Mass Transport for ALL
Transport Planning and Management
Transport Planning and Management...
17/10/2018
ቮልቮ በርዝመቱ ከዓለም አንደኛ ነው የተባለውን አውቶብስ ይፋ አደረገ
........................................
የተሽከርካሪ አምራች ኩባንያ የሆነው ቮልቮ በርዝመቱ ከዓለም አንደኛ ነው የተባለውን ተሽከርካሪ መስራቱን አስታውቋል።
አዲሱ የቮልቮ አውቶብስ በብራዚል ውስጥ የተሰራ ሲሆን “ግራን አርቲክ 300” የሚል ስያሜ የተሰጠው መሆኑም ተነግሯል።
የዓለማችን ረጅሙ ነው የተባለው አውቶብስ 30 ሜትር ርዝመት ያለው መሆኑን ነው ኩባንያ ያስታወቀው።
በአንድ ጊዜ እስከ 300 ሰዎችን እንደሚጭን የተነገረለት “ግራን አርቲክ 300” ቮልቮለ አሰውቶብስ አምስት መግቢያና መውጫ በሮች አሉት ተብሏል።
የአዲሱ የቮልቮ አውቶብስ በተለይ በህዝብ መጓጓዣ ዘርፍ ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያስችልም ነው ኩባንያው ያስታወቀው።
ይህም በአንድ ረጅም አውቶብስ በርካታ ሰዎችን ብቻ በማመላለስ ለስምሪት የሚወጡ አውቶብሶችን ቁጥር ለመቀነስ ያስችላል።
የአውቶብሶቹ ቁጥር መቀነስ ደግሞ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይከሰት በማድረግ ፈጣን የህዝ ማመላለሻ አገልግሎት እንዲሰጥ የኒያስች ነው ተብሎለታል።
ምንጭ፦ www.volvobuses.com
15/10/2018
የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ባለስልጣን የከተማውን የትራንስፖርት እጥረት ለማቃለል ለብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) ትዕዛዝ ከሰጣቸው 850 አውቶብሶች 700ዎቹን እስካሁን አልተረከበም ተባለ፡፡
ለአውቶብሶቹ 3.4 ቢሊዮን ብር ተከፍሏል ተብሏል፡፡
የባለስልጣን መ/ቤቱ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ሀላፊ ወ/ሮ እፀገነት አበበ ዛሬ ለሸገር ሲናገሩ፣ ከሜቴክ ጋር የአውቶብሶቹን ስራ ውል የገባነው በሰኔ ወር 2009 ዓ/ም ሲሆን አውቶብሶቹን መረከብ የነበረብን ሰኔ 2010 ነበር ብለዋል፡፡
የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን አውቶብሶቹን በቃሌ መሰረት ያላስረከብኩት በውጪ ምንዛሬ ችግር ነው ብሎናል ያሉት ወ/ሮ እፀገነት ከዚህ ወር ጀምሮ ግን ቀስ በቀስ ቀሪ 700 አውቶብሶቹን ሊያስረክበን ቃል ገብቶልናል ብለዋል፡፡
ሜቴክ ለአውቶብሶቹ መስሪያ የሚያስፈልገውን እቃዎች አስቀድሞ ገዝቷል፣ በተባለው ጊዜም ያደርስልናል ብለን ተስፋ እናደርጋለን ሲሉ ወ/ሮ እፀገነት ተናግረዋል፡፡
(ወንድሙ ኃይሉ)
Door-to-Door Transport
21/09/2018
Best Practice in Developed Countries
-------------------------------------------------
Pedestrian Crossing
===============
እንጂነሮቻችን ከዚህ ምን መማር አለባቸው ብሎ ያስባሉ???
13/09/2018
13/09/2018
የመዲናዋ ፈጣን የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት BRT 2 ፕሮጀክት ተግባራዊ ለማድረግ የዲዛይን ማሻሻያ ክለሳ የተደረገ ሲሆን ዝርዝር የዲዛይን ስራው እ.ኤ.አ. ሀምሌ 2018 ይጠናቀቃል፡፡
ፕሮጀክቱ 102 ሚሊዮን ዩሮ የሚጠይቅ ይሆናል፡፡
የዲዛይን ማሻሻያው ከዚህ ቀደም ያልታዩ የእግረኞች መተላለፊያዎች በበቂ ርቀት እንዲሰሩ የሚያደርግ ከመሆኑም በተጨማሪ በመንገድ መጋጠሚያዎች ደህንነቱ የተጠበቀ የእግረኞች መተላለፊያ እንዲኖር የሚያስችል የተለያየ ዲዛይን ያላቸው የእግረኞች መተላለፊያዎች እንዲካተቱ ተደርጓል፡፡
የፕሮጀክቱ ስራ ለመጀመር የሚያስችሉ ቅድመ ሁኔታዎች በመከናወን ላይ ሲሆን የፕሮጀክቱ ግንባታ በ2011 ዓ.ም ለማስጀመር ርብርብ በመደረግ ላይ ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቱ በሁለት ዓመታት ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ታቅዷል፡፡
የቢአርቲ 2 ኮሪደር መነሻው ከዊንጌት በፓስተር፣ በአውቶቡስ ተራ፣ በአንዋር መስጊድ፣ በተክለሃይማኖት፣ በሜክሲኮ፣ በቄራ፣ በጎፋ ገብርኤል እና መድረሻው ጀሞ ቁጥር አንድ ሲሆን የጉዞው ርዝመት 16 ኪሎ ሜትር ይሸፍናል። የቢአርቲ 2 ኮሪደር መነሻውንና መድረሻውን ጨምሮ 20 የአውቶቡስ ማቆሚያዎችና ሁለት ተርሚናሎች ይኖሩታል።
ምንጭ፡ Tpmo Aac
13/09/2018
https://www.facebook.com/tpm2008/
and
Transport For All
13/09/2018
ከፍተኛ ወጪ ወጥቶበት ለህዝብ ትራንስፖርት/Public transport/ ማቆሚያ መጠለያ/ bus stop with shelters/ ተብሎ የተሰሩ አደጋ እየደረሰባቸው መሆኑን ተመልክተናል፡፡ ስለዚህ የሚመለከተው አካል ክትትል ቢያደርግበት እንላለን፡፡
10/09/2018
07/09/2018
Transport For All
07/09/2018
የፈጠራ መጓጓዣ ቴክኖሎጂ
METRINO:- Innovative Transportation Technology
Click here to claim your Sponsored Listing.
Location
Category
Website
Address
Civil Service University
Addis Ababa
2008E.C