Transport Planning and Management

Transport Planning and Management

Share

Transport Planning and Management...

01/07/2023

Mass Transport for ALL

17/10/2018

ቮልቮ በርዝመቱ ከዓለም አንደኛ ነው የተባለውን አውቶብስ ይፋ አደረገ
........................................
የተሽከርካሪ አምራች ኩባንያ የሆነው ቮልቮ በርዝመቱ ከዓለም አንደኛ ነው የተባለውን ተሽከርካሪ መስራቱን አስታውቋል።

አዲሱ የቮልቮ አውቶብስ በብራዚል ውስጥ የተሰራ ሲሆን “ግራን አርቲክ 300” የሚል ስያሜ የተሰጠው መሆኑም ተነግሯል።

የዓለማችን ረጅሙ ነው የተባለው አውቶብስ 30 ሜትር ርዝመት ያለው መሆኑን ነው ኩባንያ ያስታወቀው።

በአንድ ጊዜ እስከ 300 ሰዎችን እንደሚጭን የተነገረለት “ግራን አርቲክ 300” ቮልቮለ አሰውቶብስ አምስት መግቢያና መውጫ በሮች አሉት ተብሏል።

የአዲሱ የቮልቮ አውቶብስ በተለይ በህዝብ መጓጓዣ ዘርፍ ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያስችልም ነው ኩባንያው ያስታወቀው።

ይህም በአንድ ረጅም አውቶብስ በርካታ ሰዎችን ብቻ በማመላለስ ለስምሪት የሚወጡ አውቶብሶችን ቁጥር ለመቀነስ ያስችላል።

የአውቶብሶቹ ቁጥር መቀነስ ደግሞ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይከሰት በማድረግ ፈጣን የህዝ ማመላለሻ አገልግሎት እንዲሰጥ የኒያስች ነው ተብሎለታል።

ምንጭ፦ www.volvobuses.com

Photos from Transport Planning and Management's post 15/10/2018

የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ባለስልጣን የከተማውን የትራንስፖርት እጥረት ለማቃለል ለብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) ትዕዛዝ ከሰጣቸው 850 አውቶብሶች 700ዎቹን እስካሁን አልተረከበም ተባለ፡፡
ለአውቶብሶቹ 3.4 ቢሊዮን ብር ተከፍሏል ተብሏል፡፡

የባለስልጣን መ/ቤቱ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ሀላፊ ወ/ሮ እፀገነት አበበ ዛሬ ለሸገር ሲናገሩ፣ ከሜቴክ ጋር የአውቶብሶቹን ስራ ውል የገባነው በሰኔ ወር 2009 ዓ/ም ሲሆን አውቶብሶቹን መረከብ የነበረብን ሰኔ 2010 ነበር ብለዋል፡፡

የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን አውቶብሶቹን በቃሌ መሰረት ያላስረከብኩት በውጪ ምንዛሬ ችግር ነው ብሎናል ያሉት ወ/ሮ እፀገነት ከዚህ ወር ጀምሮ ግን ቀስ በቀስ ቀሪ 700 አውቶብሶቹን ሊያስረክበን ቃል ገብቶልናል ብለዋል፡፡

ሜቴክ ለአውቶብሶቹ መስሪያ የሚያስፈልገውን እቃዎች አስቀድሞ ገዝቷል፣ በተባለው ጊዜም ያደርስልናል ብለን ተስፋ እናደርጋለን ሲሉ ወ/ሮ እፀገነት ተናግረዋል፡፡

(ወንድሙ ኃይሉ)

21/09/2018

Door-to-Door Transport

Photos from Transport Planning and Management's post 21/09/2018

Best Practice in Developed Countries
-------------------------------------------------
Pedestrian Crossing
===============
እንጂነሮቻችን ከዚህ ምን መማር አለባቸው ብሎ ያስባሉ???

Photos from Transport Planning and Management's post 13/09/2018
Photos from Transport Planning and Management's post 13/09/2018

የመዲናዋ ፈጣን የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት BRT 2 ፕሮጀክት ተግባራዊ ለማድረግ የዲዛይን ማሻሻያ ክለሳ የተደረገ ሲሆን ዝርዝር የዲዛይን ስራው እ.ኤ.አ. ሀምሌ 2018 ይጠናቀቃል፡፡
ፕሮጀክቱ 102 ሚሊዮን ዩሮ የሚጠይቅ ይሆናል፡፡

የዲዛይን ማሻሻያው ከዚህ ቀደም ያልታዩ የእግረኞች መተላለፊያዎች በበቂ ርቀት እንዲሰሩ የሚያደርግ ከመሆኑም በተጨማሪ በመንገድ መጋጠሚያዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የእግረኞች መተላለፊያ እንዲኖር የሚያስችል የተለያየ ዲዛይን ያላቸው የእግረኞች መተላለፊያዎች እንዲካተቱ ተደርጓል፡፡

የፕሮጀክቱ ስራ ለመጀመር የሚያስችሉ ቅድመ ሁኔታዎች በመከናወን ላይ ሲሆን የፕሮጀክቱ ግንባታ በ2011 ዓ.ም ለማስጀመር ርብርብ በመደረግ ላይ ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቱ በሁለት ዓመታት ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ታቅዷል፡፡

የቢአርቲ 2 ኮሪደር መነሻው ከዊንጌት በፓስተር፣ በአውቶቡስ ተራ፣ በአንዋር መስጊድ፣ በተክለሃይማኖት፣ በሜክሲኮ፣ በቄራ፣ በጎፋ ገብርኤል እና መድረሻው ጀሞ ቁጥር አንድ ሲሆን የጉዞው ርዝመት 16 ኪሎ ሜትር ይሸፍናል። የቢአርቲ 2 ኮሪደር መነሻውንና መድረሻውን ጨምሮ 20 የአውቶቡስ ማቆሚያዎችና ሁለት ተርሚናሎች ይኖሩታል።
ምንጭ፡ Tpmo Aac

Photos from Transport Planning and Management's post 13/09/2018

ከፍተኛ ወጪ ወጥቶበት ለህዝብ ትራንስፖርት/Public transport/ ማቆሚያ መጠለያ/ bus stop with shelters/ ተብሎ የተሰሩ አደጋ እየደረሰባቸው መሆኑን ተመልክተናል፡፡ ስለዚህ የሚመለከተው አካል ክትትል ቢያደርግበት እንላለን፡፡

10/09/2018
07/09/2018

Transport For All

07/09/2018

የፈጠራ መጓጓዣ ቴክኖሎጂ
METRINO:- Innovative Transportation Technology

Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Category

Website

Address


Civil Service University
Addis Ababa
2008E.C