13/06/2024
ሁሉን ታደርግ ዘንድ ቻይ እንደሆንህ፤ አሳብህም ይከለከል ዘንድ ከቶ እንደማይቻል አወቅሁ።
PhD in Computer Science and Engineering successfully completed with excellent grade in dissertation. Glory to Jesus.
Truth and Fact only
13/06/2024
ሁሉን ታደርግ ዘንድ ቻይ እንደሆንህ፤ አሳብህም ይከለከል ዘንድ ከቶ እንደማይቻል አወቅሁ።
PhD in Computer Science and Engineering successfully completed with excellent grade in dissertation. Glory to Jesus.
17/07/2022
Congratulations to all Ethiopians
29/01/2022
በሀዲያ ህዝብ እና ወጣቶች ጥረት የተሠራ የኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ አደባባይ በሀዲያ ዞን ዋቸሞ ከተማ።
12/08/2021
አስደሳች ዜና ለዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ
የውል ስምምነት(MOA) ተደረጓል
የዋቸሞ ዩኒቨርስቲ ከቡና ባንክ አክሲዮን ማህበር ጋር የውል ስምምነት አደረገ
ዋቸሞ ዩኒቨርስቲ ለዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ ልዩ ጠቀሜታን ሊያስገኝ የሚችል የብድር ስምምነት ውል ከቡና ባንክ አ.ማ ጋር በመፈራረሙ ለዩኒቨርስቲው ህብረተሰብ ትልቅ ዕድልን ይፈጥራል።
የቡና ባንክ ሆሳዕና ቅርንጫፍ ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ተመስገን አቡዬ እንደገለፁት፤ ዩኒቨርሲቲው ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት ከዩኒቨርስቲው ጋር አብሮ ለመሥራት ከብዙ ተፎካካሪ ባንኮች ጋር ለመወዳደር ፕሮፖዛል ማቅረቡን ገልፀው የቀረበውም ፕሮፖዛል በሚያይ ኮሚቴ በኩል ታይቶ እና በሚመለከታቸው አካላት ተገምግሞ ባንካችን ተመራጭ የሚያደርገውን proposal ማቅረቡን ኮሚቴው ባደረገው ምዘና መሠረት ይፋ አድርጓል ፡፡ በተጨማሪም ዝቅተኛ የወለድ መጠን ማለትም 7% interest rate ከሌሎች ባንኮች ባነሰ መልኩ በማቅረቡና በማሸነፉ ከዩኒቨርስቲው የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ደርሶናል ብለዋል፡፡
ዩኒቨርስቲው ባመቻቸው እድል መሠረትም ባንኩ በዋናነት የዩኒቨርስቲውን ማህበረሰብ በልዩ ሁኔታ ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮፖዛል ያቀረበ ሲሆን ማንኛውም የዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ የሚበደረውን የገንዘብ መጠን 5%ቱን በባንኩ በመቆጠብ በባንኩ በኩል በተመቻቸው 7% interest rate / የወለድ መጠን በመበደር መጠቀም ይችላል።
አንደኛ :- ዩኒቨርሲቲው ስኬታማና ዉጤታማ ተከታታይ ድሎችን ማስመዝገቡን ተከትሎ ባንኩ ከዩኒቨርስቲው ጋር ለመሥራት ዕድል ማግኘቱ እጅግ ያስደሰተው ሲሆን ከንግድ ባንክ ካለው የትስስር አጋርነት በመቀጠል አብሮ ለመስራት በመፈለግ ዩኒቨርሲቲው የትኛውንም አይነት deposit በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በኩል ለማንቀሳቀስ ከሚገደድባቸው ገንዘብ ውጭ ያለውን በባንኩ በኩል እንዲደረግ በማሰብ፦
በሁለተኛነት ደግሞ የዩኒቨርስቲው ማህበረሰብን በተነሳሽነት ሰሜት ሰራውን እንዲከውን ከማድረግ አንፃር ከምንም በላይ ዝግጁ ሆኖ የስራ ድርሻውን እንዲወጣ ከማሰብ አንፃር ስራዉን በአግባቡ እንዲወጣ የእኔነት ስሜት ተሰምቶት በትክክል በሚሰራበትም ጊዜ እንደ አጠቃላይ ዩኒቨርሲቲው ውጤት ማምጣት ይችላልና ያን በማሰብ ባንኩ ለዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ በዋናነትም ለሰራተኛው የሚያስፈልጉትን ለምሳሌም ቤት ለመገንቢያ ፣ ቤት ለማደሻ : ቤት ለመግዢያ እንዲሁም የቤት መኪና ግዢ ብድር እንዲመቻችለት ሆኗል ። በተጨማሪም የ6 ወር ደሞዝ (gross salary) በ2 አመት የሚከፈል በ7% ወለድ መበደር የሚቻል መሆኑን የባንኩ ዋና ሰራ አስኪያጅ አቶ ተመስገን አቡዬ ተናግረዋል።
የውል ስምምነት ፊርሚያ ሂደቱም በዩኒቨርስቲው ፕሬዘዳንት ዶ/ር ሀብታሙ አበበ እና በባንኩ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ተመስገን አቡዬ በኩል ተከናውኗል። የብድር ሂደቱም የሚጀመረው ለዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ የውል ስምምነቱ ከተፈፀመበት ለት ማለትም ከነሀሴ 5/2013 ቀን ጀምሮ ካሉት ከ2 እስከ አራት ሳምንታት በኋላ ዩኒቨርሲቲውና ባንኩ የገቡትን የውል ስምምነት ተግባራዊ ሲያደርጉ ሠራተኞቹ የብድር አገልግሎቱን ማግኘት ይችላሉ። በውል ስምምነቱ ላይ የተጠቀሱ ነገሮች በዩኒቨርስቲውም በባንኩም በኩል ተግባራዊ ይደረጋሉ።
ነሃሴ 5/12/ 2013 ዓ.ም
ዘገባው የህዝብ ግንኙነት እና አለም አቀፍ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟላ መረጃዎችን ለመግኘት፣
ድረ ገጽ:- www.wcu.edu.et
ፌስቡክ:-Wachemo University-WCU
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
ዋቸሞ ዩኒቨርስቲ
WCU Wachemo university is situated in SNNPR region of ethiopia, Established in 2009 G.C. and registered in 2012 G.C. enrolling 538 students foe degree program in four faculties and 12 departments. Today our university having four Campus: Main Campus in Hadiya Zone, Duramee Campus Kembata Tembaro Zone an...
Truth is vaccine of soul