Ethiopian Academic Staffs Union of Universities-EASUU
We aim to unite all academic staffs through out Ethiopian Universities.
All major Universities set to open new campus in all major cities in Ethiopia and even in east African countries. This will crash all 2nd, 3rd and 4th generation Universities, I don't know if there is 5th generation too, if there is say goodbye!
Now, universities have to open campuses everywhere and compete among each other. This pursuit is primarily about attracting more students to maximize profit and ensure Universities' survival. Welcome to Et-Autonomous Universities, this is often called the neoliberalism.
07/12/2025
Time to support and develop an Et-Universities Artificial Intelligence (AI) use guideline for our Unis.
Credit, sheger FM
በሀላፊነት ላይ ያለ የመንግስት ሹመኛ ወይም ተመራጭ ለ እንዳይታጭ የሚከለክል መመሪያ የትምህርት ሚኒስቴር አወጣ፡፡
መመሪያው 8 ዙር ተማሪዎችን ያላስመረቁ እና ሶስተኛ ዲግሪ ወይም (PhD) የማያስተምሩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የክብር ዶክትሬት እንዳይሰጡ ይከለክላል፡፡
በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ሃምሌ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ተፈርሞ ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት የተመራው ይህ መመሪያ በቅርብ ጊዜ የተመሰረቱ የትምህርት ተቋማት የክብር ዶክትሬት እንዳይሰጡ ይከለክላል፡፡
በመመሪያው ክፍል ሁለት ላይ የክብር ዶክትሬት የሚሰጡ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መስፈርትን በተመለከተ የተቀመጠው ድንጋጌ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የክብር ዶክትሬት ለመስጠት ቢያንስ ከ8 ጊዜ በላይ ተማሪዎችን ያስመረቁ እና የሶስተኛ ዲግሪ የሚሰጡ መሆን እንዳለባቸው ያስገድዳል፡፡
በዚህም መሰረት ሰላሌ፣ ደምቢ ዶሎ፣ መቅደላ አምባ፣ ራያ፣ ደባርቅ እና መሰል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ስምንት ዙር ተማሪዎችን ስላላስመረቁ በመመሪያው መሰረት የክብር ዶክትሬት መሰጠት አይችሉም፡፡
በዚሁ ክፍል ስር ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የክብር ዶክትሬት ማዕረግ ለመስጠት አገር እና አለም አቀፍ መስፈርቶችን ማሟላት እንዳለባቸው ሰፍሯል፡፡
በሞያ መስኩ የተለየ ስራ ያበረከተ ከሆነ ኢትዮጵያዊም ሆነ ሌላ ዜጋ የክብር ዶክትሬት ማዓረግ ማግኘት እንደሚችል የዘረዘረው መመሪያው መስፍርቱን ካሟሉ ለግለሰብም ይሁን ለቡድን መስጠት እንደሚቻል አመላክቷል፡፡
በሕይወት ላለም ይሁን ለሌለ ሰው ማዕረጉን መስጠት እንደሚቻል የሚፈቅደው ይህ መመሪያው የክብር ዶክትሬት ለማግኘት የማይቻልባቸውን ገደቦችም በክፍል ሁለት አንቀጽ 10 ስር ዘርዝሯል፡፡
በዚህም መሰረት የከፍተኛ ትምህርት ተቋሙ የሙሉ ሰዓት ተቀጣሪ ሰራተኛ፣ የሴኔት አባላት ወይም የአስተዳደር አካላት ከተቋሙ ጋር ያላቸው ቀጥተኛ ግንኙነት እስካላበቃ ድረስ ለክብር ዶክትሬት መታጨት እንደማይችሉ ደንግጓል፡፡
መመሪያው በስራ ላይ ያሉ የመንግስት ሹሞች ወይም ባለስልጣናት ለክብር ዶክትሬት እንዳይታጩም የሚከለክል ነው፡፡
የክብር ዶክትሬት የተሰጠው ግለሰብ ዶክተር፣ የክብር ዶክተር እና መሰል መጠሪያዎችን ከሰጪው ተቋም ውጪ በየትኛውም ድርጅት ውስጥ መጠቀም እንደማይችሉም ደንግጓል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር በለፈው ዓመት በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በሽምያ የሚሰጡ የክብር ዶክትሬት ማዕረጎች መመሪያ እስኪወጣ ድረስ እንዲያቆሙ ማዘዙ ይታወሳል፡፡
MoE
በተከታታይ ሦስት ጊዜ በተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ከ25 በመቶ በታች ውጤት በሚያስመዘግቡ ዩኒቨርሲቲዎች ላይ እርምጃ እንደሚመወሰድ ተገለፀ።
የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ከቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት ጋር ተወያይተዋል።
------------------------------------------------------
(ሚያዝያ 25/2017 ዓ.ም) በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዩኒቨርሲቲዎች ሰው እውቀትና እውነት ፈልጎ የሚመጣባቸው ተቋማት ሊሆኑ ይገባል ብለዋል።
ዩኒቨርሲቲዎች በተፈጥሮ የተሰጡ የአካባቢው ፀጋዎች ላይ ራዕይ ይዘው መሥራት ይገባቸዋል ያሉ ሲሆን ቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲም በማዕድን ላይ ሰፊ ምርምር በማድረግ ህብረተሰቡን ብሎም ሀገርን የሚጠቅም ሥራ መስራት ይጠበቅበታል ብለዋል።
አክለውም ዩኒቨርሲቲዎች የሚያስተምሯቸው ተማሪዎች ብቃት ያላቸውና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ማድረግን ዋና ተግባራቸው አድርገው መሥራት አለባቸው፦
በዚህ ረገድ በተከታታይ ሦስት ጊዜ በተመራቂ ተማሪዎች በመውጫ ፈተና ውጤት ከ25 በመቶ በታች ካስመዘገቡ በትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን በኩል እርምጃ እንደሚወሰድ አመላክተዋል።
የዩኒቨርሲቲ አመራሮች በብቃትና በችሎታ እንዲመደቡ እየተደረገ መሆኑን አንስተው አሰራራቸውን ለማዘመንም የዩኒቨርሲቲ አመራሮች ማሰልጠኛ ተቋም ለማቋቋሞ እየተሠራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲዎች በተሰጣቸው የተልዕኮ መስክ ልየታ መሠረት ትኩረት አድርገው ሊሠሩ ይገባል ብለዋል።
አክለውም ዩኒቨርሲቲዎች የእውቀትና የሥነ ምግባር ፋና በመሆናቸው ተማሪዎቻቸውን ማብቃት ላይ ትኩረት አድርገው ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲን በተመለከተ በትምህርት ሚኒስቴር የሱፐርቪዥን ቡድን በጥንካሬና በክፍት የተለዩትን ጉዳዮች ያቀረቡት ደግሞ የከፍተኛ ትምህርት የአሰተዳደርና መሠረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) ሲሆኑ።
ዩኒቨርስቲው ብቃት ያላቸውና ተወዳዳሪ የሆኑ ተማሪዎችን በማፍራት ተመራጭ ዩኒቨርስቲ እንዲሆን ራዕይ ይዞ መሥራት ይጠበቅበታል ብለዋል።
የቡሉሆራ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላትም በአካዳሚክ እና በአስተዳደር ረገድ አሉ ያላቸውን ጥያቄዎች አንስተው ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
With no intent to Politics, we felt this is worth reading.
17/03/2025
Excellent step
Click here to claim your Sponsored Listing.
Location
Category
Contact the school
Website
Address
Addis Ababa