Ustaz Abubeker Ahmed/ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ.

Ustaz Abubeker Ahmed/ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ. ኡስታዝ አቡበከር አህመድ የእስልምና መምህር/Ustaz Abubeker Ahmed Mohammed Islamic Teacher and preacher
(297)

ያልሞከርነው አዲሱ መንገድ ሀገራዊ ምክክሩ በስኬት በመጠናቀቁ የተሰማኝን ደስታ ለመግለፅ  እወዳለሁ:: ሀገራችን ኢትዮጵያ ያልሞከረችው የነበረው ይህ አዲሱ መንገድ የሁሉንም ኢትዮጵያዊ ፍላጎት...
22/08/2026

ያልሞከርነው አዲሱ መንገድ

ሀገራዊ ምክክሩ በስኬት በመጠናቀቁ የተሰማኝን ደስታ ለመግለፅ እወዳለሁ:: ሀገራችን ኢትዮጵያ ያልሞከረችው የነበረው ይህ አዲሱ መንገድ የሁሉንም ኢትዮጵያዊ ፍላጎት እና መሻት በማቀራረብ ደረጃ የተገኘበት ውጤት አመርቂ የሚባል ነው::

እጅግ ተራርቀው የነበሩ ሀሳቦች ተቀራርቦ በመድረኩ ላይ መመካከር በመቻሉ በአብዛኛው የውይይቱ አጀንዳዎች ላይ ጥቅል መግባባት ላይ መደረስ መቻሉ ለሀገራችን አዲስ ተስፋ እና ስኬት ነው::

ይህ የምክክር መድረክ ብዙ የተለፋበት የሁሉንም ኢትዮጵያዊ መሰረታዊ የልዩነት ነጥቦች እና ጥያቄዎች ወደ ምክክር ጠረቤዛ ማምጣት የቻለ ነበር::

ይህ የምክክር መድረክ በጥላቻ እና በመገዳደል እንዲሁም በመራራቅ ሊፈቱ የማይችሉ ጉዳዮችን በመወያየት እና በመቀራረብ መፍታት እንደሚቻል ያሳየ ነው::

ይህ ጉባኤ በስኬት መጠናቀቁ ለሀገራችን ኢትዮጵያ እና ለህዝቦቿ ከስኬትም በላይ ሀገራችንን በአዲስ ጠንካራ መሰረት ላይ ለመገንባት እድል የፈጠረ ነው::

በጉባኤው ከስምምነት ላይ የተደረሱባቸው ነጥቦች ወደ ተግባር ወርደው ሁሉም ኢትዮጵያዊ በብሄር፣ በሀይማኖት እና በዘር አንዱ ከአንዱ ሳይበላለጥ በፍትህ እና በእኩልነት የምንኖርባትን ኢትዮጵያ እውን ትሆን ዘንድ መስራት ያስፈልጋል::

ይህ የምክክር ጉባኤ በስኬት እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ኃላፊነት ለተወጡ አካላት በሙሉ ምስጋናዬን ለማቅረብ እወዳለሁ

ኢትዮጵያ አሸንፋለች!

21/08/2026

'ለፍትሕ ባልቆም፤ አላህ ይጠይቀኛል!'

#ኡስታዝአቡበከርአሕመድ

አላህ ሆይ!ከተቆጣህባቸው፤ ትዕዛዝህን ከጣሱት፤የቅናቻውን መንገድ ካስተባበሉት፤ መስመሩን ከሳቱትም፤ ከጠመሙትምአታድርገን!በመንገድህ አጽንተህ፤ በመንገድህ ውሰደን!ቀኑንም፤  ቁርኣን በመቅራትና...
21/08/2026

አላህ ሆይ!
ከተቆጣህባቸው፤ ትዕዛዝህን ከጣሱት፤
የቅናቻውን መንገድ ካስተባበሉት፤ መስመሩን ከሳቱትም፤ ከጠመሙትም
አታድርገን!
በመንገድህ አጽንተህ፤ በመንገድህ ውሰደን!

ቀኑንም፤ ቁርኣን በመቅራትና በሰለዋት የምንደምቅበት፤
ዱዓችንን የምትቀበልበት፤
መልካም ጁምዓ አድርግልን!

#ኡስታዝአቡበከርአሕመድ

20/08/2026

አንድም የሚራብ ሰው በጠፋ ነበር

#ኡስታዝአቡበከርአሕመድ

20/08/2026

የመፍትሔው አሰጣጥ...

#ኡስታዝአቡበከርአሕመድ

18/08/2026

ዓለሙ ላንተ ተፈጥሮ...

#ኡስታዝአቡበከርአሕመድ

17/08/2026

ደብረ ታቦር ትጣራለች! የመስጂድ ግንባታ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም

አልሃምዱሊላህ‼️የ3 ዓመቷ ህፃን ከ5 ቀን ቦኃላ ተገኝታለችበአላህ ፍቃድ ከዛም በናንተ ደጋግ ኢትዮጵያዊያን ጥረት እና ትብብር ተገኝታለች‼️ሁላችሁንም እናመሰግናለን:-ቤተሰቦቿከቀናት በፊት በ...
17/08/2026

አልሃምዱሊላህ‼️

የ3 ዓመቷ ህፃን ከ5 ቀን ቦኃላ ተገኝታለች

በአላህ ፍቃድ ከዛም በናንተ ደጋግ ኢትዮጵያዊያን ጥረት እና ትብብር ተገኝታለች‼️

ሁላችሁንም እናመሰግናለን:-ቤተሰቦቿ

ከቀናት በፊት በቤት ሰራተኛ ተሰርቃ የነበረችው የ3 ዓመቷ ህፃን ሃያት ሻሂድ ቡራዩ ፖሊስ ጣቢያ ተገኝታለች።

ሰራተኛው በተደረገው ሰፊ የማህበራዊ ሚዲያ ስርጭት ተደናግጣ ይዛት መሰወር ስላልቻለች ጥላት ያመለጠች ሲሆን ማምሻውን ያካባቢው ማህበረሰብ ባደረገው ጥቆማ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ተወስዳ ዛሬ ከቤተሰቦቿ ጋር እንድትገናኝ ተደርጋለች።

ሁላችሁም ያለ ስስት ላደረጋችሁት ትብብር እጅግ አድርገን እናመሰግናለን‼️

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ustaz Abubeker Ahmed/ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ. posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The School

Send a message to Ustaz Abubeker Ahmed/ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ.:

Shortcuts

Share