Anwar seid

Anwar seid

Share

Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Anwar seid, College & University, Addis abebe, Addis Ababa.

07/07/2023

የስም ሀብታም ነኝ። ማለቴ ብዙ መጠሪያ ስም ነው ያለኝ። ከ’ነሱ ውስጥ አንዱ ዛህራ ነው። ይህንን ስም ያወጡልኝ የቁርዓን ቤት ሸኼ ናቸው። ይወዱኝ ነበር። ለዛም ይሆናል ስም ያወጡልኝ። እሳቸው ከሌሉ በቦታቸው ይሾሙኛል። እናም እርሳቸውና የቁርዓን ቤት ልጆች በዚህ ስም ነው የሚጠሩኝ። ትዝ ይለኛል። እንደዛሬው ጁምዓ ሲሆን ቂርዓት አይኖርም ነበር። የእረፍት ቀን ነው። ቁርዓን ከምንቀራባት ትንሿ መስጊድ በቅርበት የምንኖር ልጆች በጠዋት ሄደን የሸኻችንን ጀለብያና ጥምጣም እናጥብላቸዋለን። ልብሳቸው እስኪደርቅ ፀሐይ እየሞቁ፣ ሲዋክና ሙስበሐቸውን ይዘው ጎርደድ እያሉ ይጠባበቁና ሰዓት ሲደርስ ለባብሰው ወደ ዋናው መስጅድ ይሄዳሉ።

ሸኻችን እንደዬአቅማችን ያስቀሩንና "በሉ ሀይያ ከርሩ!" ይሉናል። ያስቀሩንን በትእዛዛቸው መሰረት ደጋግመን እናጠናና "ተሰሙን" ብለን ዞረን እርሳቸው ጋር እንቀርባለን። ያኔ እንደ አሁኑ የቁርዓኑን ምዕራፎች በስም አናውቃቸውም ነበር። በምዕራፎቹ መጀመሪያ ላይ በሚገኘው አንቀፅ ቃል እንጂ። "የት ደረስሽ?" "ፈሰብቢህ!" ማን ጋር ነሽ? "ተባረክን አለፍኩ።" በአንዳንድ ምዕራፎች መጨረሻ ላይ ካለው ቃል ጋር ደግሞ አዛምደን እንገጥም ነበር። ለምሳሌ በሱረቱል ፈትሕ መጨረሻ ላይ ኢንነሁ ካነ ተውዋባ ካልን በኋላ የሸኻችን ላም ትንቧቧ እንል ነበር። ሱረቱዱሐ ላይ ደግሞ ወአምማ ቢኒዕመቲ ረብቢከ ፈሐድዲስ ብለን የሸኻችን ልብስ ሁሉም አዳዲስ እንላለን። ሌላው በሌሎች አካባቢዎች ሲቀራ አናባቢ ምልክቶች ፈትሐ፣ ከስራ፣ ዾማ እንደሚባሉት ደሴ ነስባ፣ ኪፍዻ፣ ኡርፋ ነበር የምንለው። የአሊፉን ነስባ አ…ኪፍዻውን ኢ…ኡርፋውን ኡ አ ኢ ኡ። የቁርዓኑን ቃላት አቀጣጥሎ የመቅራት ስልት "ሸድዳ" የሚባል ሲሆን (ከማጥበቂያው ሸድዳ የተለዬ ነው) ጀማሪዎች የሚጠቀሙት ፊደላቱን ነጣጥሎ ቀርቶ በመጨረሻ ማገጣጠም "ውጥጥ" ይባላል። ሌላው ነገር አድጌ ትርጉሙን ከተረዳሁ በኋላ እንደገመትኩት ምናልባት በልጅነት አንደበት የትርጉም መፋለስ እንዳያመጣ ከመስጋት ይመስለኛል ሸኾቻችን ሱረቱል ካፊሩንን ያዘልሉን ነበር። ሙስሊም ያልሆኑ ወዳጆቻችን ታድያ እንደ ከባድ ግኝት "ቁርዓን ውስጥ ሳይቀራ የሚታለፍ ሚስጥር አለ!" እያሉ ይንሾካሾኩ ነበር።😆

ከሁሉም ደስ የሚለው በዬደረጃው ደግሰን የምናበላው ነገር ነው። ከላይ ወደታች ስለነበረ የምንቀራው ኢቅራዕ ላይ የደረሰ ቆሎ ያበላል። ዐምመን የጨረሰ ድፎ ያስደፋና ከጆሊጁስ ጋር ያመጣል። እንዲህ እንዲህ እያለ ጊዜው ደርሶ ሲኸተምማ ደስታ ነው። ሰደቃ ነው። በግ ይታረዳ
ል።
እንዲህ እ
ንደዛሬው እንደ አጭር ኮርስ የሶስት ወር ለብ ለብ ሳይሆን በፊት የቁርዓን ኺታም ይሄን የመሰለ ወዝና ለዛ ነበረው።
My ቂርኣት style via atiqa ahmed ali

ጁምዓ ሙባረክ!💚💚💚

04/06/2023

Hasen taju!!!!!!!!!
በኡሁድን ዘመቻ የደረሰዉን ጊዚያዊ መጎሳቆልና ህመም ተከትሎ የወረዱ የቁርአን አንቀጾች 59 (አለ-ዒምራን 21-79) ሲሆኑ ባለፉት ጽሁፎች ያየነዉ ሁለቱን ብቻ ነዉ፡፡ እነርሱም ቢሆኑ ከቀናት በፊት በደረሰብን ስብራት የተጎዱ ስሜቶችን በቁርአን ለመጠገን የተመረጡ ናቸዉ፡፡ በእርግጥ የቁርአን ቅኝት፣ከታሪክ ተነስቶ፣ወቅታዊዉን ሁኔታ አስሶ፣ ዉጫዊዉን የትግል ሜዳ ፈትሾ፣ የነፍስያን የትግል መስክ ሀይሶ የሚያጽናናበት፣ ስብራትን የሚጠግንበትና የሚያስተምርበት መንገድ እጅግ ድንቅና ምሉእ፣እጅግ ማራኪ ከመሆኑ የተነሳ ተደጋግሞ ቢነበብም የማይጠገብ ሁልጊዜም አዲስ ነዉ፡፡ እነዚህን አንቀጾች ከነኋላ ታሪካቸዉ ለዓመታት ደጋግሜ ያነበብኳቸዉ ቢሆንም ዛሬም ለመጀመሪያ ጊዜ ያየኋቸዉ ያህል ያስደምሙኛል፡፡ የቁርአን ነገር ገራሚ ነዉ፡፡ ‹ላየንቀጢዑ ዐጃኢቡሁ›› ተብሎ የለ? አይተዉ የማይሰለቹት፣ ጠጥተዉ የማይጠግቡት፤ ኢማሙል አዕዞም 7000 ጊዜ አንብበዉ፣ ኢማሙ ሻፊዒ በየቀኑ እያኸተሙ ጥማቱ መች ወጣላቸዉ!? የሸኽ ሚስላይን ግጥም ልዋስ፡-

ምን የወጣ መጠጥ ሽታዉ እሚያሳብድ
ቢጠጡት አይሰለች ጥማት አያስወግድ
ከሆድ እማይጠፋ ስለቱ የማይበርድ
አከላት እንደጧፍ አያይዞ እሚያነድ
ላይ በላይ ግለቱ አክሎ እሚጀደድ

ሁሉንም ቢያወጉት ሆድ ባዶ ይቀራል፡፡ ከቁርአን የዑሁድ ቅኝት ከገረሙኝ ነገሮች መካከል ሁለቱን ብቻ አንስቼ ልሰናበት፡-

1. ቅኝቱ ሶስት የትግል መስኮችን ያጠቃለለ ነበር፡፡ የነፍስያን መስክ፣የአዕምሮን መስክና የዉጫዊ ትግል ሜዳን መስክ፡፡ ከሀጢአት ስለመመለስ፣ስለምህረት ልመና፣ስለመመጽወት፣ቁጣን ስለመቆጣጠር፣ስለ ይቅር ባይነትና በጎነት የሚተነትኑት አንቀጽ 130-136 የነፍስያን የትግል ሜዳ ይመለከታሉ፡፡ በዑለሞች ‹‹ትልቁ ጅሀድ›› የተሰኘና ብዙ ጥረት የሚጠይቅ ከባዱ የትግል መስክ ነዉ፡፡ በዚህ መስክ የተሸነፈ በሌላዉ ድል ቢቀናዉ እንኳ ከሳሪ ነዉ፡፡ ስለዚህ ‹‹አትራፊ ድል እንድትጎናጸፉ ወይም ሞታችሁ ዋጋዉ ከፍ ያለ እንዲሆን የነፍስያዉን የትግል ሜዳ ችላ እንዳትሉ›› የሚል መልዕክት ያስተላልፋል፡፡

በአዕምሮዉ የትግል ሜዳ ረገድ ስለአላህና ስለራስ፣ስለህይወትና ስለሞት፣ስለስኬትና ዉድቀት፣ ትግልን ከመሪ ግለሰብ ሳይሆን ከዕሴት ጋር ስለማስተሳሰር፣ ስለመሪና ተመሪ ግንኙነት ባህሪ ወዘተ በመለኮታዊ ጥበብ ግንዛቤ ያስጨብጣል፡፡

በዉጫዊዉ የትግል መስክ ረገድ በኡሁድ ዉሎ ላይ የታዩ ወታደራዊና ታክቲካዊ ግድፈቶችን ይሀይሳል፡፡

እነዚህ ሶስት የትግል መስኮች መሳ ለመሳ መሄድ ያለባቸዉ ናቸዉ፡፡ የነፍስያ ትግል ከተዘነጋ የትኛዉንም ጥረትና ስኬት ዋጋ ያሳጣል፡፡ የአመለካከት እነጻዉ ችላ ከተባለ ለተሳሳቱ ወይም ላልበሰሉ ዉሳኔዎች በመዳረግ ተጋላጭነትን ያስከትላል፡፡ የዉጫዊ ትግል መስክ ጠቀሜታ የታወቀ ስለሆነ ብዙ ማለት አያስፈልገዉም፡፡

2. የቁርአን ትምህርትና ተግሳፅ ዉጤት ያስመዘገበዉ ሳይዉል ሳያድር ነበር፡፡ ሶሀቦችን ከዚያ ሁሉ መጎሳቆል፣ስብራት፣ተስፋ መቁረጥ አዉጥቶ በደማቸዉ ዉስጥ አዲስ ሙቀት ለመርጨት ጊዜ አልወሰደበትም፡፡ ቁስላቸዉ ሳይደርቅ፣የአካል ስብራታቸዉ ሳይጠገን፣ነፍሳቸዉን በጨርቃቸዉ ቋጥረዉ ለአዲስ ተጋድሎ በአስደናቂ ብርታት እንዲሳሱ አደረጋቸዉ፡፡ ይህ ብርታት ይፈተነበትም ከስተት ዕዉን ሆነ፡፡ ይኸዉም ቁረይሾች በድል አድራጊ ስሜት፣ሙስሊሞችም በሽንፈት ስነልቦና ወደየመጡበት እንዲመለሱ ‹‹ሰይዱል ከዉነይን›› (ሰ0.ዐ.ወ) አልፈለጉም ነበርና ጠላትን ከኋላ ለማሳደድ በመወሰን ለተጎሳቆለ ሠራዊታቸዉ ጥሪ ሲያደርጉ ተአምር ታየ፡፡ ሁሉም ወደሞት ተሸቀዳደሙ- (አለዒምራን 172)
الَّذ

03/06/2023

ይህም ያልፋል 😐😐😐😐

03/06/2023

አሁንም ይዋሹናል። ልክ ክህደት እንደፈፀሙብን ሁሉ የጋራ ግብረሀይል እያሉ በግፍ የገደሏቸውን ዜጎች አፅም እያነደዱ ከአጥንታቸው ብራና ቀለም ፍቀው የተሳሳተ ሀሰተኛ መግለጫ ይሰጣሉ። በመሰረቱ አንድም መሰረታዊ የመረጃ ግብአት አቀባበልን መሰረት ያደረገ አዎንታዊ መግለጫ መስጠት አያቁም። አሰለጠናቸው የሚሏቸው የፖሊስ አባሎቻቸው እጅግ አረመኔና ኢሰዋዊ አረመኔ እንጅ አንድም የሰለጠነና የተገራ ህዝባዊ ሀይል የላቸውም።

መጅሊሱን እንደ ፍየል ማሰሪያ ገመድ ነው የናቁት። እንደተቋም አያከብሩትም። አይፈሩትም። ይህ የዋህ ህዝብ ስንቱን ችሎ የተሸከመውን ስረአት ይፈርስ አይመስላቸውም። በግድ ጦርነት እገጥማለሁ አትበሉ ተው ብለን ስንመክራቸው እናተ ሁሉንም የምታቁት ለምን ስሜታዊ ትሆናላችሁ ይሉናል። የህዝብ ልጅ ነን። ህዝብ የሰቀለን ህዝብ የተቀበለን በህዝብ የተወደድን እንጅ ከስረአታቸው ጋር ውል የለንም። ይህ መንግስት በሰራው ስህተት 238 ዜና ተሰርቶበታል። ይህ በአለማቀፍ ሚዲያ ጉዱ የተዘከዘከው መንግስት አደገኛ ኢስላም ፎቢያ እንዳለው የአለም ሙስሊም ኡለሞች የሰሩበትን ዜና አይተናል።

ለነሱ ይህ አደገኛ ሁኔታቸው መሆኑን አያቁም።
ስልጣን ከተረከቡ ጀምሮ አንድ ነጥብ 2 ሚሊየን የአገሪቱን ዜጋ አስገድለዋል። ልክ የኩዌትን ህዝብ ቁጥር ጨርሰዋል። 10 አመት የተደረገው የሶሪያ ጦርነትን በእጥፍ በልጠው ተገኝተዋል። ሙስናቸው አለምን ያስንቃል። የስልጣን መዋቅራቸው እጅግ ያፀየፈ ነው። ይህንን ጎደሎ ተሸክሞ የኖረ ህዝብ ላይ ጥይት ሲተኩሱ አያፍሩም። አይፈሩም። ለምን ከተባለ ንቀት አላቸው። ስለዚህ ልክ ማስገባት ያለበት ህዝቡ ነው።

ደም ለምደዋል። ገለው መዋሸት ውሸት ማቀነባበር ሱሳቸው ነው። 5 አመት አታለሉን አምስት አመት ገደሉን ረሀብ ጦርነት ዝርፊያ ማፈናቀላቸው ሁሉ ጆኖሳይድ ነው። በደም የሰከረ ስረአት ለማንም አይጠቅምም። ከአዲስ አበባ 400 km እርቀት ላይ በአማፂ እየተቆላ ዋና ከተማ ላይ የተቀመጠን ሰላማዊ ህዝብ ጥላቶቸ ናቸው የሚል ስረአት ነው አሁን ያለው ስረአት። እያበዱ የሚስቁ በሰው ደም ውስኪ የሚራጩ በደሀ ኢኮኖሚ የሚንደላቀቁ አንድም ለአገር ሰላም የማያስቡ ለሚመሩት ህዝብ የማይራሩ አደረጃጀቶችን ይዘው ነው እናበልፅጋችሁ የሚሉን።

ሱሌማን አብደላ

03/06/2023
27/05/2023

አንዋር ሰኢድ እባላለሁ። ኃይማኖቴን ከምንም በላይ የምወድ ሙስሊም ኢትዮጲያዊት ነኝ። መስጂድ የህልውናዬ መሰረት እና የማልደራደርበት የእምነት ተቋሜ ነው።

በተጨማሪም ቤተ‐እምነቶች የየትኛውም ስልጡን ከተማ ውበት እንጂ እንከን እንደማይሆኑ በፅኑ አምናለሁ። የሸገር ከተማ አስተዳደር ከተማዋን ከመስጅድ የማፅዳት ጅማሬውን እንዲያቆም እንዲሁም የፈረሱትን መስጅዶች በተሻለ አቋም እንዲገነባ አበክሬ እጠይቃለሁ።

#ሙስሊምጠልነት

07/05/2023

ደወል ሲደወል
🍁 🍁 🍁
በጥልቅ እንቅልፍ ውስጥ ሰጥሜ እያለ የቤቴ በር በኃይል ተንኳኳ። «በዚህ ደረቅ ሌሊት በሩን የሚያንኳኳው ማን ነው?» በማለት በድንጋጤ ተነሳሁ። ከቅርብ ዘመዶቼ አደጋ ያጋጠመው እንዳይኖር ሰጋሁ። አንደበቴ ተርበተበተ። እጆቼ ተንቀጠቀጡ። እያለከለኩ ወደ በሩ አመራሁ። ፈራ ተባ እያልኩ በሩን ስከፍተው እንግዳ የሆነ ፍጡር ከፊቴ ተገትሯል።

«ጤና የለህም እንዴ ?? ለመሆኑ ሰፈሩን እና ቤተሰቦቼን ሰላም እንደነሳህ ታውቆሃል? ማን ነህ አንተ ??» አልኩት።

«ተረጋጋ ! ካንተ ውጭ በሩ ሲንኳኳ የሰማ አንድም ሰው የለም። አሁን ሰዓት የለንም። ፈጠን በል እንሂድ» አለኝ።

«ወዴት ነው የምንሄደው?» አልኩት።

«እኔ መልዓከ ሞት ነኝ። የምድር ቆይታህ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ሊገባደድ የቀሩህ ደቂቃዎች ኢምንት ናቸው። አሁን ጨርቄን ማቄን ሳትል በለበሰከው የመኝታ ልብስ ተከተለኝ» አለኝ።

ፊቴ በእንባ ጎርፍ ታጠበ። ሰውነቴ ከብርድ አምልጠው በእናታቸው እቅፍ ውስጥ ለመግባት እንደሚሽቀዳደሙ ጫጩቶች ተርገፈገፈ። መልዓከ ሞትን ቢያንስ ተጨማሪ የአስር ደቂቃ ዕድል እንዲሰጠኝ ተማጸንኩት። ለበርካታ ቀናት ያስቀየምኳት ሚስቴን ይቅርታ ለመጠየቅ እና በእንቅልፍ ዓለም ውስጥ ያሉ ልጆቼን እንድስማቸው ፈቃዱን ጠየኩት። ይህ ጉዳይ በጭራሽ የማይታሰብ እንደሆነ ቁርጡን ነገረኝ።

«ከሁለት ወራት በላይ ወላጆቼን በአይነ ስጋ አላየሁም። በስልክም እንደምን ናችሁ ብዬ አላናገርኩም። እባክህን አንዴ ድምጻቸውን እንድሰማ ፍቀድልኝ ?» በማለት በጉልበቴ ተንበርክኬ ለመንኩት። ሰማይ ከፍ መሬት ዝቅ ቢል የማይሆን ነገር እንደሆነ አረዳኝ።

«ባለቤትህን ከማስቀየምህ ሌላ ይህን ያህል ጊዜያት የወላጆችህን ደህንነት ለማወቅ አለመጣርህ ትልቅ ነውር ነው። ጥያቄህ በፍጹም ተቀባይነት የለውም። የመጨረሻ ህቅታህ ከሰዓቷ ዝንፍ የማትል መሆኑን ማወቅ አለብህ። ስማ አንተ ክፉ የሆንክ ! በል አሁን ዓይኖችህን ክፈት» ሲለኝ ድንገት ከእንቅልፌ ባነንኩ።

«በህልም ዓለም ስዋኝ ኖሯል። ከእንቅልፌ የነቃሁት ከሌሊቱ 9:00 ላይ ነው። አልጋዬ ላይ ቁጭ ብዬ እየዬዬን አቀለጥኩት። ፊቴ በእንባ ጎርፍ ወረዛ። በክስተቱ አላህ በምድር ላይ የመኖር ዕድል ሰጥቶኝ እኔን ለማስተማር ያሳየኝ ህልም መሆኑን ተረዳሁ። ሚስቴ ከእንቅልፏ እንድትነቃ በማድረግ ጉዳዩን አጫወትኳት። ይቅርታ አደረገችልኝ። ልጆቼ ከተኙበት አልጋ ላይ በፍቅር ተጠመጠምኩባቸው። ሲነጋ ስንቄን ሸክፌ ወደ ወላጆቼ ቤት አቀናሁ። ይቅርታ እንዲያደርጉልኝ ተማጸንኩ። ጥያቄዬም ተቀባይነት አገኘ።» በማለት አንዱ ባለ ታሪክ ያጫውተናል...

ምጥን አስተምህሮ
🍁🍁🍁🍁🍁🍁
ባቡሩ ፈጣን ነው። እስከዛሬ በመንገዱ ላይ ባሉ ፌርማታዎች ቆመው የሚጠብቁ ብዙ ተጓዥ መንገደኞችን እየለቀመ አንስቷል። የኛም ወረፋ ደርሶ ነፍስና ስጋችንን ለመነጠል ተልዕኮ የተሰጠው መልዓከ ሞት የቤቶቻችንን በር ከማንኳኳቱ በፊት ቀሪ የቤት ስራዎቻችንን ንቁ ሆነን ከስር ከስሩ ለመቀነስ እንሞክር።
Mohammed Ahmed

06/05/2023

"Some have reasons to Live for
Some have reasons to Kill for, and
Other have reasons to die for” … John Wick 4

የአርበኞች ቀን ሲነሳ በተለያዬ ጊዜ ለሃገር (ህዝብ) ብለው የወደቁትን እናስታውስና እኛስ ስለ እኛና ስለሃገራች የት ነው ያለነው ብለን እንጠይቃለን? መልሱ የሚያስፈራን ከሆነ ማንሳትም አንፈልግ!

አባቶቻችን እንደነገሩን አንድን "ጠላት" ሲታገሉ የሃሳብ ልዩነት ሳይኖራቸው አልነበረም - ይልቁንም የህልውና ጉዳይ ሲሆን አንዱ ያንዱን እንዳከበረ ቅድሚያ ሰጥተው ሃገር ላይ አንድ ናቸው::

ለምሳሌ:- ከጣልያን ጋር የታገሉትን አርበኛ ሼህ ጠልሃ ጃእፈርን ታሪክ ብንወስድ ከሼህ አህመድ ዳና (ዳንዩል አወል) ጋር ሰፊ ተቃርኖ ነበራቸው:: ጉዳዩ ደግሞ እንዲህ ነው:

እፄ ዩሃንስ በወሎ ዘማቻቸው ያድኑ የነበሩት የሙስሊሙን ታላላቅ ምሁናራን ነበር:- በዋናነት ከሚጠቀሱት ጀማሉዲን አንይና ተማሪወቻቸው እንዲሁም ጦልሃ ጃእፈር ናቸው:: በቀጥታ መያዝ ያልቻሉትን ሼህ ደግሞ በጣም በሚወዱዋቸው መምህራኖቻቸው በግድ ያጠምዱ ነበር::

ሼይ ጠልሃ ጃእፈር ሼይሃቸው በጣም ይወዳሉ እና ይህን ኢንተለጀንስ የደረሳቸው አፄ ሼሃቸውን አድነው ከያዙ በሁዋላ ተማሪያቸው ጠልሃን በጣም ናፍቀህኛልና በቶሎ መጥተህ እየኝ ብለው መልእክት ያሳያሉ::

የጦልሃ ጃእፈር ደርሶች ሼሃቸው ያሉበት የዩሃንስ ክልል ነው ብለው ቢያስጠነቅቁም የሼሃቸው ነገር ያልሆነላቸው ጦልሃ ጃእፈር - አልቀርም ብለው ይሄዳሉ:: ደረሶቻቸውም ካልክ እንግዲህ ብለው እጅበው ይሄዳሉ::

እንደደረሱም - መጀመርያ የሼሁን መኖሪያ ካጠሩ በሁዋል ጠልሃን አስገብተው እነሱ ዙሪያውን ከበው ይጠብቁ ጀመር:: ጠልሃ ሼይሃቸውን ሲዘይሩ- እንዲት ልጅ እየሮጠች ከቤት ወጣች:: የዚህች ልጅ ሩጫ ያላማራቸው ደረሶች ጠልሃ ቶሎ እንዲወጡ ሊናገሩ ገቡ::

ልጅቱ የወጣችው የጠልሃን መምጣት ለዩሃንስ ወታደሮች ለመንገር ነበርና ሰፈሩ ወዲያውኑ በጦርነት ተተራመሰ:- በዩሃንስና በጦልሃ ጃእፈር ወታደሮች መካከል::

ጦልሃም የሼሃቸውን ግንባር ስመው ሊወጡ ሲሰናበቱ - ሼሃቸው እጃቸውን ይዘው "እጅህን ለዩሃንስ ስጥ ባንተና/ደረሶችህ የተነሳ ሙስሊሞች እያለቁ ነው" ይላሉ:: ጦልሃም ሊያስለቅቁ ሞክረው እምቢ ሲሉዋቸው ግዜ በሳንጃ የሼሃቸውን እንገት ቆርጠው እጃቸውን በማስለቀቅ ያመልጣሉ::

ከብዙ ትግልና ግዜ በሁዋል ዩሃንስን በሌላ ግንባር ከሼይሃቸው ጀማሉዲን አንይ ጋር ሆነው ሲታገሉ ተማርከው ያመለጡት ዳንዩል አወል ጋር ይገናኙና ያወራሉ:: ከወሬወቻቸው መሃል:-

ዳንዩል አወል:- " ያ ጦልሃ እኔ ግን የሚጨንቀኝ ጌታህ ሙስሊሞችን (ሼይህህን እና ደረሳወቹን) ለምን ጨፈጨፍክ ብሎ ሲጠይቅህ ምን ብለህ እንደምትመልስ ነው?"

ጦልሃም መለስ አድርገው "ያ ሼይህ እኔ ደግሞ የሚጨንቀኝ እሱ ሳይሆን - ሙስሊም ወንድሙን አሳልፎ የሰጠን "ከሃዲ" ለምን አስተረፍካቸው? ለምን አልጨረስካቸውም? ብሎ ቢጠይቀኝ ምን ብዬ እንደምመልስ ነው::" ብለው መለሱ::

አስቡት ሁለቱ ጉምቱ ምሁራን (አንድ ህዝባዊ አላማ ቢኖራቸውም) የተለያዩበት ጉዳይ ምን ያክል ከባድ እንደነበር:: ያም ሆኖ ግን ከልዩነታቸው ጋር ሆነው በሰለጠነ መንገድ ነበር የሚነጋገሩት!

ልዩነትን ጠረጴዛ ዙሪያ ማምጣት ከመማርም ከማወቅም በላይ ስልጣኔንና ብስለትን (wisdom) ይጠይቃል::

ያ ሁሉ የታገሉት ድካማቸውንና ደማቸውን እንዲህ ከንቱ እንደምናደርገው ቢያውቁ ምን ይሉ ይሆን?!

#የአባቶቻችን ልጆች ያድርገን

Nush
Harare, .
ViaM sani

31/03/2023

ስለ ቁርኣን በጥቂቱ እንናገር!!
-----
(በአፈንዲ ሙተቂ)
------
ቅዱስ ቁርኣን 114 ምእራፎች (ሱራ) እና 6236 አንቀጾች (አያህ) ያሉት የአላህ ቃል ነው። በየወሩ ለማንበብ በሚያመች መልኩም በሰላሳ ጁዝእ (ክፍሎች) ተከፋፍሏል።

ረጅሙ የቁርኣን ሱራ "አል በቀራህ" ሲሆን እርሱም 286 አንቀጾች አሉት።

አጭር የሆኑት የቁርኣን ሱራዎች "አል ዐስር"፣ "አል ከውሠር" እና "አል ነስር" ሲሆኑ እያንዳንዳቸው ሶስት አንቀጾች አሏቸው።

ረጅሙ የቁርኣን አንቀጽ ስለ ብድርና ውል የሚያወሳው የሱረቱል በቀራህ 282ኛ አንቀጽ ነው። ይህ አንቀጽ ለብቻው የአንድ ገጽ ርዝመት አለው።

አጫጭሮቹ የቁርኣን አያዎች "ጣሃ"፣ "ሃ ሚም" እና "ያ ሲን" ናቸው። እነዚህ አንቀጾች በሁለት ፊደላት ብቻ ነው የተዋቀሩት።

መጀመሪያ የወረደው የቁርኣን ሱራ "አል ዐለቅ" ሲሆን መጨረሻ ላይ የወረደው ሱራ "አል ነስር" ነው።

በአንቀጽ ደረጃ ደግሞ በቅድሚያ የወረዱት የሱረቱል ዐለቅ አምስት የመጀመሪያ አንቀጾች ሲሆኑ መጨረሻ ላይ የወረደው የሱረቱል ማኢዳ ሶስተኛ አንቀጽ (አያህ) ነው።

የቁርኣን ሱራዎች በመጽሐፉ ውስጥ የተቀመጡት በወረዱበት ቅደም ተከተል ሳይሆን ለውሀል ማሕፉዝ (ጥብቁ ሰሌዳ) በሚባለው ታላቁ ሰሌዳ ላይ በተጻፉበት መልክ ነው።

የቁርኣን አወራረድ ሁለት መልክ አለው። በመጀመሪያ ከለውሐል ማሕፉዝ (የተጠበቀው ሰሌዳ) ተወስዶ "ለይቱል ቀድር" በምትባለው ታላቋ የረመዳን ሌሊት፣ በቅርቢቷ ሰማይ በሚገኘውና ቤይቱል ማእሙር በሚባለው ቤት ወደ ጂብሪል ወርዷል።

ቁርኣኑ ወደ ጂብሪል የወረደው በተሟላ ሁኔታ እና በለውሐል ማሕፉዝ ላይ ያለውን የሱራዎችና የአያዎች ቅደም ተከተል በጠበቀ መልኩ ነው።

የነቢዩ ሙሐመድ መልእክተኛነት ከተበሰረ በኋላ ደግሞ ጂብሪል ቁርኣኑን በምእራፎችና በአንቀጾች እየከፋፈለ በ23 ዓመታት ውስጥ በነቢዩ (ሰዐወ) ላይ አውርዷል።

ነቢዩ ሙሐመድም (ሰዐወ) ወሕዩን ከጂብሪል መቀበል የጀመሩት በወርሃ ረመዳን "ለይቱል ቀድር" በምትባለው ትልቋ ሌሊት ነው። "ረመዳን" የወራቶች ንጉሥ የሚባለው በዚሁ ምክንያት ነው።
----
አላህ ለይቱል ቀድርን ከሚወፍቃቸው ባሮቹ ያድርገን።
አሚን
አሚን
አሚን
አሚን
አሚን
----

26/03/2023

በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የሚተኩ የስራ ዘርፎች
ከሰው ልጅ ተነጥቀው በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የሚተኩ የስራ ዘርፎች የትኞቹ ናቸው?
March 25, 2023
በቀጣዮቹ ጥቂት ዓመታት በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ሊያዙ ይችላሉ የተባሉ የዓለማችን ስራዎች ይፋ ሆነዋል
በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የሚተኩ የስራ ዘርፎች የትኞቹ ናቸው?
በየጊዜው ይፋ የሆኑ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎች የሰው ልጆችን ህይወት በማቅለል ይታወቃሉ።
እነዚህ ፈጠራዎች በየጊዜው እየዘመኑ እና እየተሻሻሉ የመጡ ሲሆን አንዳንዶቹ መልሰው የሰው ልጆችን ፍላጎት ሲጋፉ ይስተዋላል።
በቀርቡ በአሜሪካው ኦፕን አይ ኩባንያ ይፋ የተደረገው ቻትጅፒቲ የቴክኖሎጂ ስራ በሚሰጣቸው አገልግሎቶች ብዙዎችን አስገርሟል።
የሙዚቃ ግጥም እና ዜማን ጨምሮ በርካታ ስራዎችን ይሰራል የተባለው ቻትጅፒቲ አሁን ደግሞ በሰው ልጆች ይሰራሉ የተባሉ እልፍ ስራዎችን በመረከብ በፍጥነት ያከናውናል ተብሏል።
ጎግል የስራ ማመልከቻን ጨምሮ ስራን የሚያቀል ሰው ሰራሽ አስተውሎት አስተዋወቀ
የቻይናዋ ሮቦት ዜና አንባቢ አለማቀፍ ትኩረት ስባለች
የሰው ልጅ ህዝብ ቁጥር እና የስራ ፍላጎት እየጨመረ ባለበት በአሁኑ ወቅት ይህ ቴክኖሎጂ ሰዎችን ተክቶ መስራቱ ጉዳቱ ያመዝናልም እየተባለ ይገኛል።
ዩሮ ኒውስ ባለሙያዎችን አነጋግሮ ይዞት በወጣው ዘገባ መሰረት በቻትጅፒቲ ቴክኖሎጂ ሊተኩ የሚችሉ ስራዎችን እንደሚከተለው አስቀምጧል።
እንደ ባለሙያዎቹ አስተያየት በቻትጅፒቲ ቴክኖሎጂ ብዙ ስራዎች በከፊል እና ሙሉ ለሙሉ ሊተኩ ይችላሉ ብለዋል።
ከቋንቋ ጋር የተያያዙ 86 የስራ ዘርፎች ሙሉ ለሙሉ በቻትጅፒቲ ሊተኩ ይችላሉ የተባለ ሲሆን በአጠቃላይ 15 ጠቅላላ የሙያ መስኮች በዚሁ ቴክኖሎጂ ይተካሉ ተብሏል።
ከዚህ በፊት በሰው ልጆች ሲከናወኑ የነበሩ በቀጣይ ግን ሙሉ ለሙሉ በቻትጅፒቲ ቴክኖሎጂ ይተካሉ ከተባሉ ሙያዎች ውስጥም የሒሳብ ስራ፣ የግብር መረጃ ዝግጅት ፣ የፋይናንስ ትንታኔዎች፣ ድርሰት እና ጽሁፍ ስራዎች፣ የዌብሳይት ዲዛይን እና ማስተዳድር ስራዎች ዋነኛዎቹ ናቸው።
እንዲሁም የጥናት ስራዎች፣ትርጉም ስራዎች፣ የህዝብ ግንኙነት ፣ የእንስሳት ሳይንስ እና ከቋንቋ ጋር የተያያዙ ሌሎች ስራዎችም ሙሉ ለሙሉ እና በከፊል በዚህ ቴክኖሎጂ ሊከናወኑ እንደሚችሉ ተገልጿል።
በተጨማሪም የጋዜጠኝነት ስራዎች፣ የአየር ንብረት ፖሊሲ፣ ክሊኒካል ዳታ ፣ የህግ ጉዳዮች ጽህፈት፣ የፍርድ ቤት ሪፖርት እና የአርትኦት ስራዎች በቻትጅፒቲ ሊከናወኑ እንደሚችሉ በዘገባው ላይ ተጠቅሷል።
ይሁንና ይህ የአርቲፊሻል ቴክኖሎጂ የተሳሳቱ ውጤቶችን እና ሪፖርቶችን የመስራት እድሉ ከፍተኛ ሊሆን እንደሚችል ተሰግቷል።

Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Website

Address


Addis Abebe
Addis Ababa