18/09/2021
ድርጅታችን ኤም ቪው አጠቃላይ የትምህርት አማካሪ እና የባለሙያ ድጋፍ ሰጪ ከ Gooday Online - ጉዳይ እና ከ Minab IT Solution (HaHu jobs) ጋር በጋራ አብሮ ለመስራት የስምምነት ሰነድ ተፈራርመናል።
በስምምነቱም ለስራ ፈላጊዎች እና ቀጣሪዎች የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን መስጠት፣ የስራ ምልመላ እና ማስቀጠር ሂደት የአጋዥ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት ላይ እንዲሁም በአሰሪ ተቋማት፣ በሰራተኞች እና በባለድርሻ አካላት ላይ ያሉትን ክፍተቶች እና ተጨባጭ መፍትሔዎች ላይ በድርጅታችን በመዘጋጀት ላይ ላለው ነፀብራቅ ሳምንታዊ የቴሌቪዥን ፕሮግራም ላይ በጋራ ለመስራት ነው። በሂደቱ ለነበራቸው ቀናነት ሁለቱንም ድርጅቶች እናመሰግናለን! መልካም የስራ ጊዜ ይሁንልን።
17/06/2021
እንኳን ደስ አለን!! አላማውን የአፍሪካ ድርጅቶችን አለማቀፋዊ ተወዳዳሪ ማድረግ ላይ ትኩረቱን በማድረግ የሚሰራው የ GrowthAfrica Accelerator ውድድርን ተቋማችን Aim View General Educational Consultancy & Support አሸንፈናል:: ውድድሩም አብዛኛውን የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ የሚገኙ ተቋማትን ያሳተፈ ነበር ከሀገራችንም በርካታ ተቋማት ለአንድ አመት ተወዳዳሪ ነበርን በመጨረሻም አሸንፈን ለቀጣይ አንድ አመት አብረን ስራ ጀምረናል:: ተቋማችንን በማገዝ እና ከሌሎች አፍሪካ ሀገር ተቋማት ጋር አብረን እንድንሰራ በማድረግ ትልቅ አስተዋፆ አለው:: መልካም የስራ ጊዜ ይሁንልን! እናመሰግናለን::
01/06/2021
ዛሬ አጋር ድርጅታችን ሚኒመም ለርኒግ ኮምፒተንሲ ኢትዮጵያ (MLCE) ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር (MOE) በጋራ አብሮ ለመስራት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመናል ስምምነቱም የሀገራችንን የትምህርት ስርዐት በተለይም የሳይንስ፣ ሂሳብ እና አርት ትምህርቶች ላይ ትኩረቱን በማድረግ በተግባር የተደገፈ እና የ21ኛ ክፍለ ዘመን የትምህርት ስርዐትን ባማከለ መልኩ ለአጠቃላይ የትምህርት መሀበረሰቡ እንሰራለን:: ለኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚንስቴር ዴኤታ ዶ/ር ገረመው ሁሉቃ እና ለሳይንስ እና ሂሳብ መዐከል ጀነራል ዳይሬክተር ዶ/ር አብረሀም አለማየሁ እንዲሁም ለአጠቃላይ ሙያተኞች ምስጋናችንን እናቀርባለን:: በተግባር የተደገፈ ትምህርት ለዜጎች በማድረስ ሀላፊነታችንን እንወጣለን!
16/04/2021
ዛሬ ድርጅታችን ኤም ቪው አጠቃላይ የትምህርት አማካሪ እና የባለሙያ ድጋፍ ሰጪ ከ እናት ባንክ ጋር በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመናል:: በስምምነታችንም ላይ ድርጅታችን በሚሰጠው አጠቃላይ የትምህርት የማማከር አገልግሎት ላይ የሚሰጡትን አገልግሎቶች ክፍያ በእናት ባንክ በኩል እንዲሆን እንዲሁም የተምህርት ስርአቱን እና የባንኩን ራዕይ የሚደግፉ የተለያዩ መርሀ ግብሮችን በመንደፍ በጋራ ለመስራት ተስማምተናል:: የባንኩን ፕሬዝዳንት አቶ ኤርሚያስን እንዲሁም አጠቃላይ የማኔጅመንት አባላትን ከልብ እናመሰግናለን:: መልካም የስራ ጊዜ ይሁንልን!
ማን እንደእናት!
07/04/2021
እናት ባንክን ከልብ እናመሰግናለን!
የሶስት ወር የፕሮዳክሽን ወጪያችንን እስፖንሰር አድርገውናል እንዲሁም በጋራ አብረን ለመስራት የመፈራረሚያ ሰነድ አዘጋጅተናል:: በቅርቡ እንፈራረማለን!
Coming Soon MOU Aim View General Educational Consultancy & Support with Enat Bank
ማን እንደ እናት!
04/03/2021
የኤም ቪው አጠቃላይ የትምህርት አማካሪ እና የባለሙያ ድጋፍ ሰጪ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር በመተባበር የሚቀርብ ነፀብራቅ ሳምንታዊ የቴሌቪዥን ፕሮግራም በቅርብ ቀን..
22/02/2021
ድርጅታችን ኤም ቪው አጠቃላይ የትምህርት አማካሪ እና የባለሙያ ድጋፍ ሰጪ ድርጅት በኢትዮጵያ የ26 አመታት የበጎነት አምባሳደር ከሆነው አንጋፋው ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ ጋር በጋራ አብሮ ለመስራት የስምምነት ሰነድ ተፈራርመናል::
በስምምነቱም መሰረት የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች መስጠት ፣ ተግባር ተኮር ትምህርትን ተደራሽ ማድረግ እና ትምህርታዊ ውድድሮች በማዘጋጀት ላይ በመስራት አጠቃላይ የሀገራችንን የትምህርት ጥራት ለማረጋገጥ እንተጋለን።
የሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ መስራች እና ስራ አስኪያጅ ሲስተር ዘቢደር ዘውዴ በድርጅታችን ስም ከልብ እናመሰግናለን።
19/02/2021
ድርጅታችን ኤም ቪው አጠቃላይ የትምህርት አማካሪ እና የባለሙያ ድጋፍ ሰጪ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር በመተባበር ሣምንታዊ አዝናኝ እና ትምህርታዊ የቴሌቪዥን ፕሮግራም አዘጋጅቶ ለማስተላለፍ ውል ተፈራርሟል።
ነፀብራቅ የቴሌቪዥን ፕሮግራምም አጠቃላይ የአገራችንን የትምህርት አሰጣጥ ሥርዓት በመዳሰስ በሥልጠና፣ በተግባር ተኮር ትምህርት እና በትምህርታዊ ውድድሮች ላይ በማተኮር እያዝናና የሚያስተምር ፕሮግራም ነው።
ድርጅታችን ለቀና ትብብራቸው እና ለፈቃደኝነታቸው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ አድማሱ ዳምጠው እና ለምክትል ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሰጠኝ እንግዳው ፣ እንዲሁም ለአቶ ተፈራ መኮንን እና ለአጠቃላይ ኦዲቶሪየም አባላቱ ምሥጋናውን ያቀርባል!
07/02/2021
ድርጅታችን የሚሰጣቸው አገልግሎቶች - ኤም ቪው አጠቃላይ የትምህርት አማካሪ እና የባለሙያ ድጋፍ ሰጪ
ከስር ያለውን ሊንክ በመጫን የዩትዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ
ድርጅታችን የሚሰጣቸው አገልግሎቶች - ኤም ቪው አጠቃላይ የትምህርት አማካሪ እና የባለሙያ ድጋፍ ሰጪ
ኤም ቪው አጠቃላይ የትምህርት አማካሪ እና የባለሙያ ድጋፍ ሰጪ ድርጅትአማራጭ የማህበራዊ ትስስር ገፆችን ይቀላቀሉበ Telegram :- https://t.me/aimviewበ Facebook :- https://www.facebook....