24/02/2025
አየር ጤና የጤና ሳይንስና እና ቢዝነስ ኮሌጅ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን አስመረቀ።
I ኮሌጁ በድህረ-ምረቃ እና በቅድመ-ምረቃ መርሃግብሮች ደረጃ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ሲሰጥ የቆየውን ሥልጠናዎች በተሳካ ሁኔታ ያጠናቀቁ ተማሪዎችን ዛሬ የካቲት 15 ቀን 2017 ዓ.ም በኦሮሚያ ባህል ማዕከል አስመርቋል።
በዘንድሮው ዓመት በድህረ-ምረቃና በቅድመ-ምረቃ መርሃ-ግብሮች በተለያዩ ፕሮግራሞች ሲማሩ የቆዩ እና በአገር አቀፉ መውጫ ፈተና የተመዘኑ እንዲሁም በኮሌጁ መመዘኛዎች ተገቢውን የምረቃ መስፈርት ያሟሉ ተማሪዎች ናቸው የተመረቁት።
በዚህም በድህረ-ምረቃ Masters of business administration, Masters of adult and nursing, Masters of public health የትምህርት መስኮች 204 ተመራቂዎች፤ በቅድመ-ምረቃ ቢ ኤስ ሲ ነርሲንግ፣ የህብረተሰብ ጤና አጠባበቅ እና በአካውንቲንግና ፋይናንስ የትምህርት መስኮች 150 ተመራቂዎችን፤ በTVET ደረጃ 4 አካውንቲንግ እና ፋይናንስ እንዲሁም ማርኬቲንግና ሴልስ የትምህርት መስኮች 115 በጠቅላላው 469 ተማሪዎችን አስመርቋል። ከተመረቁት መካከል 361 ያህሉ ሴቶች ናቸው።
የኮሌጁ መስራች አቶ ምህረቱ ቁሜ "ኢትዮጵያ የተማረ ትውልድ በብዛትና በጥራት እንዲኖራት ለማስቻል ኮሌጃቸውን ትኩረት ትጥቶ እየሰራ" እንደሚገኝ ጠቅሰው ለዘንድሮ አመት ተመራቂ ተማሪዎች መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።
የአየር ጤና የጤና ሳይንስና እና ቢዝነስ ኮሌጅ ፕሬዝደንት ወ/ሮ ሰርካለም ጫኔ በበኩላቸው ኮሌጁ ያስመረቃቸው ተማሪዎች በተለይም በሃገር አቀፍ መውጫ ፈተና ከፍተኛ የሚባል ውጤት በማምጣት ያለፉ መሆናቸውን ጠቅሰው "ለሃገር የሚጠቅሙ፣ በዕቅትና ክህሎት የተሻሉ ምሩቃንን አብቅተናል" ብለዋል።
01/10/2024
19/01/2024
01/12/2023
10/11/2023