Ustaz Abubeker Ahmed/ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ.

Ustaz Abubeker Ahmed/ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ.

Share

ኡስታዝ አቡበከር አህመድ የእስልምና መምህር/Ustaz Abubeker Ahmed Mohammed Islamic Teacher and preacher

23/06/2026

የአሹራ ፆም

ሙሐረም 10 ነብዩላህ ሙሳ(ዓ.ሰ) ከአንባገነኑ የፊርዓውን ጭቆና ነፃ የወጡበት ቀን ነው:: ይህን ቀን አንድ ቀን ቀደም ተብሎ ሙሐረም 9 አልያ ሙሐረም 11ን በማስከተል መፆም ይወደዳል::

ረሱል ስለ አሹራ ፆም ሲናገሩ "ምናልባት ለሚቀጥለው አመት በህይወት ከቆየሁ ዘጠነኛውንም እፆማለሁ ብለዋል (ሶሒሁ ሙስሊም 1134)

ሙሐረም 10 የአሹራ ቀን የፊታችን ሐሙስ ሰኔ 18 (Jun 25)ነው:: ይህን ቀን መፆም የአላህ መልዕክተኛ(ሰዓወ) "የአንድ አመት ወንጀል ያስምራል ብዬ በአላህ ላይ ተስፋ አደርጋለው ብለዋል (ሶሒሁ ሙስሊም 1163)

ቤተሰባችንንም ሌላውንም ይህን መልዕክት እናስታውስ!

Photos from Ustaz Abubeker Ahmed/ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ.'s post 22/06/2026

ለጠቅላይ ምክር ቤቱ የሀጅ ልዑክ አመራሮችና አባላት የእውቅናና የምስጋና መርሃ ግብር ተካሄደ።
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ሰኔ 15/2018 ዓ.ል| ሙሀረም 6/1447 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በምክትል ፕሬዝደንት ማዕረግ የሀጅና ዘርፍ ኃላፊ ዶክተር ሙሀመድ ሷሊህ የተመራው የሀጅ ልዑክ እና ባለድርሻ አካላት የእውቅናና የምስጋና መርሃ ግብር ተከናወነ።

​በሸራተን አዲስ ሆቴል በተካሄደው በዚህ የምስጋና መርሃ ግብር ላይ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ ስራ አስፈጻሚ አባላት፣ ሚኒስትሮች፣ አምባሳደሮች፣ የክልል የመጅሊስ ፕሬዝዳንቶች፣ የልዑካን ቡድኑ አባላት፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝደንት የክቡር ዶክተር ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ በመርሃ ግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግር በሀጅ አገልግሎትና መስተንግዶ ዘርፍ በዓለም አቀፍ መድረክ የተገኘው የዲያመንድ ሽልማት በአላህ ፈቃድ በጋራ ጥረት የተገኘ ነው ብለዋል።

ስኬትን ከማግኘት ይልቅ ስኬትን ማስቀጠል ትልቅ ስራ ነው ያሉት ፕሬዝደንቱ ሀገራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ያገኘችውን ደማቅ ውጤት ለማስቀጠል በቀጣይም በቅንጅት መስራት ይጠበቃል ብለዋል።

ሕዝበ ሙስሊሙ የሀገራችን ሰላም ለማረጋገጥና በአንዳንድ የሀገራችን ክልሎች የታየው የዝናብ እጥረት እንዲስተካከል ዱዓ እንዲያደርግም የአደራ ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ ሙሀመድ እድሪስ በበኩላቸው ህዝበ ሙስሊሙ ከስምንት ወራት በፊት ሰላማዊ የመጅሊስ ምርጫ በማድረጉ ለዛሬው ውጤት መሠረት እንደሆነው በመጥቀስ የተገኘው ውጤት የተቋሙ ብቻ ሳይሆን የመላ ኢትዮጵያዊያን ነው ብለዋል።

ሚኒስትሩ አክለውም ውጤቱ ይህ ለነገ ስኬት መነሻ በመሆኑ ቅንጅታዊ ስራው በሌሎች የልማት ዘርፎችም ሊደገም እንደሚገባ ገልጸዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝደንት ሸይኽ አብዱልከሪም ሸይኽ በድረዲን በዚህ ወቅት እንደገለጹት ጠቅላይ ምክር ቤቱ በ1447 የሐጅ መስተንግዶ ባከናወናቸው ውጤታማ ተግባራት የዳይመንድ ደረጃ ተሸላሚ በመሆን የሀገራችንን ስም በዓለም አቀፍ መድረክ ከፍ አድርጓል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ የፕሬዝደንት ጽህፈት ቤት ኃላፊ ዑስታዝ አቡበከር አህመድ በበኩላቸው ይህ ስኬት በአንድ ጀምበር እና በጥቂት ግለስቦች ጥረት የመጣ ሳይሆን የብዙዎች ዱዓ እና የሌት ከቀን ትጋት እንዲሁም በተቋም ቅንጅታዊ አሰራር የመጣ ነው ብለዋል።

ከሕዝብ በተሰጣቸው አደራ መሠረት ተቋማዊ አደረጃጀቱን ዘመናዊና ውጤታማ በማድረግ ስራውን በበላይነት ለመሩት የጠቅላይ ምክር ቤቱ አመራሮች የላቀ ምስጋናም አቅርበዋል።

በጠቅላይ ምክር ቤቱ በምክትል ፕሬዝደንት ማዕረግ የሀጅና ዑምራ ዘርፍ ኃላፊ ዶክተር ሙሐመድ ሷሊህ ስራው ከፍተኛ ውጣ ውረድ ያለው መሆኑን ገልጸው የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝደንት የክቡር ዶክተር ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ የሰጡት ቆራጥ አመራር ውጤቱ እንዲገኝ ማስቻሉን በመግለጽ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የሀጅ ልዑኩ አመራር እና አባላት በክቡር ፕሬዝደንቱ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
••••••••••••••••••••••••••
ከ‐ የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት

22/06/2026

ሕዝባችን ተጎድቷል


#ኡስታዝአቡበከርአሕመድ

Photos from Ustaz Abubeker Ahmed/ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ.'s post 22/06/2026

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ​የሐጅ ልዑክ አመራሮችና አባላት ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው።
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ሰኔ 15/2018 ዓ.ል| ሙሀረም 07/1447 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ]

​ሀገሩን በዓለም አቀፍ መድረክ የአልማዝ ደረጃ ተሸላሚ ያደረገው በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በምክትል ፕሬዝደንት ማዕረግ የሐጅና ዑምራ ዘርፍ ኃላፊ ዶክተር ሙሐመድ ሷሊህ የተመራውን የሐጅ ልዑክ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ ደማቅ አቀባበል ተደረገለት።

ልዑኩ ከተጠሪ፣ ከባለድርሻ እና ከአጋር አካላት ጋር በቅንጅት በመስራትና በመምራት ኢትዮጵያ በሳዑዲ አረቢያ በተዘጋጀው ዓለም አቀፍ መድረክ የአልማዝ (Diamond) ሽልማት እንድትቀዳጅ አስችሏል።

የሐጅ ልዑኩ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የልማትና ማህበራዊ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝደንት ሸይኸ ሃሚድ ሙሣ፣ በስራ አስፈጻሚ አባላት እና ጥሪ በተደረገላቸው እንግዶች አቀባበል የተደረገለት ሲሆን ጠቅላይ ምክር ቤቱ ለዚህ አገራዊ ስኬት ዕውውና ለመስጠት ባዘጋጀው የምስጋና መርሃ ግብር ላይ ለመታደም ሸራተን አዲስ ሆቴል ተገኝቷል።
•••••••••••••••••••••••••••••••••••

21/06/2026

የንጹሐንን ነፍስ ለርካሽ ፖለቲካ


#ኡስታዝአቡበከርአሕመድ

20/06/2026

የእናቱን አደራ ለመወጣት ከመሪር ሐዘኑ ጋር ለመፈተን ከወጣው ታዳጊ ጎን እንድንቆም ጥሪዬን አቀርባለሁ።

ታዳጊው ኻሊድ የሚኒስትሪ ፈተናውን በሚፈተንበት ዕለት ነበር ወላጅ እናቱን ያጣው። ይሄንን መሪር ሐዘኑን እንደተሸከመ ነበር፤ ከዓላማው እንዳይዛነፍ 'አደራ' ያለችውን እናቱን ቃል አክብሮ ለመፈተን ወጥቶ የነበረው። በፈተና መሐል ሆኖም ነበር እናቱን የቀበረው።
በእናቱ እጅ ተቀማጥሎ እያደገ የነበረው ታዳጊው ለቤቱ የመጀመሪያ ልጅ ሲሆን፤ 2 ታናናሽ ወምድሞችም አሉት። አሁን በኻሊድ ትከሻ ላይ የታናናሽ ወንድሞቹም ኃላፊነት ወድቆበታል። ይህንን ታዳጊ አለሁ ማለት ደሞ የኛ የወገኖቹ ድርሻ ነው።

መሰል ከዓላማቸው የማይዘናጉ ትጉኃንን ማገዝ እንደማህበረሰብ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን እያስታወስኩ፤ አላህ ለታዳጊው፣ ለመላው ቤተሰቦቹና ወዳጅ ዘመዶቹ መፅናናቱን እንዲለግስ እማፀነዋለሁ።

ተማሪ ኻሊድን መርዳት ለምትፈልጉ የሲንቄ ባንክ እና የአዋሽ ባንክ አካውንት ተከፍቷል። ተማሪ ኻሊድ እድሜው 18 ስላልሞላውና ዘመድም ስለሌለው፤ ብቻውን ገንዘብ አውጥቶ መጠቀም ስለማይችል፣ አካውንቱ በአካባቢው መስጅድ ኡስታዝ፣ ከሀገር ሽማግሌ እና ከራሱ ጋር በጋራ በመሆን አካውንት ተከፍቶለታል።

①) ስንቄ ባንክ
11 14385901915

②) አዋሽ ባንክ
013201115433100

20/06/2026

ተገፍተንም፤ ተበድለንም፤ ስለ ሰላም ነው የምንጮኸው


#ኡስታዝአቡበከርአሕመድ

19/06/2026

ገ*-ዳይ ገ*-ዳይ ነው!


#ኡስታዝአቡበከርአሕመድ

19/06/2026

አላህ ሆይ!
ከዱንያ ግርግር፤
የነፍስን ሰላም ከሚያውክ ወከባ፤
የልብን ንፅሕና ከሚያጠፋ ውሎ፤
ቃልህና መልዕክተኛህ (ሰ.ዐ.ወ) ከማይወሱበት ስብስብ
አንተው አርቀን!
ቀኑንም፤
ለዱዓ ያነሳነው እጅ በተቀባይነት የሚመለስበት፤
በሰለዋት የምንደምቅበት
መልካም ጁምዓ አድርግልን!


#ኡስታዝአቡበከርአሕመድ

18/06/2026

ሁላችንም ተጠቂዎች ነን!


#ኡስታዝአቡበከርአሕመድ

Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Address


Addis Ababa