ኢስላማዊ ጥቅሶች

ኢስላማዊ ጥቅሶች

Share

Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ኢስላማዊ ጥቅሶች, Education, Addis Ababa.

23/12/2025

"የሙስሊም ዜግነቱ ዐቂዳው ነው"
ዶ/ር አይመን አል-በለዊ

Photos from ኢስላማዊ ጥቅሶች's post 04/10/2025

እነዚያም የካዱት ከፊሎቻቸው ለከፊሉ ረዳቶች ናቸው፡፡ (ከምእምናን መረዳዳትን ከከሓዲያን መቆራረጥን) ባትሠሩት በምድር ላይ ሁከትና ታላቅ ጥፋት ይኾናል፡፡

22/07/2025
13/06/2025

وَأَعْتَزِلُكُمْ وَمَا تَدْعُونَ مِن دُونِ اللَّهِ وَأَدْعُو رَبِّي عَسَىٰ أَلَّا أَكُونَ بِدُعَاءِ رَبِّي شَقِيًّا

«እናንተንም ከአላህ ሌላ የምትግገዙትንም እርቃለሁ፡፡ ጌታዬንም እግገዛለሁ፡፡ ጌታዬን በመገዛት የማፍር አለመኾኔን እከጅላለሁ፡፡»

07/06/2025

۞ إِنَّ الصَّفَا وَالْمَرْوَةَ مِن شَعَائِرِ اللَّهِ ۖ فَمَنْ حَجَّ الْبَيْتَ أَوِ اعْتَمَرَ فَلَا جُنَاحَ عَلَيْهِ أَن يَطَّوَّفَ بِهِمَا ۚ وَمَن تَطَوَّعَ خَيْرًا فَإِنَّ اللَّهَ شَاكِرٌ عَلِيمٌ

ሶፋና መርዋ ከ #አላህ (ትዕዛዝ መፈጸሚያ) ምልክቶች ናቸው፡፡ ቤቱን (ካዕባን) በ #ሐጅ ወይም በ #ዑምራህ ሥራ የጎበኘ ሰው በሁለቱ (መካከል) በመመላለሱ በርሱ ላይ #ኃጢአት የለበትም፡፡ መልካምንም ሥራ በፈቃደኛነት የሠራ ሰው (አላህ ይመነዳዋል)፤ #አላህ አመስጋኝ ዐዋቂ ነውና፡፡

06/06/2025

ግመሎችንም ለእናንተ ከአላህ ሃይማኖት ምልክቶች አደረግናቸው፡፡ በእርሷ ለእናንተ መልካም ጥቅም አላችሁ፡፡ በእርሷም ላይ (ስታርዷት) በሶስት እግሮችዋ ቆማ የተሰለፈች ሆና የአላህን ስም አውሱ፡፡ ጎኖቻቸውም በወደቁ ጊዜ ከእርሷ ብሉ፡፡ ለማኝንም ለልመና የሚያገዳድምንም አብሉ፡፡ እንደዚሁ ታመሰግኑ ዘንድ ለእናንተ ገራናት፡፡

وَالْبُدْنَ جَعَلْنَاهَا لَكُم مِّن شَعَائِرِ اللَّهِ لَكُمْ فِيهَا خَيْرٌ ۖ فَاذْكُرُوا اسْمَ اللَّهِ عَلَيْهَا صَوَافَّ ۖ فَإِذَا وَجَبَتْ جُنُوبُهَا فَكُلُوا مِنْهَا وَأَطْعِمُوا الْقَانِعَ وَالْمُعْتَرَّ ۚ كَذَٰلِكَ سَخَّرْنَاهَا لَكُمْ لَعَلَّكُمْ تَشْكُرُونَ

30/05/2025

አስሩን የዙልሒጃ ቀናት እንዴት እናሳልፍቻው?

1-እውነተኛ ተውበት ማድረግ

እነዚህንም ሆነ ሌሎች የዒባዳ ቀናትን ለመቀበል ከሰራናቸው ወንጀሎች በመጸጸት ወደ አላህ መመለስ አለብን። አላህ እንዲ ብሏል:-

{ ምእምናኖች ሆይ! ትድኑ ዘንድ ሁላችሁም ወደ አላህ (በመመለስ) ተጸጸቱ።﴿ [ሱረ አል-ኑር፣31]

2- ቀኖቹን በአግባቡ ለመጠቀም ቁርጠኛ መሆን

በዙልሒጃ 10 ቀናት ውስጥ ልዩ ትኩረት ሰጥተን አላህ በደነገጋቸው ኢባዳዎች ለማሳለፍ ከወዲሁ ራስን እና ያግዘናል ያልነውን ነገሮች በሙሉ ማዘጋጀ ተገቢ ነው።

አላህ እንዲ ብሏል:- {እነዚያም በኛ መንገድ የታገሉ መንገዳችንን በእርግጥ እንመራቸዋለን፤ አላህም በእርግጥ ክበጎ ሠሪዎች ጋር ነው።﴿[ሱረቱ አል-ዐንከቡት፣69]

3- ከወንጀል መራቅ

የአላህን ተእዛዛት መፈጸም ወደርሱ እንደሚያቃርብ ሁሉ የከለከላቸውን እና እርም ያደረጋቸውን ነገሮች መዳፈር ከርሱ መራቅን እና ከእዝነቱ ለመባረር ምክንያቶች ናቸው።

🕋 አስሩ የዙልሒጃ ቀናት ያላቸው ደረጃ

1-አላህ ሱብሓነሁ ወተዓላ በነዚህ ቀናት ምሏል

አላህ በሆነ ነገር ሲምል የዛን ነገር ትልቅነት እና ደረጃ ያመለክታል፤ አላህ በትልቅ ነገር እንጅ አይምልም። አላህ እንዲህ ብሏል:-

﴾በጎህ እምላለሁ።በዐሥር ሌሊቶችም።﴿
[አል-ፈጅር፣1-2]
ኢብን ከሢርን ጨምሮ አብዛኞች ሙፈሲሮች እንዳሉት ‘አስሩ ሌሊቶች’ የዙልሒጃ የመጀመሪያዎቹ ናቸው።

2-አላህ በርሱ ውስጥ እሱን ማውሳትን የደነገገባት “የታወቁ ቀናት” መሆናቸው።

አላህ እንዲህ ብሏል:-
﴾በታወቁ ቀኖችም ውስጥ ከማለዳ እንሰሳዎች በሰጣቸው ሲሳይ ላይ የአላህን ስም ያወሱ ዘንድ፣ (ይመጡሃል)﴿
[አል-ሐጅ፣28]
ኢብን ዐባስ እንዳሉት የታወቁ ቀኖች የተባሉት የዙሒጃ የመጀመሪያዎቹ አስሩ ቀኖች ናቸው።

3- ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ከዱንያ ቀኖች በላጭ መሆኗን ተናግረዋል

ከዐብደላህ ቢን ዐባስ(አላህ ስራቸውን ይውደድላቸውና) እንደተወራው ነቢዩ( ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ:-
[ከነዚህ አስርት(ከዙልሒጃ የመጀመሪያዎቹ) ቀናት ይበልጥ አላህ ዘንድ በውስጣቸው የሚሰሩ መልካም ስራዎች ተወዳጅ የሚሆኑበት ቀን የለም።] ብለው ሲናገሩ ሶሐቦች፡- ”የአላህ መልእክተኛ ሆ! በአላህ መንገድ ላይ የሚደረግ ጂሃድም ቢሆን?“ በማለት ጠየቁ፤ ነብዩ(ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም):- [ (አዎን!)ነፍሱንና ንብረቱን ይዞ የወጣ፣ ከዚያም አንዱንም ይዞ ያልተመለሰ ሰው ካልሆነ በስተቀር፣ በአላህ መንገድ ላይ የሚደረግ ጂሃድም ቢሆን(አይበልጥም።)] አሉ። (አቡ-ዳውድ ዘግበውታል።)

4- በአስሩ ቀናት ውስጥ የዐረፋ ቀን አለ።

ዐረፋ ከዙልሒጃ የዘጠነኛው ቀን ነው። አላህ ﴾ ዛሬ ሃይማኖታችሁን ለናንተ ሞላሁላችሁ። ጸጋዬንም በናንተ ላይ ፈጸምኩ። ለናንተም ኢስላምን ከሃይማኖት በኩል ወደድኩ﴿የሚለውን አያህ ያወረደበት፣ወንጀሎች የሚማሩበት፣ የአላህ ባሮች ከእሳት ነጻ የሚባሉበት ቀን ነው።

5- በአስሩ ቀናት ውስጥ የእርድ ቀን (ዒደል-አድሐ) አለ።

የዙሒጃ አስረኛው የውመነሕር(የእርድ ቀን)የዒድ ቀን ነው። ከቀናቶች ሁሉ ታላቅ ቀን ነው። ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:-(አላህ ዘንድ ከቀናት ሁሉ ትልቁ የእርዱ(ዒደል-አድሐ) ቀን ነው።(አቡ-ዳውድ ዘግበውታል።)

6-ዋና ዋና የዒባዳ አይነቶች በነዚህ ቀናት ውስጥ ተሰብስበው ይገኛሉ።

ኢብን ሐጀር(አላህ ይዘንላቸው እና) እንዲህ አሉ:- “የዙልሒጃ አስሩ ቀናት ልዩ የሆኑበት ምክንያት ዋና ዋና የአምልኮ አይነቶች እነሱም:ሶላት፣ ጾም፣ ሶደቃ እና ሐጅ በውስጧ ስለተሰበሰቡ ነው። ይህ(ስብስብ) በሌሎ

08/05/2025

قَالَ إِنِّي عَبْدُ اللَّهِ آتَانِيَ الْكِتَابَ وَجَعَلَنِي نَبِيًّا

(ሕፃኑም) አለ «እኔ የአላህ ባሪያ ነኝ፡፡ መጽሐፍን ሰጥቶኛል ነቢይም አድርጎኛል፡፡»

27/04/2025

!

Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Category

Website

Address


Addis Ababa