ለማን ብዬ

ለማን ብዬ

Share

Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ለማን ብዬ, College & University, Addis Ababa.

Photos from የኢትዮጵያ መምህራን መድረክ's post 06/08/2025
Photos from Ethio Trust Media's post 29/07/2025
24/07/2025


👉አንድ ተማሪ ያለበቂ ምክንያት በአንድ መንፈቀ-ዓመት ከት/ቤት በተከታታይ ለ12 የትምህርት ቀናት እያሰለሰ ወይም በተከታታይ ለ15 የትምህርት ቀናት ከቀረ ከት/ቤቱ ለአንድ የትምህርት አመት ይሰናበታል፣
👉በሚወጣው የትምህርት ፕሮግራም መሠረት በሰዓቱ በክፍል ውስጥ መገኘትና ትምህርቱን መከታተል፣
👉በክፍልም ሆነ ከክፍል ውጭ በመምህራን የሚሰጠውን ትምህርት በጥሞና መከታተል፣ መልመጃዎች፣ የቤት ሥራዎችንና የቡድን ስራዎችንና የመሳሰሉትን በተሰጠው ጊዜ አጠናቆ ማቅረብ፣
👉የትምህርት ቤቱ አመራር፣ መምህራንና የድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች የሚሰጡትን ድጋፍ፣ ምክርና መመሪያ መፈፀም፣
ፆታዊ ትንኮሳ (ሴት ተማሪዎችን ከማስፈራራት፣ ከመድፈር፣ ከመደብደብና ሰብአዊ መብታቸውን ከመንካትና) ከመሳሰሉት መቆጠብ፣
👉የመማሪያ መፃሕፍትና ሌሎች የትምህርት መሣሪያዎችን በጥንቃቄ አለመጠቀም፣ አለመያዝ፣ መቅደድ፣ ተደጋጋሚ አገልግሎት እንዳይሰጥ ማድረግና የመሳሰሉት ተግባራት ከመፈጸም መቆጠብ፣
👉ከሌሎች ተማሪዎች ጋር በመግባባትና በመተሳሰብ መሥራትና መማር፣
ለመምህራን፣ ለሠራተኞችና ለትምህርት ቤት ጓደኞቹ ተገቢውን ክብር መስጠት፣
👉የትምህርቱን ጊዜ በማይሻማ ሁኔታ ዕውቀቱንና ጉልበቱን ለትምህርት ቤቱና ለአካባቢው ኀብረተሰብ አገልግሎት ማዋል፣
👉የትምህርት ቤቱ የመቀመጫ ወንበሮችን፣ የመማሪያ ክፍሎችንና ምድረ ግቢውን በንጽሕና መያዝ፣
👉የመማርያ መጻህፍትን በክፍል ውስጥ ይዞ መገኘት፤
👉በትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ ማንኛውንም በአካልና በጤና ላይ ጉዳት የሚያደርስ መሣሪያ ይዞ አለመገኘት፣
👉የደንብ ልብስን ት/ቤቱ ባወጣው ደንብ መሰረት ንፅህናውን ጠብቆ መልበስ፤
👉በትምህርት ሰዓት ያለ በቂ ምክንያት በትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ አለመዟዟር፣
👉በትምህርት ጊዜ ያለበቂ ምክንያት አቋርጦ አለመውጣትና የትምህርት ቤቱን አጥር ዘሎ አለመሄድ፣
👉በትምህርት ቤት ውስጥ ሲጋራ አለማጨስ፤ ጫትና ሌሎች አደንዛዥ ዕፆችን አለመጠቀም፣
👉ተገቢውን የአለባበስ፣ የጸጉር አሰራር/አቆራረጥ እንዲሁም የግል ንፅህናና የአካባቢ ባህልና ወግ መጠበቅ፤
👉በት/ቤት ግቢ ውስጥ ሞባይል ይዞ አለመገኘት
በሰንደቅ ዓላማ ስነ-ሥርዓት ወቅት ተገኝቶ በመዘመር ማክበር፤
👉መምህራንና ሠራተኞችን አለመዝለፍ፣ አለመስደብ፣ አለማንቋሸሽና አለመደብደብ፣
👉በመማር ማስተማር ሂደት ወቅትና በት/ቤቱ ቅጥር ግቢ ተገቢ ያልሆነ ባህሪ አለማሳየት
ስርቆት መፈፀም፣ በፈተና ወቅት መረበሽ፣ መኮረጅና ማስኮረጅ፣ ቁማር መጫወት ከመሳሰሉ ሕገወጥ ድርጊቶችና ከሌሎች ጥፋቶች ሁሉ መራቅ፣

24/07/2025

ድንቅና አስተማሪ አባባሎች!!
‎ ================
‎1. ‹‹የዘጠኝ ወር እርጉዝ በማግባት በአንድ ወር የራስህን ልጅ ልትወልድ አትችልም››

‎2. ‹‹ዛሬ ዛፍ ጥላ ስር የምንቀመጠው የሆነ ጊዜ ላይ የሆነ ሰው ዛፉን ስለተከለው ነው፡፡››

‎3. ‹‹ዝናህን ለመገንባት ሃያ ዓመት ይወስድብሃል፡፡ ዝናህን ለማበላሸት ግን ሃያ ደቂቃ በቂህ ነው፡፡ ይሄን ጉዳይ ካሰብክ ነገሮችን በተለያየ መንገድ ታከናውናቸዋለህ፡፡››

‎4. ‹‹ባልገባህ ቢዝነስ ላይ ኢንቨስት አታድርግ››

‎5. ‹‹ስጋት ወይም ፈተና የሚመጣው የምትሰራውን ባለማወቅ ነው፡፡››

‎6. ‹‹በአንድ ገቢ ብቻ ጥገኛ አትሁን፡፡ ሁለተኛ የገቢ ምንጭ ፍጠር››

‎7. ‹‹በአሜሪካ ቢዝነስ ቁጭ ብሎ ማሰብ ያልተለመደ ነው፡፡ እኔ ግን ብዙ ጊዚዬን የማጠፋው ቁጭ ብዬ በማሰብ ነው፡፡

‎8. ‹‹በጣም አስፈላጊው ኢንቨስትመንት በራስህ ላይ የምታደርገው ነው፡፡››

‎9. ‹‹የማትፈልገውን የምትገዛ ከሆነ የምትፈልገውን ወዲያው ትሸጣለህ፡፡››

‎10. ‹‹ከመጥፎ ሰው ጋር ጥሩ ውል ማሰር አትችልም፡፡

‎11. ‹‹ደስተኛ ሰዎች የሚደሰቱት ምርጥ ነገር ስላላቸው አይደለም፡፡ እነሱ የሚደሰቱት ያላቸውን ነገር አክብረውና ወደው ስለያዙ ነው፡፡

‎12. ‹‹በመኝታህ ሰዓት ገንዘብ ለማግኘት አስበህ አዲስ መላ ካልፈጠርክ እስክትሞት ትሰራለህ፡፡

‎13. ‹‹አጥፍተህ የቀረህን አትቆጥብ፡፡ ከቁጠባ በኋላ የተረፈህን አጥፋ፡፡››

‎14. ‹‹ብዝሃነት ወይም ሁለገብ ዕውቀት ከመሐይምነት ይከላከላል፡፡

‎15. ‹‹ታማኝነት በጣም ውዱ ስጦታ ነው፡፡ ይሄን ስጦታ ከርካሽ ሰዎች አትጠብቅ፡፡››

‎16. ‹‹ያልተለመደ ከሆነ ሰዎች ብዙ ጊዜ ትክክለኛውን ነገር ከመስራት ሊያስቆሙህ ይሞክራሉ፡፡

‎17. ‹‹በዓለም ላይ ሐይል ያለው ምንም ቅድመ ሁኔታ የሌለው ፍቅር ነው፡፡

‎18. ‹‹ሁልጊዜም ሐብት ማግኛ ምርጡ መንገድ ለራስህ ዋጋ መስጠት ነው፡፡

‎19. ‹‹አነባለሁ፣ አነባለሁ፣ አነባለሁ! በቀን ውስጥ ከአምስት እስከ ስድስት ሰዓት ድረስ አነባለሁ፡፡››

‎20. ‹‹ብዙ በተማርክ ቁጥር ብዙ ታገኛለህ። ››

Photos from መረጃ አዲስ FAST NEWS's post 23/07/2025
Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Telephone

Website

Address


Addis Ababa
145534