African Chess Academy, Ethiopia

African Chess Academy, Ethiopia

Share

" ህፃናት ላይ የማትሠራ ሀገር ትጠፋለች "
/ ሀዲስ አለማየሁ /

09/03/2023

ዓለማቸውን በመገናኛ ብዙኃን የሚነጠቁ ኢትዮጵያውያን ሕጻናት

በተለያዩ ለአዋቂዎች በሚሰናዱ የመዝናኛ ፕሮግራሞች ላይ ሕጻናት እንግዳ ሆነው ይቀርባሉ።
ስለዚህ ውጥንቅጥ ስለበዛበት ዓለም፣ ፖለቲካ እና ማኅበራዊ ሕይወት ምስቅልቅል ይጠየቃሉ።
በሚሰጡት ምላሻም የሞቀ ጭብጨባ ይቀበላቸዋል፤ የማያቋርጥ የሳቅ ምንጭ ይሆናሉ።
ይህንኑ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ሚሊዮኖች እየተቀባበሉ ይመለከቱታል።
ታዳጊ ሕጻናቱ በጨቅላ እድሜያቸው ዝናን ይከናነባሉ።
ፕሮግራሞቹ የተመልካችን ቀልብ እና ልብን መሳብ ዋነኛ ግባቸው ነው።
በርካታ ቁጥር ያለው ተመልካች ማግኘት ይፈልጋሉ።
ከዚያ ደግሞ ዝናና ገንዘብን ማትረፍ የዓላማቸው አንዱ አካል ነው።
እነዚህ አንደበታቸው የሚጣፍጥ፣ ሲያይዋቸው የሚያሳሱ ልጆች የበርካቶችን ቀልብም ልብም የመግዛት አቅማቸው ተፈጥሯዊ ነው።
የመዝናኛ ፕሮግራሙን ከሕጻናት ጋር አስተሳስረው የሚቀርፁ አካላት አብረው ታሳቢ ያደረጉት ይህንን የልጆች ተወዳጅነትን ነው።
እውነትም በርካታ ተመልካች በማግኘት ፍላጎታቸውን ያሳኩ ይመስላል።
የልጆች ዕድገት እና የሕጻናት ሥነ ልቦና ባለሙያዎች ግን የፕሮግራም አዘጋጆቹ እንዲሁም ወላጆች የዘነጉት ነገር መኖሩን ይናገራሉ።
እኛም የተዘነጋው ቁም ነገር ምንድን ነው? ስንል ጠይቀናቸዋል።

For more info BBC Amharic

Photos from African Chess Academy, Ethiopia's post 08/03/2023

ዩዴሞኒያ 28-ዶ/ር ሌሊ ሌንሳሞ
====================
ሌሊ በትምህርቷ በጣም ጎበዝ ናት። አባቷ ደግሞ ዶክተር ነው። ስለዚህ 12ኛ ክፍል ጨርሳ ዩኒቨርሲቲ ስትገባ ምን እንደምትማር ግልፅ ነበር። ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ህክምና ትምህርት ቤት ገባች። እነዛ እንኳን ተነበው ተቀደው የማያልቁ መፅሀፎችን አነበበች። እጅግ ብዙ እንቅልፍ የለሽ ዲውቲዎችን ህክምና እየሰራች አሳለፋ ዶክተር ሆና ተመረቀች። እኔ ሳይካትሪ ስፔሻላይዝ እያደረግሁ እሷ ደግሞ አምስተኛ አመት ህክምና ተማሪ ሆና የሳይካትሪ ሴሚናር ስታቀርብ አይቼያት አውቃለሁ። "ምናለ ሳይካትሪ በተማረች!" ብዬ ተመኝቼ ነበር።

ከምረቃ በኋላ ግን ሼክስፒራዊ ጥያቄው አፍጥጦ መጣ። መሆን ወይም አለመሆን። ዶ/ር ሌሊ ከልጅነቷ ጀምሮ ሙዚቃ ትወዳለች። ደግሞ ተስጥኦም አላት። ህክምናን ትወዳለች። ሙዚቃን ደግሞ የበለጠ ትወዳለች። ኑረታዊ ጭንቀት (Existential anxiety) ግራ አጋባት። በመጨረሻ ከባዱን ውሳኔ ወስና ልቧን ተከተለች። She flirted with medicine and married music.😂 የስራ አቅጣጫዋን መቶ ሰማኒያ ዲግሪ ቀየረች። ምክኒያቷን ስትጠየቅ "ውስጥህ የሚንቦለቦል ፍላጎት ካለህ ከመቀየር ውጭ አማራጭ የለም!" ትላለች።

ለውጡ ቀላል አልነበረም። ሆኖም ጠንክራ በመስራት እንዲሁም በውስጧ ላለው ተስጥኦ ብዙ ነገሮችን መስእዋት በማድረግ አሁን መስመር እየያዘላት ነው። የJulian Marley ጊታሪስት ከሆነው Jamie Hinckson ጋር አብራ መስራት ጀምራለች። ነገ የት እንደምትደርስ መገመት ያስቸግራል።

ዶ/ር ሌሊ እውነተኛ ማንነቷን ስታወጣ ይቅርታ አትጠይቅም። She is unapologetically authentic. በየትኛውም ዘርፍ ቢሰማሩ የከፍተኛ ትምህርት መማርና መጨረስ መልካም ነው። ተስጥኦና ፍላጎት ሲገጣጠሙ ደግሞ ልብን መከተል የተሻለ ጥሩ ነው።

'ባሉ ዳንቻሆ' የሚለው ሙዚቃዋ በሲዳምኛ "ሁሉ መልካም" ማለት ነው። Way to go Leli.
ዩዴሞኒያ ለሁላችን!!!! ባሉ ዳንቻሆ!!!!!!
ዶ/ር ዮናስ ላቀው።

የአፕል ካምፓኒ መስራችና ፈጣሪ የነበረው ስቲቭ ጆብስ ከመሞቱ በፊት በስታንፎርድ ዩንቨርስቲ የ2005 ዓ.ም. ተመራቂ ተማሪዎችን ለመመረቅ ተገኝቶ ነበር፡፡ በዚህ የምርቃት መድረክ ላይ የተናገረው ነገር የብዙ ሰዎችን ልብ ያነሳሳ ነበር፡፡ በዛን ሰሞን ጆብስ የPancreatic ካንሰር ሕመምተኛ የነበረ በመሆኑ በሕይወት ሊቆይ የሚችለው ከሶስት እስከ ስድስት ወር ብቻ እንደነበር ሐኪሞቹ ነግረውት ነበር፡፡ ሞት አፋፍ ላይ ሆኖ ተመራቂ ተማሪዎቹ ሶስት ጥያቄዎችን ለራሳቸው ይጠይቁ ዘንድ መክሮአቸዋል፡፡ ጥያቄዎቹም፡-

1ኛ፡- ‹‹መኖር የምፈልገውን ሕይወት ነው እየኖርኩ ያለሁት? የምፈልገውንስ ነው እየሰራሁ የምገኘው? (Am I living the life that I want and doing the work that I want to do?)››

ጆብስ በሕይወታችን ደስተኛ የሚያደርገን የምንፈልገውን ሕይወት በመኖርና የሚያስደስተንን ስራ በመስራት ነው ሲል ይገልፃል፡፡ ብዙዎቻችን በተኮረጀ ሕይወት ዕድሜአችንን እያቃጠልን እንገኛለን፡፡ ሰው እንዴት የሌላ ሰውን ሕይወት ይኮርጃል? ሰው መነሻ ሃሳብ ሊኮርጅ ይችላል፤ የሌላ ሰው ህይወት ግን አይኮረጅም!

2ኛ፡- ‹‹ዛሬ የሕይወቴ የመጨረሻ ቀን ቢሆን ኖሮ ልሰራ የምፈልገውን ለመስራት እችላለሁን?›› (If today were the last day of my life, would I want to do what I am about to do today?)››

ለዚህ ጥያቄ መልሳችን ‹‹አይደለም›› ከሆነ ልንለውጣቸው የሚገቡን ብዙ ነገሮች አሉ ማለት ነው፡፡ መልሳችን ‹‹አዎ›› እስከሚሆን ድረስ ጥያቄአችንን ማቋረጥ እንደሌለብን ይመክረናል፡፡ ይሄን ጥያቄ ለመመለስ ከራሳችን ጋር ግብግብ ልናደርግ ይገባናል ሲል ያሳስባል፡፡

3ኛ፡- ‹‹እየሰራሁ ያለሁት የምወደውን ነው? (Am I doing what I love?)››

በነገራች ላይ የምንፈልገው ሁሉ የምንወደው ላይሆን ይችላል፡፡ አንዳንዶቻችን የፍላጎታችን ምንጭ የሌሎች ፍላጎት ሊሆን ይችላል፡፡ ስለዚህ መጀመሪያ ፍላጎታችን የራሳችን መሆኑን ማረጋገጥ አለብን፡፡ ሁለተኛ የምንፈልገው ነገር የምንወደው መሆኑን መፈተሽ ይገባናል፡፡ ሶስተኛ የወደድነውን ካገኘነው በኋላ የሚያስደስተን መሆኑን ቀድመን ልንረዳው ያስፈልጋል፡፡ የወደድነው ሁሉ ካላስደሰተን ትክክለኛ ውዴታችን አይደለም ማለት ነው፡፡ ስለዚህ እውነተኛ መውደዳችን ምን ላይ እንደሆነ ቀድሞ መመርመር ይገባናል ማለት ነው፡፡ አለበለዚያ ትርጉም የሌለው የቅብዝብዝ ሕይወት ነው የምናሳልፈው፡፡

ለዚህ ነው እህቴ ስቲቭ ጆብስ ‹‹Your time is limited, so do not waste it living someone else’s life‹‹ የሚለን፡፡ አዎ ዕድሜያችን ውስን ነው! የሌላ ሰውን ኑሮ በመኖር የህይወት ዘመናችንን አናባክነው፡፡

Photos from African Chess Academy, Ethiopia's post 25/02/2023

ማሰብን ለነሱ መሸከምን ለኛ ያደረገው ማነው ?
በእናቶች አሳቢነት የማን አገር ነው ያላደገው ?
" በምድር ላይ የመጨረሻው ምርጥ ህይወት ፥ ለሌሎች በረከት መሆን ነው።" / ኦሊቃ ድንግል /
የእናት በረከት ከወላድነቷ ይጀምራል። ማሰብን ስትጨምርበት ደግሞ ወደ በረከቶች ይቀየራሉ።
" አንድን ወንድ ስናስተምር: አንድን ወንድ አስተማርን ይባላል። አንድን ሴት ስናስተምር ትውልድ እንዳስተማርን ይቆጠራል። "/ ብሪንግሃም ያንግ /
ያልተሰራች እናት የተሠራ ልጅ ከየት ታመጣለች ?
በሌላ አባባል ለሴቶች እና ለህፃናት ቅድሚያ የማትሰጥ ሀገር ከሥሯ የተቆረጠቾ ዛፍ ትሆናለች ለማለት ነው።
ሴትን አስተምሮ ማብቃት? አምስት ልጆቿንም አብረው እንደተማሩ ስለሚቆጠር ነው ሀገር የተማረ ወይንም አሳቢ ትውልድ አላት የምትባለው።

“ እናትነት በዓለም ላይ ትልቁ ቁማር ነው።
እሱ የከበረ የሕይወት ኃይል ነው።
በጣም ትልቅ እና አስፈሪ ነው - ማለቂያ የሌለውም ብሩህ ተስፋ ነው። " /- ጊልዳ ራድነር /
ፀሐፊዋ ቁማር የሚለውን ቃል የተጠቀመችው፦ ልጅ በመውልድ ውስጥ እናቶች የራሳቸውን ህይወት ስለሚያጡ ነው።

Photos from African Chess Academy, Ethiopia's post 23/02/2023

ስፖርት እና ልጆች
በዓለም ላይ ስምንት መቶ የሚሆኑ ለአካልና ለአዕምሮ የሚጠቅሙ የተለያዩ ዓይነት ስፖርቶች ይገኛሉ። ዓላማቸውም ሰውን ከሰው እያወዳደሩ ወቅታዊውን አቋም ማሳየት ነው። ግቡም በውድድር አዙሪት ውስጥ የስፖርተኛውን የአካል እና የአእምሮ ጥንካሬ ማውጣት እና ጤነኜና አምራች ኃይል ለሀገር ማቅረብ ነው። ለዚህም ይመስላል በስፖርት ውድድሮች ውስጥ ቋሚ አሸናፊ የለም የሚባለው። ስፖርት በአሁኑ ዘመን ደግሞ ራስንና ሀገርን ከማስተዋወቅ አልፎ የከፍተኛ ኢንቨስትመንት ምንጭ እየሆነ ነው። ሀገራትም ውድድሮችን በማዘጋጀት ከፍተኛ ትርፍ ያጋብሳሉ። ለምሣሌ ኤርትራውያን ባንዲራቸውን ለማውለብለብ ሠላሣ ዓመት የፈጀባጀውን የትግል ጉዞ ስፖርተኞቿ ዓመት ሣይሞላ በዓለም አደባባይ ላይ ለመስቀል በቅተዋል። ወላጆችም ይሀንን በመረዳት ልጆቻቸው የዚህ በረከት ተቋዳሽ እንዲሆኑ ስፖርት የህይወታቸው አካል እንዲሆን ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። ለምሳሌ ጃፖኖች ከስድስት ወር ልጅ ጀምሮ ውድድር ያካሂዳሉ።

በአገራችን ሰባ ፐርሰንት ወጣት በሆነበት አገር ሁሌ ስለ ሥራ አጥ ከመናገር እና እርሻ ብቻ ነው መፍትሔ ማለት ? ዓለምን ያአለመረዳት ይመስላል። በሀገራችን ስፖርት እንደ ሥራ ዕድል አይታይም ማለት ነው ?
ልጆቻችንን ወደፊት ሁለት ምርጫ ይጠብቃቸዋል። ሶስተኛ ምርጫ ግን የላቸውም!!!
ሀ) ታዋቂ ስፖርተኛ ሁነው መደነቅ ?
ለ ) ተመልካች ሁነው ሌሎችን ማድነቅ ?
ይሄን አለመወሰን በራሱ ውሣኔ ነው።

Photos from African Chess Academy, Ethiopia's post 22/02/2023

ኢትዮጵያ እንኳን ደስ አለሽ=እልልልልልል!!!

" ነገ የምንፈልጋትን ሀገር ለመገንባት በዛሬው ትውልድ ላይ መሥራት ይኖርብናል። "ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 14 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)ነገ የምንፈልጋትን ሀገር ለመገንባት በዛሬው ትውልድ ላይ መሥራት ይኖርብናል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለፁ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በልደታ ክፍለ ከተማ ሳር ቤት አካባቢ እንደ አዲስ የተገነባውን የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ ስራ አስጀምረዋል፡፡

የስፖርት ማዘውተሪያው ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት እና በሁሉም የበቃ ትውልድ ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

በተጨማሪም በአካል፣ በሥነ ምግባር እና በሥነ ልቡና የዳበረ ትውልድ ለመፍጠር የሚያግዝ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ ገንብተናል ሲሉም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል፡፡

ነገ የምንፈልጋትን ሀገር ለመገንባት በዛሬው ትውልድ ላይ መሥራት ይኖርብናል ሲሉም ገልፀዋል። በየአካባቢው ተመሳሳይ የስፖርት ማዕከላትን እያስፋፋን እንቀጥላለንም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ።
==================//==============
2ተኛው ሠባብሮ የገባው ዜና ደግሞ በአዲስ አበባ ከተማ አየር ጤና አካባቢ የሚገኘው ኢባዱ ረህማን መስጊድ ለወጣቶች በማሰብ አልባሌ ቦታ እንዳይውሉ የጠረጴዛ ቴኒስ በመግዛት ከአምልኮ ውጭ ባለ ስዓታቸው እንዲጫወቱ አድርጓል። ትውልድ አትራፊነታቸው ሊያስመስግናቸው ይገባል።
ኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን ደግሞ ከመስጊዱ አጠገብ ነው የሚገኘው። እነሱም ይሄን የትውልድ አትራፊነት አርአያነት በመከተል የቅርጫት እና የመረብ ኳስ ሜዳ እንጠብቃለን። ከዚያም "እሠይ ሥለቴ ሠመረ" "እንላለን።
ብራዚል የሚገኙ የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያኖች አብዛኞቹ የእግር ኳስ ክለቦች እንዳላቸው ያውቃሉ ?

21/02/2023

ልጅ የማነው ?
ልጅ መውለድ በህይወት ውስጥ ከሚያጋጥሙ አስደናቂ ነገሮች መካከል ተወዳዳሪ የለውም። ልጅ መፍጠርን ቴክኖሎጂ ከመፍጠር ጋር ብናነፃጽረው እንኳ በዓለም ላይ እስከ ዛሬ ከተፈጠሩትና ወደፊትም ከሚፈጠሩ ቴክኖሎጂ ዎች ሁሉ እጅግ አስደናቂውና ውስብስቡ ነው።
የልጅ መወለድን ተዓምራዊ ስሜት በጵሑፍ ከማንበብ ይልቅ በዜማ መስማት ይመረጣል ፤ ልክ አርቲስት ብፅዓት ስዩም " ልጄን አደራ!! " እያለች ልብን በሚነካ ዜማ እንዳዜመችው። ሆኖም ግን ንግግር፤ ከጵሁፍ ዜማም ከንግግር ይበልጥ ገላጭ ስሜት ቀስቃሽ ነውና ስለልጅ የሚቀነቀን ዜማ ግጥሙ አጥንት የሚሰረስር፤ ዜማውም ከባድ ትካዜ ላይ የሚጥል መሆን አለበት።
የልጅን ፍቅር ፈልገን የምናመጣው አይደለም ፤ ሳናውቀው እላያችን ላይ የተጫነ ኃላፊነት ነው። ሁሉም ሰው በልጅ ፍቅር እንዲያር ፣ ለትውልድ እንዲሰዋ የተፈጥሮ ባርያ ሁኗል። እኛ በፍቅር የልጆቻን ባርያ ነን።
የባርያ የሥራ ድርሻ ምንድን ነው ? መታዘዝ አይደለም! ? መታዘዝ ብቻ !!! የልጅ ባርያ መሆን ግን ለፍቅርና ስለ ፍቅር ብቻ ነው። ለዚህም ይመስላል የጋብቻም ትርጉም በዚህ የታጠረው፦ " ጋ" ብቻ። ይቀጥላል.....
/ ከብሩህ አለምነው /

Photos from African Chess Academy, Ethiopia's post 18/02/2023

በዱባይ ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች አሸነፉ

አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 5/2015 በዱባይ ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች አሸናፊ ሆነዋል።
ዛሬ ማለዳ በተደረገው ውድድር በወንዶች ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ከ1 እስከ 10 እንዲሁም በሴቶች ከ1 እስከ 8 በመውጣት ፍጹም የበላይነትን ይዘዋል።
በወንዶች አትሌት አብዲሳ ቶላ 2 ሰዓት ከ5 ደቂቃ ከ42 ሴኮንድ ውድድሩን በመጨረስ አሸንፏል።

አትሌት አብዲሳ በአሜሪካ ኦሬጎን በሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም በተካሄደው 18ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በወንዶች ለኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኘው አትሌት ታምራት ቶላ ታናሽ ወንድም ነው።
አትሌት ደሬሳ ገለታ እና አትሌት ሃይማኖት አለው ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃ ይዘዋል።
በሴቶች አትሌት ደራ ዲዳ 2 ሰዓት ከ21 ደቂቃ ከ11 ሴኮንድ በመግባት የውድድሩ አሸናፊ ሆናለች። አትሌት ደራ የአትሌት ታምራት ቶላ ባለቤት ነች።
አትሌት ሩቲ አጋ እና አትሌት ስራነሽ ይርጋ ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቀዋል።
በሁለቱም ጾታዎች ያሸነፉት አትሌቶች በተመሳሳይ የ80 ሺህ ዶላር ሽልማት ያገኛሉ።

በተያያዘ ዜና ዛሬ ማለዳ በተካሄደው የሆንግ ኮንግ ማራቶን በሴቶች አትሌት ፋንቱ ኢቲቻ 2 ሰዓት ከ27 ደቂቃ ከ51 ሴኮንድ በመግባት አሸንፋለች።

ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊ አትሌት ስንቄ ደሴ ሁለተኛ ወጥታለች።
በወንዶች ኬንያዊው አትሌት ፊልሞን ኪፕቶ ኪፕቹምባ አሸንፏል።
ኢትዮጵያዊያኑ አትሌቶች ልመንህ ጌታቸው እና ሰንበታ ገዛ ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል።
=================//===============
ለአገርም ለትውልድም ይህ መልካም ዜና ነው። እንደዚህ የምንሰራ ከሆነ ይሄ በየቀኑ ቀርስ ላይ ሊቀርብልን የሚገባ ዜና ነው። ማንኛውም ስፖርት ለሰው ልጆች ልዩ ጥቅም ይሰጣቸዋል የሰውን ልጆ ከራሱ ጋር አወዳድሮ ወጤቱን ማሳየት ይችላል። ለምሣሌ አንድ ሯጭ አራተኛ ሲወጣ አራተኛ ነህ አይባልም። አሁን ባለህ ብቃት ሶስት ሰዎች ብቻ ነው የቀደሙህ ተብሎ ነው መነገር ያለበት። እውነትም ሶስቱ ሯጮች ከሱ የተሻለ ለመሥራታቸው ውጤታቸው እንደመሳያ ሊወሰድ ይችላል። ሶስቱም ሯጮች ቀደሙት ማለት እሱ አራተኛ ነው ማለት አይደለም። ነገ አንደኛ ሲወጣ ምን ልንለው ? ሰው ሁልጊዜም አንደኛ ነው። የአንድ ውድድር ውጤት የዛ ውድድር መግለጫ ብቻ ነው። ያ በቂ ቢሆን ኖሮ ሌላ ውድድር አያስፈልግም ነበር። በዚህም ምክኒያት ነው በማግስቱ አሸናፊዎችንም ተሸናፊዎችንም በልምምድ ሜዴ ላይ የምናገኛቸው። ነገም ሌላ ቀን ስለሆነ ነው። ምንም እንኳ ስፖርት ከተለያዩ ከሰዎች ጋር ቢያወዳድረንም የሚሰጠን የራሳችንን ውጤት ነው ( You Vs You )።

ት/ቤቶች ሌላው ይቅርና ስፖርተኞችን እንኳ ፍጠሩልን። አንድ ቤተሰብ ሁለት እና ሶስት አትሌቶችን በሚፈጥርበት ዘመን የስፖርት አካዳሚያችንና ት/ቤቶች ለሀገሪቱ አትሌቶች በማቅረብ በድርቅ ተመተዋል። ሌላው ይቅርና የተማሪዎች ስፖርት ከቆመ ስንት ጊዜ ሆነው ? የትምህርት ፓሊሲያችን ሲፈተሽ ስፖርትንም ማካተት አለበት።

Photos from African Chess Academy, Ethiopia's post 12/02/2023

ህፃናት ችግር የሚፈታላቸው ሰው ከመፈለጋቸው በፊት?
ችግር መፍታትን እናስተምራቸው።

መምህር ተማሪያቸውን ለማበረታታት በማሰብ የጠየቁትን ጥያቄዎች ባለመመለሱ ተናደው " ደደብ " ፕሬዚዳንት ኬኔዲ በአንተ ዕድሜ ሁሉምን ይመልስ ነበር። " አሉት። ተማሪውም ቀድሞውኑ ቤት ውስጥ የተማረ ስለነበር " ቲቸር ፕረዚዳንት ኬኔዲ በእርሶ ዕድሜ የሀገር መሪ አልነበረም እንዴ ? " አላቸው። ወላጆቹ ቤት ውስጥ ያስተማሩት የዚህን ጥያቄ መልስ ሳይሆን የሚገጥሙትን ነገሮች የማሰብ ብቃቱን ተጠቅሞ ለሰውም ሆነ ለሚገጥመው ችግር መልስ እና መፍትሄ እንዴት ማዘጋጀት እንዳለበት ነው። ወላጆችም ልጆቻቸው ት/ቤት ውሰጥ የሚሰደቡ አና የሚገረፉ ከሆነ ባያስተምሯቸው ይመረጣል። ልጆችን መሳደብና መግረፍ እንኳንስ ለመምህራን ለወላጅም የተፈቀደ አይደለም። የሀገራች መልካም ዜና ወላጆች በአሁኑ ጊዜ የማሰብን ጥቅም በመረዳት አምስት ዓመት ያልሆኑ ልጆችን ቼዝና ኪዩብ በማስተማር ላይ ይገኛሉ። ሀገራችን ውስጥ ባሉ ብዙ ውስብስብ ችግሮች ምክንያት አብዛኛው ህብረተሰብ ተስፋ የለንም ሲል ይደመጣል። ልጆቻችንን በዚህ መልኩ ካዘጋጀናቸው አሁን እኛ ችግር ተብለው የምንጠራቸው በሙሉ ለነሱ ጌም የመጫወት ያክል ነው።
ይሄ አስጭንቋቸው ይመስላል አባታችን ሀዲስ አለማየሁ " ህፃናት ላይ የማትሠራ ሀገር ትጠፋለች " ያሉት። ይሄ የሳቸው አባባል ይመስላል አሁን በሀገራችን " የባነነ ትውልድ " እንዲታይ ምክንያት የሆነው።

Photos from African Chess Academy, Ethiopia's post 09/02/2023

ቼዝ ጾታ የማይለየው ስፖርት!!!

" ለሴቶች እና ለህፃናት ቅድሚያ የማትሰጥ ሀገር መጨረሻነትን የሚከለክላት የለም።"
/ ኦሊቃ ድንግል /

ቼዝ በዓለም ላይ ጾታ ሣይለይ የሚያወዳድር ብቸኛው ስፖርት ነው። ማሰብን መሠረት አድርጎ የሚካሄድ ጨዋታና አካላዊ ንክኪ ስላሌለው ጾታና ዕድሜ ሣይገድብና ሳይወስን የሚዘጋጅ ውድድር ነው። እንደ አስፈላጊነቱም በፃታና በዕድሜ እየሆነም ይዘጋጃል። የሚገርመው ነገር የሴቶችን ልዩ የማስታወስ እና የማሰብ ብቃት በአደባባይ ያሳየ ብቸኛው ስፖርት ነው። ለመጀመሪያ ጊዜ ኮምፒውተርን ያሸነፈ ወንድ በሴት እንደሚሸነፍ ያሣየ የዓለማችን ድንቅ ስፖርት ነው።
" የሴት ልጅ ወላጆች እንኳን ደስ አላችሁ!!! "
ለበለጠ መረጃ ይሄን ናሽናል ጂኦግራፊ ያዘጋጀውን ዶክመንተሪ ማየት ትችላላችሁ።
my brilliant brain featuring susan polgar
By national geography

Photos from African Chess Academy, Ethiopia's post 08/02/2023

ፈጠራ / Creativity /
ፈጠራ የሚጀመረው በእጃችን ባለ ነገር ላይ ነው!!!
ለልጆቻችን የምንመርጥላቸው ወይንም የምንፈቅድላቸው እያንዳንዱን ጨዋታና መጫወቻ እንዲሁም የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች እንዲያስቡ እና ለፈጠራ የሚረዳቸው ከሆነ ብቻ ነው። ካለበለዚያ ፈጣሪ የሆነ ልጅ ሰጥተናቸው ፍጡርን አድናቂ አድርገው ይመልሱልናል። በተለይ የስፖርት ሚዲያዎችና አቋማሪ ድርጅቶች ኳስ ተጨዋች ልጅ ሰጥተናቸው እግር ኳስ ተመልካች አድርገው ከሜዳ ወደ 'ዲኤስ' ቲቪ መስኮት ፊት ለፊት ያስቀምጡልናል።
የአካዳሚያችን መርህ በራሱ ከዚህ አንፃር ነው የተቃኘው።
" ትንሽ ልጅ ስጡንና ትልቅ ሰው አድርገን እንመልስላችሁ"

" ልጆች የተፈጠሩት ከትምህርት ለበለጠ ዓላማ ነው። ትምህርትን ጨምሮ ትምህርት ያልፈጠራቸው ነገሮች እንዲፈጥሩ ነው ፈጣሪ የፈጠራቸው። "
/ ኦሊቃ ድንግል /

" ህፃናት ላይ የማትሠራ ሀገር ትጠፋለች "
/ ሀዲስ አለማየሁ /

Photos from African Chess Academy, Ethiopia's post 07/02/2023

የጠንክሮ መሥራትና የጠንክሮ ማሰብ ልዩነቶች!!!
በሬውም ጠንክሮ አርሶ ፣ አባትም ጠንክሮ ሠርቶ፣ ልጅም ጠንክሮ ተምሮ ? ወይ መባከን!!!
በህይወትህ ውሰጥ ጨማሪ እንጂ ጭማሪ አትሁን ይባላል። ጠንክሮ ላለመሥራት እኮ ነው ጠንክሮ ማሰብ ያስፈለገው። በዘመናችን ኮምፒውተሮችና ሮቦቶች የሚሠረሩት ሥራ የዓለም ህዝብ ቁጥር በእጥፍ ቢጨምር አይሠራውም። የኛ ትውልድ ማትሪክን አልፎ በሬውንና ገበሬውን ከጉልበት ሥራ ሳያላቅቀው ማትሪክን ማለፍ ያልቻለ ትውልድ ጨመርንበት። ለዚህም ይሆናል ትንቢተኞቹ ደራሲዎች እንደዚህ ያሉን፦
" ህፃናት ላይ የማትሠራ ሀገር ትጠፋለች "
/ ሀዲስ አለማየሁ /

"ልጅ በልጅነት ዕድሜው ማሰብ ካልተማረ ? ካደገ በኃላ ከየት አምጥቶ ነው የሚያስበው ? " / ኦሊቃ ድንግል /

"ማሰብን እንደ ሥራ የሚቆጥር ባህል መፍጠር አለብን።"
/ዶክተር ምህረት ደበበ/

" እብደት ማለት፦ ተመሣሣይ ነገር እየሠሩ የተለየ ውጤት መጠበቅ ነው። " / አልበርት አንስታይን /

የጠንክሮ ማሰብ ዋናው ዓላማ የጠንክሮ መሥሪያን ጊዜና ልፋት ለመቀነስ ነው። ዓመቱን በሙሉ ጠንክረን እያረስን ዓመቱን በሙሉ ጠንክረው የሚያስቡትን ስንዴ እንለምናለን። እግዚእዎ ወይንም ሰፉፉ ለትምህርት ሥርዓታችን።
ለምሳሌ ይረዳን ዘንድ በ14 ዓመቷ ሬምያ ጆሴ ከኬረላ ያደረገችው ይህንኑ ነው።በየቀኑ ልብሶችን በእጅ ማጠብ ስለሰለቻት ወጣቷ ፈጣሪ ወደ ፊት ሄዶ ከኤሌክትሪክ በተቃራኒ ፔዳሊንግ የሚጠቀም የልብስ ማጠቢያ ማሽን ፈለሰፈቾ። ማሽኑ በአንድ ጊዜ ወደ ሶስት ኪሎ የሚጠጉ ልብሶችን ማጠብ ብቻ ሳይሆን ልብሱንም 80% አድርቆ ያወጣል ይህም ጊዜንና ጉልበትን ይቆጥባል።

Photos from African Chess Academy, Ethiopia's post 06/02/2023

የማሰብና የመጨነቅ ልዩነቶች።

ማሰብ፦ ዓላማው መፍትሄ ለመፈለግና ለማግኘት ነው።
መጨነቅ፦ ማሰብ ባለማወቅና ባለመቻል የሚፈጠር የውጥረት አዙሪት ነው።
ጨለማ ቦታ የሚለቀው ብርሀን ሲመጣ ብቻ ነው። በተመሳሳይ ጭንቀትም የሚቆየው ማሰብ እስኪመጣ ብቻ ነው። ብርሃንና ጭለማ ፣ ጨንቀትና ማሰብ አብሮ መኖር የማይችሉ የተለያዩ ነገሮች ናቸው። በሌላ አነጋገር ማሰብ ብርሃን ሲሆን መጨነቅ ደግሞ ጭለማ መሆኑ ነው። ብርሃን እስካልመጣ ድረስ ጭለማ የመኖር መብት አለው። ጭንቀትም ማሰብ እስካልመጣ ድረስ ራሱን እያባዛ የመኖር መብት አለው።
ለዚህም ይመስላል ደራሲ ኦሊቃ ድንግል " ሀሣብን የሚያውቅ በሃሣብ ይጫወታል ፤ ሀሣብን የማያውቅ ሀሣብ ይጫወትበታል " ያሉት።
ቶማስ ኤድስን የሚባል ሰው ጭለማ የሚያስጨንቀውና የሚፈራ ሰው ነበር። በመጨነቅና በፍራቻ ለጭለማ መፍትሄ ሊገኝ እንደማይቻል ስለተረዳ ራሱን የመፍትሄ አካል በማድረግ በምሽት ላይ የሚበራ ብርሃን ለመፍጠር አሐዱ ብሎ ጉዞውን በመጀመር ከረጅም ጊዜ ጥረትና ሙከራ በኃላ አምፖልን በመፍጠር ራሱንም የሰው ፍጡርንም ከጭለማ ስጋት ለመታደግ በቅቷል።

" ልጅ በልጅነት ዕድሜው ማሰብ ካልተማረ ? ካደገ በኃላ ከየት አምጥቶ ነው የሚያስበው ? " / ኦሊቃ ድንግል /

Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Category

Telephone

Address


Addis Ababa
1000