡
** ለመጀመሪያ ጊዜ በክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች በሚገኙ በ104 ቅድመ አንደኛ ደረጃ፤አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የአጠቃላይ ትምህርት ኢንስፔክሽን አገልግሎት እንዲያገኙ ተደርጓል፤
** በ30 የዓለምአቀፍ እና የማህበረሰብ ትምህርት ተቋማት ላይ የክትትልና የቁጥጥር ሥራ ተከናውኗል፤እና
** ለ9 ተቋማት በአጠቃላይ ትምህርት ቁጥጥር ወቅት በታዩ ክፍተቶች ላይ ማስተካከያ እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ ተላልፏል፡፡
** ለዓለም አቀፍ እና የማህበረሰብ ትምህርት ቤቶች ርዕሳነ መምህራን እና ባለሀብቶች በኢንስፔክሽን አሰራር ላይ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
** በሁሉም ክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች ለሚገኙ የትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች በአጠቃላይ ትምህርት ኢንስፔክሽን አሰራር ላይ ውይይት ተደርጓል፡፡
የኢፊዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት Www. neta.gov.et ይከታተሉ::
22/05/2026
በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ የተገኙ ስኬቶች “የፀና ቃል፤ የላቀ እመርታ!”
-----------------------------------------------------------------
** በፌደራል መንግስት ወይም በውጭ ሀገር ባለሃብት ወይም በሀገር ዉስጥ በፌደራል ደረጃ ለመሰማራት የተቋቋሙ ወይም በውጭ ሀገር ህግ ተቋቁሙው ስልጠና የሚሰጡ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ናቸው፡፡
** የከፍተኛ ትምህርት እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ፈቃድ እና ፈቃድ እድሳት አሰጣጥ መመሪያ ፤
** ስታንዳርድ ፤ እና
** ቼክሊስት፤
** ለ14 የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት ፈቃድ ተሰጥቷል፡፡
** ለ10 የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት የፈቃድ ዕድሳት ተሰጥቷል፡፡
** በሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ሥር ለሚገኙ የሚሰጡ ተቋማት ወደ ፈቃድ ስርዓቱ እንዲገቡ ሰርኩላር ተላልፏል፡፡
** በዘርፉ ለሚገኙ ተቋማት የፈቃድ ጥያቄ ሂደትን በተመለከተ እና ተቋማት በፈቃድ ስርዓት ውስጥ እንዴት መግባት እንዳለባቸው ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
** በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት በስርዓተ ትምህርት ቀረጻላይ በመገኘት ሙያዊ ድጋፍ ተደርጓል፡፡
** በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ ለመሰማራት ለሚፈልጉ ተቋማት በቴክኒክና ሙያ ፈቃድ አሰጣጥ መመሪያ እና ስታንዳርድ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
የኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት Www. neta.gov.et ይከታተሉ።
21/05/2026
“የፀና ቃል፤ የላቀ እመርታ!”
በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ የተገኙ ስኬቶች
---------------------------------------
** የዓለም አቀፍ እና የማህበረሰብ ትምህርት ቤቶች ፈቃድ እና እድሳት መመሪያ
** ስታንዳርዶች
** ጋይድላይኖች
** ቼክሊስቶች እና
** የመገምገሚያ መስፈርቶች
** ለ31 የዓለም አቀፍ እና የማኅበረሰብ ትምህርት ቤቶች የፈቃድ እድሳት ተደርጓል፤እና
** ለ11 ዓለም አቀፍ ትምህርት ቤቶች አዲስ ፈቃድ ተሰጥቷል፤
** ከኬንያ የፒርሰንና የኬምብሪጅ ስርዓተ ትምህርት ላይ ለባለሙያዎችና መፅሀፍ ላይ በመፅሐፍ አቅራቢ ( Correspondence) የግንዛቤ ማስጨበጫ እና
** ከኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ የአለም አቀፍ እና የማህበረሰብ ት/ርት ቤቶች ለመገምገም ያስችል ዘንድ መምህራን ስለ አለም አቀፍ ካሪኩለም ስልጠና ተሰጥቷ፡፡
የኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት Www. neta.gov.et ይከታተሉ።
20/05/2026
በፈቃድ አሰጣጥ እና ፈቃድ እድሳት ዘርፍ የተገኙ ስኬቶች “የፀና ቃል፤ የላቀ እመርታ!”
--------------------------------------------------------------------------
** የከፍተኛ ትምህርት እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ፈቃድ እና ፈቃድ እድሳት አሰጣጥ መመሪያ
** የፈቃድ አሰጣጥ እና እድሳት ስታንዳርድ
** የመገምገሚያ ቼክ ሌስት እና
**የዳግም ምዝገባ መምሪያ
** ፈቃድ መስጠት እና ፈቃድ ማደስ፤
** የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዳግም ምዝገባ ሰነድ ምርመራ እና የመስክ ምልከታ፤
** የሁሉም የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዳግም ምዝገባ ሰነድ ምርመራ፤
** በክልሎች እና በሁሉም ከተማ አስተዳደር የሚገኙ የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመስክ ምልከታ፤
** የመንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዳግም ምዝገባ ሰነድ ምርመራ ሥራ መጀመር፤
** በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሚገኙ የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን የዳግም ምዝገባ የሰነድ ምርመራ እና የመስክ ምልከታ ሥራ ማጠናቀቅና ለህብረተሰቡ ይፋ ማድረግ ፤እና
** የፈቃድ አሰጣጥ ሥራን ዲጂታላይዝ ማድረግ
** በፈቃድ አሰጣጥ እና ፈቃድ እድሳት ዙሪያ በሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች ለሚገኙ ለፍትህ፣ ለሲቪል ሰርቪስ ፣ለፖሊስ፣ለትምህርት ቢሮ እና ለሚዲያ ተቋማት ኃላፊዎች እና ተወካዮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷ ል፤
** በዳግም ምዝገባ መምሪያ ላይ ለሁሉም የግል እና የመንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አመራሮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷ ል፤እና
** የዳግም ምዝገባ ሥራን ለሚያከናውኑ ባለሙያዎች የሥነ ምግባር እና ሙስናንን የመከላከል ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
** 290 የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፤533ካምፓሶቻቸው እና 3126ፕሮግራሞቻቸው፤
** 47 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና 119 ካምፓሶቻቸው የሰነድ ምርመራ ሥራ ተጀምሯል፡፡
** 84 የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፤254 ካምፓሶቻቸው እና 921 ፕሮግራሞቻቸው በዳግም ምዝገባ ሥርዓት ሳያልፉ ቀርተዋል፡፡
** በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 75 የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፤116 ካምፓሶቻቸው እና 784 የዳግም ምዝገባ የሰነድ ምርመራ እና የመስክ ምልከታ ተደርጎላቸዋል፡፡
** ተቋማት ተዛማጅ ካልሆኑ የንግድ መስኮች ጋር ተቀላቅለው እንዳይሰሩ ያደርጋል፤
** ህጋዊ የአሰራር ስርዓት ተቋማት ላይ እንዲሰፍን ያደርጋል፤
** ተቋማት በራሳቸዉ ህንጻ ወይም ሙሉ ህንጻ ተከራይተው ማስተማር እንዲችሉ ያደርጋል፤
** ተቋማት ሰነዶቻቸውን በአዲሱ የጥራት መስፈርት መሰረት እንዲከልሱ ያደርጋቸዋል እና
** ተቋማት የመምህራን የትምህርት ዝግጅትና የቅጥር ሁኔታ በሚፈለገው ደረጃ እንዲያሟሉ ያስችላል፡፡
** ተቋማት ለጥናትና ምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት ትኩረት ሰጥተዉ እንዲሰሩ ያበረታታል፤
** ማህበረሰቡ ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኝ ያስችላል፤
** ለህብረተሰቡአሁናዊ የትምህርት ጥራት መረጃ በመስጠት የጥራት ጠያቂ ማድረግ ያስችላል፤
** ተቋማዊ መዋቅራቸዉን በመገምገም ውጤታማ የአስተዳደር ስርዓት እንዲኖራቸው እድል ይሰጣቸዋል፡፡ እና
** ተቋማት በተጨባጭ በጀት እንዲመሩ ያደርጋል፡፡
የኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት Www. neta.gov.et ይከታተሉ።
19/05/2026
በባለሥልጣኑ ለፕሮግራም እውቅና የወጣውን የጥራት ስታንዳርድ ላሟሉ በባለሥልጣኑ ተገምግሞ የሚሰጥ የጥራት ማረጋገጫ እውቅና አሰጣጥ ዘርፍ የተገኙ ስኬቶች
“የፀና ቃል፤ የላቀ እመርታ!”
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተቋም እና የፕሮግራም እውቅና አሰጣጥ መመሪያ
** ህክምና እና ጤና ሳይንስ
** ግብርና
** ምህንድስና እና ኮምፒዩተር ሳይንስ
** ቢዝነስ እና ሂዩማኒቴስ እና
** የተፈጥሮ እና የቀመር ሳይንስ
** በስታንዳርዶች እና በመገምገሚያ መሳሪያዎች ዙሪያ በአካል እና በበይነ መርብ (virtual) በመታገዝ ከሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጭ ባለሙያዎችን በመጋበዝ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና የመስጠት ፤ እና
** የውጭ ገምጋሚ ባለሙያ ማሰልጠን
** ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን መቀመር፤
** የእውቅና አሰጣጥ ካውንስል ማቋቋም፤
** የእውቅና አሰጣጥ ስርዓትን ዲጂታላይዝ ማድረግ፤
** የፕሮግራም እውቅና ለጠየቁ ተቋማት የውስጥና የውጭ ገምጋሚዎችን (Team of Assessors) በመላክ የዴስክ ሪቪው፣ ዶክመንት ስተዲና የመስክ ምልከታ ማድረግ፤እና
** የጥራት ስታንዳርዱን ለሟሉ ፕሮግራሞች እውቅና መስጠት፡፡
** በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ለ18 ፕሮግራሞች ተገምግመውበእውቅና ካውንስሉ ውሳኔ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
** ተማሪን በልዩ ሁኔታ መመደብ፤
** ለጥናትና ምርምር በልዩ ሁኔታ በጀት መመደብ፤
** ለተቋሙ መምህራንና ተማሪዎች በልዩ ሁኔታ የትምህርት እድል መስጠት፤
** ከባለስልጣኑ ጋር በመሆን የተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎችን በመጠቀም እውቅና ያላቸውን ተቋማት ወይም ፕሮግራም ማስተዋወቅ፤ እና
** ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ወይም ባለድርሻ አካላት ጋር በልዩ ሁኔታ ትስስር እንዲፈጥሩ ድጋፍ ማድረግ፡፡
የኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት Www. neta.gov.et ይከታተሉ።