16/02/2026
ሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር ተካሄደ፡፡
ሰኞ የካቲት 09/2018 ዓ.ም
የሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር የጽ/ቤቱ ኃላፊ እንዱሁም የስራዎች አስተባሪዎች እና ሠራተኞች በተገኙበት ተካሂዷል፡፡
የሰኞ ማለዳ የሠራተኞች የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር "የስራ ተነሳሽነት" በሚል ርዕስ ዙሪያ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት የፈተና አስተዳደር ባለሙያ በሆኑት ወ/ሮ ኬሪያ ሳዲቅ የቀረበ ሲሆን በክፍለ ከተማው ጽ/ቤት ውስጥ ላሉ የጽ/ቤቱ ሠራተኞች የስራ ተነሳሽነት በተቋም ያለው ጥቅም፣ የስራ ተነሳሽነት ላይ በጎ ተፅዕኖ ያላቸው ጉዳዮች እና አስፈላጊነት ዙሪያ የራሳቸውን ልምድ ያካፈሉ ሲሆን በእውቀት ሽግግሩ ላይ በተገኙ ሰራተኞች በቀረበው የእውቀት ሽግግር ርዕስ ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጎበት የተገኘውን እውቀት መሰረት በግለሰብ ደረጃ የስራ ተነሳሽነትን በመጨመር የጽ/ቤታችንን አፈፃፀም ከፍ ለማድረግ የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ የዛሬው የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር ተጠናቋል፡፡
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/addisketemaeducationoffice
09/02/2026
የአ/ከ/ክ/ከተማ ት/ጽ/ቤት የጥናትና ምርምር ኮሚቴ የተመረጡ ጥናትና ምርምሮች ፅብረቃ አደረገ።
የካቲት 02/2018ዓ.ም
የአ/ከ/ክ/ከተማ ት/ጽ/ቤት የጥናትና ምርምር ኮሚቴ በ6ወራት ውስጥ የተሰሩ የተመረጡ የጥናት ውጤቶችን ባለ ድርሻ አካላት በተገኙበት በዛሬው እለት ፅብረቃ አድርጓል።
በዚህ ክፍለ ከተማ አቀፍ የጥናትና ምርምር ፅብረቃ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የክፍለ ከተማው የጥናትና ምርምር ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ አዳነ ከፍያለው በዚህ 6ወራት ውስጥ በክፍለ ከተማው በሚገኙ የመንግስት ትምህርት ቤቶች ውስጥ የተሰሩ ጥናቶችን በመሰብሰብ እንደ ኮሚቴ ግምገማ በማድረግ ደረጃ ማውጣት መቻሉን ጠቅሰው በዛሬው እለትም ከአንድ እስከ ሶስተኛ የወጡ የጥናት ውጤቶችን ፅብረቃ ተደርጎባቸው ለሌሎች ልምድ ለማካፈልና የጥናት ውጤቶቹን በክፍለ ከተማው በሚገኙ ት/ቤቶች ወደ ተግባር ለመቀየር ታስቦ የተዘጋጀ መድረክ መሆኑን ገልፀዋል።የእለቱ የክብር እንግዳ የሆኑት የክፍለ ከተማው መምህራን ማህበር ሰብሳቢ የሆኑት ወ/ሮ ፋንታነሽ በትምህርት ቤት ደረጃ የሚያጋጥሙ የተለያዩ ትምህርታዊ ችግሮችን ለመፍታት ጥናትና ምርምር ዋናው መፍትሄ መሆኑን ገልፀው ይህን የፅብረቃ መርሃ ግብር ያዘጋጀውን የክፍለ ከተማውን የጥናትና ምርምር ኮሚቴ አመስግነዋል።
በመቀጠልም በክፍለ ከተማ ደረጃ የተመረጡ እና ደረጃ ውስጥ የገቡ ጥናትና ምርምሮች ጥናቱን በሰሩት አካላት ፅብረቃ ተደርጎበትና ሰፊ ውይይት ተደርጎበት የእለቱ መርሃ ግብር ተጠናቋል።
በዚህ ፅብረቃ መርሃ ግብር ላይ የ2ኛ ደረጃ ሱፐርቫይዘሮች፣ የ1ኛ ደረጃ ሱፐርቫይዘር አስተባባሪዎች፣ የት/ቤቶች ርዕሰ መምህራንና የክፍለ ከተማ ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/addisketemaeducationoffice
09/02/2026
ሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር ተካሄደ፡፡
ሰኞ የካቲት 02/2018 ዓ.ም
የሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር የጽ/ቤቱ ኃላፊ እንዱሁም የስራዎች አስተባሪዎች እና ሠራተኞች በተገኙበት ተካሂዷል፡፡
የሰኞ ማለዳ የሠራተኞች የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር "በቡድን መስራት/TeamWork/" በሚል ርዕስ ዙሪያ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት የትምህርት መረጃና ኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ ቡድን መሪ በሆኑት አቶ ተካልኝ ጌታቸው የቀረበ ሲሆን በክፍለ ከተማው ጽ/ቤት ውስጥ ላሉ የጽ/ቤቱ ሠራተኞች በቡድን ስራ ምንነት፣ በቡድን ስራ አስፈላጊነት እንዲሁም የጠንካራ ቡድኖች ባህሪያት እና በቡድን ስራ ውስጥ ወሳኝ አይቀሬ በሆኑት በተግባቦትና የግጭት አፈታት ክህሎት የራሳቸውን ልምድ ያካፈሉ ሲሆን በእውቀት ሽግግሩ ላይ በተገኙ ሰራተኞች በቀረበው የእውቀት ሽግግር ርዕስ ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጎበት የተገኘውን እውቀት መሰረት በቢሮ ውስጥ በቡድን በመስራት የጽ/ቤታችንን ከፍ ለማድረግ የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ የዛሬው የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር ተጠናቋል፡፡
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/addisketemaeducationoffice
07/02/2026
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የካቲት 2/2018 ዓ.ም ይጀምራል፡፡
(ጥር 30/2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የካቲት 2/2018 ዓ.ም የሚጀምር መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
መልካም የትምህርት ዘመን!
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
31/01/2026
2ኛው ከተማ አቀፍ የተማሪዎች የስፖርት ሊግ እና የመምህራን ስፖርታዊ ውድድር የመክፈቻ መርሀ ግብር የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ልዑክ በፎቶ:
ጥር 23/2018 ዓ.ም
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች:
https://linktr.ee/Addis meters education office
26/01/2026
የአ/ከተማ ክ/ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት በመልካም አስተዳደር ምንነትና ልየታ እንዲሁም በቅሬታ አቀራረብና አፈታት ደንብ ቁጥር 143/2015 ዙሪያ ስልጠና ሰጠ።
ጥር 18/2018ዓ.ም
የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት በመልካም አስተዳደር ምንነትና ልየታ እንዲሁም በቅሬታ አቀራረብና አፈታት ደንብ ቁጥር 143/2015 ዙሪያ ለሚመለከታቸው የትምህርት ባለ ድርሻ አካላት በዛሬው ዕለት ስልጠና ሰጥቷል።
ይህን ስልጠና የሰጡት የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት የስራዎች አስተባባሪ የሆኑት አቶ ብርሃኑ ቱጂ ሲሆኑ በከተማ አስተዳደሩ በፀደቀው በመልካም አስተዳደር ምንነትና ልየታ እና በቅሬታ አቀራረብና አፈታት ደንብ ቁጥር 143/2015 ላይ ያተኮረ ሲሆን በስልጠናው ላይም የመልካም አስተዳደር ችግሮች መለያ መስፈርት እንዲሁም በከንቲባ ጽ/ቤት በፀደቀው የመልካም አስተዳደር እቅድ ማዘጋጃ ቢጋር ዙሪያ ሰፊ ስልጠና የተሰጠ ሲሆን በመቀጠልም በቅሬታ አቀራረብ እና አፈታት ደንብ ቁጥር 143/2015 ላይ ለተሳታፊዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ተሰጥቷል።
በስልጠናው ማጠቃለያ ላይም የስልጠናው ተሳታፊዎች በተቋም ደረጃ ከዚህ በኋላ የመልካም አስተዳደር ልየታ ሲደረግ በከተማ አስተዳደሩ ወረደው ቢጋር መሰረት እንዲሆንና በተቋማት ደረጃ ያለው የቅሬታ አቀራረብና አፈታት ስርዓት በፀደቀው ደንብ መሰረት እንዲሆን ስልጠናውን የሰጡት የጽ/ቤቱ የስራዎች አስተባባሪ የሆኑት አቶ ብርሃኑ ቱጂ መልዕክታቸውን በማስተላለፍ ስልጠናው ተጠናቋል።
በዚህ ስልጠና ላይ ሁሉም የመንግስት 1ኛ ደረጃ እና 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ዋና ርዕሳነ መምህራን፣ሁሉም የክፍለ ከተማ ቡድን መሪዎች፣ሱፐርቫይዘሮችና ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች:
https://linktr.ee/addisketemaeducationoffice
26/01/2026
ሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር ተካሄደ፡፡
ሰኞ ጥር 18/2018 ዓ.ም
የሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር የጽ/ቤቱ ኃላፊ እንዲሁም የስራዎች አስተባሪዎች እና ሠራተኞች በተገኙበት ተካሂዷል፡፡
የሰኞ ማለዳ የሠራተኞች የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር "እርግብ ፕሮግራም" በሚል ርዕስ ዙሪያ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት የ2ኛ ደረጃ ት/ቤት የአፋን ኦሮሞ ሱፐርቫይዘር በሆኑት በአቶ ደበላ ዋሲሁን የቀረበ ሲሆን በክፍለ ከተማው ጽ/ቤት ውስጥ ላሉ የጽ/ቤቱ ሠራተኞች X እንዴት ወደ E የሚቀየርበትን የራሳቸውን ልምድ ያካፈሉ ሲሆን የጋራ መግባባት ላይ የተደረሰ ሲሆን በመርሃ ግብሩ መጨረሻ ላይ የጽ/ቤቱ አስተባባሪ በሆኑት በአቶ ቤኩማ ደበሎ አማካኝነት ማጠቃለያ ተሰጥቶበት የእለቱ መርሃ ግብር ተጠናቋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች:
https://linktr.ee/addisketemaeducationoffice
24/01/2026
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በክፍለ ከተማ ደረጃ ሲያካሂድ የነበረውን የመምህራንና የተማሪዎች የስፓርት ሊግ ውድድር ዛሬ ተጠናቀቀ።
ጥር 16/2018ዓ.ም
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ 'በአካል ብቁና በአዕምሮ ንቁ ትዉልድ ለሀገር ብልፅግና! ' በሚል መሪ ቃል በክፍለ ከተማ ደረጃ ከጥር 5/2018 ጀምሮ ሲያካሂድ የነበረውን የመምህራንና የተማሪዎች የስፓርት ሊግ ውድድር ዛሬ አጠናቋል።
በዚህ የስፓርት ሊግ ውድድር በተለያዩ የስፓርት አይነቶች በወንድ እና በሴት በመምህራን አና በተማሪዎች መካከል ውድድር እየተደረገ የቆየ ሲሆን በዛሬው እለትም የተለያዩ የክብር እንግዶች በተገኙበት ለአሸናፊ መምህራንና ተማሪዎች የዋንጫ እና የሰርተፊኬት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
በዚህ የመዝጊያ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የጽ/ቤቱ የስራዎች አስተባባሪ የሆኑት አቶ ቤኩማ ደበሎ አሸናፊዎችን እንኳን ደስ ያላችሁ በማለት በዚህ በክፍለ ከተማ ደረጃ በተደረገው ስፓርት ሊግ ውድድር ላይ በተለያዩ ስፓርቶች አይነቶች በመምህራንና በተማሪዎች ተሰጥዖ ያላቸው ስፓርተኞችን ማየት የተቻለ ሲሆን በቀጣይም በከተማ ደረጃ ለሚካሄደው የስፓርት ሊግ ውድድር ክፍለ ከተማውን ሊወክሉ የሚችሉ ተጫዋቾችን መምረጥ ተችሏል ብለዋል። በመቀጠልም ይህ ውድድር ስኬታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ አስተዋፅኦ ላደረጉ አካላት ምስጋና እቅርበዎል።
በዚህ የመዝጊያ መርሃ ግብር ላይ የትምህርት ባለድርሻ አካላት፣ የት/ቤት ር/መምህራን፣ መምህራን ፣ ተማሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች ተሳታፊ ሆነዋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች:
https://linktr.ee/addisketemaeducationoffice
22/01/2026
የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት የአገልግሎት አሰጣጥ መማክርት ጉባዬ የ2018 በጀት ዓመት በ6 ወር የተከናወኑ ተግባራት አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ።
ጥር 14/2018ዓም
የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ት/ጽ/ቤት
የአገልግሎት አሰጣጥ መማክርት ጉባዬ በ6ወራት የተከናወኑ ተግባራት አፈፃፀምን የመማክርት ጉባዬ አባላት በተገኙበት አስገምግሟል።
በመማክርት ጉባዬ ሰብሳቢ አማካኝነት በ6ወራት ውስጥ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትና በቀጣይ መከናወን ያለባቸውን ተግባራት ሪፓርት ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን በዚህ ግምገማ ላይ የተገኙት የጽ/ቤቱ የስራዎች አስተባባሪ የሆኑት አቶ ቤኩማ ደበሎ በዚህ 6ወር ውስጥ የተሰሩ ስራዎችን ለቀጣይ በማስቀጠልና የሚቀሩ ተግባራትን በቅንጅት በመስራት ጽ/ቤቱን እንዲሁም በስሩ የሚገኙ ተቋማትን ውጤታማ ማድረግ እንደሚገባ ገልፀዋል።
በመጨረሻም በመማክርት ጉባዬው በቀጣይ መሰራት በሚገባቸውን ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት በመድረስ ግምገማው ተጠናቋል።
https://linktr.ee/addisketemaeducationoffice
16/01/2026
የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት 6 ወር የስራ አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ።
ጥር 8-2018ዓም
የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ት/ጽ/ቤት
በ6ቱ ቁልፍና አበይት ስራዎች አፈፃፀም፣ በቅንጅታዊ ትስስር እና በመልካም አስተዳደር የተሰሩ ስራዎች ሪፓርት በስራዎች አስተባባሪ በሆኑት አቶ ብርሃኑ ቱጂ ቀርቦ የትምህርት ባለድርሻ አካላት እና የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ብሩክ ተ/ማርያም በተገኙበት ግምገማ ተደርጓል ።
በተጨማሪም በመደመር መንግሥት የዘርፎች እምርታ ላይ በትምህርት ዘርፉ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር እና በግማሽ ዓመቱ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ከማሻሻያ አንፃር ሰፋፊ ስራዎች መሰራታቸውን የጽ/ቤቱ የስራዎች አስተባባሪ የሆኑት አቶ ቤኩማ ደበሎ ገልፀዋል።
የጽ/ቤቱ የስራዎች አስተባባሪ የሆኑት አቶ ብርሃኑ ቱጂ በበኩላቸው በመጀመሪያ ስድስት ወራት የተመዘጉ ውጤቶችን አጠናክሮ የማስቀጠልና ትኩረት የሚፈልጉ ጉዳዮች ጠንክሮ መስራትና የባለድርሻ አካላት ቅንጅት በማጠናከር በትምህርት ዘርፉ ስኬታማነት ለማረጋገጥ ልንረባረብ ይገባናል ብለዋል።
በመጨረሻም የጽ/ቤቱ ኃላፊ በሆኑት አቶ ብሩክ ተ/ማርያም የቀጣይ የትምህርት ሴክተሩ ቀጣይ ሊሰሩ የሚገባቸውን የትኩረት አቅጣጫዎች በማሳወቅ የእለቱ መርሃ ግብር ተጠናቋል።
https://linktr.ee/addisketemaeducationoffice