21/04/2024
!
፨፨////፨፨፨፨////፨፨
ቀናችሁን በፈገግታ ጀምሩ፣ በጠዋት ስሜታችሁን አስተካክሉ። የተበላሹ፣ ያልተሳኩ፣ የሚያበሳጩ፣ የሚያስጨንቁ ሀሳቦችን ለዛሬ ተዎአቸው። ስለዛሬ ቀናችሁ ብቻ አስቡ፣ አሁን ስላላችሁበት፣ አሁን በመዳፋችሁ ስለጨበጣችሁት፣ እግዚአብሔር ስላደላችሁ ፀጋ ብቻ አስቡ። ውስጡ እየተረበሸ ፈገግታን የመረጠ ሰው፣ በከባድ ሁኔታዎች መሃል እራሱን መንከባከብ የማይረሳ ሰው፣ ካጋጠመው ከባድ ሁኔታ በላይ ለእራሱ ደህንነት ቅድሚያ የሚሰጥ ሰው በጣም ጠንቃራው ሰው ነው። ቀናችሁ ስጦታችሁ ነች፣ ህይወታችሁ በረከታችሁ ነች። የሚያስደስት ነገር ባትመለከቱባት እንኳን ተስፋ አትቁረጡባት፣ ችላ አትበሏት፣ ዋጋ አታሳጧት። ጥቂት የማይባል ሰው ፀሃይ ማየት ይናፍቀዋል፣ ግማሹ የመራመድን ስሜት ማጣጣም ይናፍቃል፣ አንዳንዱ ማውራትን ይመኛል። እናንተ ግን የሰውን ሁሉ ምኞት ያለምንም ክፍያ እያገኛችሁ ከሆነ ስለምን ለትርፍ ነገር ብላችሁ በትካዜ ትዋጣላችሁ? ስለምን ታይቶ በሚጠፋ ጊዜያዊ ችግር ተሰብራችሁ ትቀራላችሁ?
፨፨////፨፨፨፨////፨፨
አዎ! ፈገግ በሉ! እራሳችሁን ዘና አድርጉ፣ የምትወዱትን ምህዳር ለራሳችሁ ፍጠሩ። የወጪው ጩሀትና ወሬ ላይ አተኩራችሁ የእኔ የምትሉትን ንፁ ሰላማችሁን አትጡ። ውጪውን መቆጣጠር ባትችሉ ጆሯችሁ የሚሰማውን፣ አይናችሁ የሚያየውን፣ እግራችሁ የሚሔድበትን፣ እጃችሁ የሚያነሳውንና አፋችሁ የሚናገረውን መቆጣጠር ትችላላችሁ። ማናችንም በራሳችን ሰውነት ላይ ስልጣን እንዳለን በምንም ላይ ስልጣን የለንም። ነገር ግን ስልጣናችንን በአግባቡ እየተጠቀምነው ስለመሆናችን እርግጠኛ መሆን አንችልም። ባህርማዶ የተከናወነ ነገር ሲረብሸን፣ የማይመለከተን ክንውን ቀናችንን ሲያውከው፣ ከእኛ ህይወት ጋር የማይገናኝ ተግባር ሰላም ሲያሳጣን መመልከት ልማዳችን ሆኗል። የዓለምን ገፅ እናስተውል ብዙ ጥሩ ነገር ቢኖርም ከየአቅጣጫው የሚነገረን ነገር ግን አስከፊውና አሳዛኙ ነው፣ ብዙ ደጋግ ተግባራት ቢኖሩም በየዘርፉ ለእይታችን የሚቀርቡት ግን ጥፋትና በደሎች ናቸው። ስሜቱ የተጎዳን ሰው መግዛት፣ ውስጡ የተረበሸን ሰው መምራት ቀላል ነውና የሚላክብን ነገር ሁሉ ቸልተኛና ልፍስፍስ እንዲያደርገን ታስቦ የሚላክብን ለዚህ ነው።
፨፨////፨፨፨፨////፨፨
አዎ! ጀግናዬ..! ለቀንህ ዋጋ ስጥ፣ በሚገባ አስብለት። ውሎህ ያስጨንቅህ፣ ለስሜትህ መውጣትና መውረድ ትኩረት ስጥ። በምን ተከበህ ምን እየፈለክ እንደሆነ እወቅ፤ ምን መርጠህ የቱጋ እንደቆምክ አስተውል። ውዱን ፈገግታህን በማይመለከትህ ነገር አትጣው፣ ደስታህ በቀላሉ እንዲርቅህ አትፍቀድ። በሆነባልሆነው እየተበሳጨህ ህይወትህን አሰልቺ አታድርጋት። ስላለህበት ሁኔታ አንተ ታውቃለህ፣ እያንዳንዱ ያጋጠመህ ነገር ላንተ ግልፅ ነው። ነገር ግን ማወቅህ ውስጥህን እንዲረብሽ አትፍቀድ፣ የተረዳሀው ነገር ቀንህን እንዲያጨልም አታድርግ። ማንም የሚረዳህ በሌለበት ዓለም በየመንገዱ የውስጥ ስሜትህን እያሳየህ አትሂድ። የሚያበሳጭ ነገር ሲመጣ በልኩ ተበሳጭ፣ የሚያስጨንቅ ሁኔታም ቢገጥምህ በልኩ ተጨነቅ። የትኛውንም ስሜት እንደ አመጣጡ ማስተናገድ ተለማመድ። ፈገግታ የጠንካሮች ምልክት ነውና በስተመጨረሻ በእውነተኛ ፈገግታህ ማሳረግህን እንዳትረሳ።
ግሩም ድንቅ ቀን ይሁንልን!
18/09/2023
07/01/2016 ዓ.ም የት/ት አጀማመር
13/09/2023
ማስታወቂያ
ለተማሪ ወላጆች በሙሉ
እንኳን ለ2016 ዓም የት/ት ዘመን በሰላም አደረሳቹ አደረሰን እያልን የ2016 ዓም ት/ት የሚጀመረው መስከረም 7/2016 ዓም መሆኑ ይታወቃል በመሆኑም በት/ት ዘመኑ አጠቃላይ ተግባራት ማለትም በሰላማዊ መማር ማስተማር ሂደት የተማሪዎች ውጤት እና ስነ ምግባር መሻሻል ዙሪያ በት/ቤቱ ልማት ዙሪያ እንዲሁም በት/ቤቱ የ2015 ዓም እቅድ አፈፃፀም እና የ2016 ዓም እቅድ ዝግጅት ዙሪያ ላይ ውይይት ስለምናደርግ በ6/1/2016 ዓም ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በት/ቤቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ እንድትገኙ እናሳውቃለን
ት/ቤቱ
Eshet Pre-Primary and Primary school
👉
Eshet Library 👉
26/07/2023
የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ማሻሻል ተወዳዳሪ ዜጎችን ለማፍራት ወሳኝ ሚና አለዉ።
==============
ይህን ሀገር አቀፍ “ትምህርት ለትውልድ" ህዝባዊ ንቅናቄ በመቀላቀል ዉጤታማ ትዉልድ እናፍራለ።
የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ማሻሻል ነገይቱን ኢትዮጵያ የሚሰሩ ተወዳዳሪ እና ምርታማ ዜጎችን ለመፍጠር ወሳኝ ነዉ ፡፡
በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ ያለው “ትምህርት ለትውልድ “ ሀገራዊ ንቅናቄ የትምህርት ተቋማትን በማሻሻል በእውቀታቸውና በችሎታቸው በአለምአቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ዜጋ ለመፍጠር ያለመ ነዉ።
ሀገር እንድትበለጽግና ቀጣይ ጊዜን የሚመጥን ትውልድ እንዲገነባ ትምህርት ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ይገባል ፡፡በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጪ ያላችሁ ማህበረሰቦች እንዲሁም የልማት አጋሮች ፣ባለሀብቶችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ይህ ወሳኝ ዓላማ ግቡን እንዲመታ ገንዘባችሁን ፣ እውቀታችሁንና ጉልበታችሁን በማስተባበርና በማቀናጀት ከጎናችን እንድትሰለፉ ጥሪ አናቀርባለን፡፡ Eshet Pre-Primary and Primary school
👉
Eshet Library 👉
26/07/2023
የእሸት ቅድመ አንደኛና የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት
"ትምህርት ለትውልድ"
ፊደል የቆጠርንባት፣ የልጅነት ትዝታችንና ፍቅራችን የተቀረፀባት፣ ጥሩና መጥፎን የለየንባት፣ የዜግነት ክብር ብለን የዘመርንባት፣ ከድንቁርና ዓለም ተለይተን እውቀትና ጥበብ የቀሰምንባት፣ ሙሉ ሰው ሆነን ማሰብ የቻልንባት በጥሩ ሥነ- ምግባር ያደግንባት ትምህርት ቤታችን፣ በተለያዩ የትምህርት ጥራት ችግሮች ውስጥ ያለች በመሆኗ ሙሉ እንድትሆንና የመማር ማስተማር ሂደቱም ምቹ እንዲሆን የትምህርት ቤት መሠረት ልማት ለመማር ማስተማር ስራው ዋናው ቁልፍ ጉዳይ በመሆኑ የትውልድ ጉዳይ የሚያሳስበው የቀድሞ ተማሪዎች፣ ባለሀብቶችና ማንኛውም በጎ አድራጎት ድርጅት የእሸት ቅድመ አንደኛና የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ድረስ በመምጣት የጎደለንን ቁሳዊ ሀብት ታሟሉልን ዘንድ በት/ቤታችን የትምህርት ማህበረሰብና ተማሪዎች ስም እንጠይቃለን፡፡
Eshet Pre-Primary and Primary school
👉
Eshet Library 👉
17/07/2023
ለትምህርት ቤታችን መምህራን ፣ ሰራተኞችና ባለድርሻ አካላት እዉቅናና ሽልማት ተሰጠ ።
ይህ ፕሮግራም እንዲሳካ ላደረጋችሁ የትምህርት ቤቱ ሶሻል ኮሜቴ ፣ ማኔጅመንት እና ባለድርሻ አካላት።
ትምህርት ቤቱ ከልብ ያመሰግናል ።
ሀምሌ 8/11/2015 ዓ.ም
Congratulations
This is the end of 2015 E.C🪕🎻🎸❤️❤️❤️❤️
14/07/2023
ሸር የሚደረግላቸው አካላት
1. ቀደም ሲል በእሸት ት/ቤት ልጆቻቸውን አስተምረው ለቁም ነገር የደረሱላቸው ወላጆች
2. በዚህ ት/ቤት የተማሩ የቀድሞ ተማሪዎች
3. በዚህ ት/ቤት ሲሰሩ የነበሩ መምህራን፣ አስተዳደር ሰራተኞች ወዘተ የት/ቤቱ ፍቅር፣ ውለታ ፣ ትዝታ አለብኝ ለሚሉ በሙሉ ሸር በማድረግ ለነገ ተረካቢ ትዉልድ ግንባታ እንስራ።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
Eshet Pre-Primary and Primary school
👉
Eshet Library 👉
12/07/2023
ቀን 5/11/2015 ዓ.ም
ለሁሉም የእሸት ቅደመ አንደኛደረጃና የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ማህበረሰብ በሙሉ (ለመምህራን ፣ ለተማሪዎች ፣ ለወላጆች ፣ ወዘተ
ት/ቤታችን የቀድሞው ተማሪዎች ጋር ተገናኝቶ መወያየት ይፈልጋል። በመሆኑም የቀድሞ ተማሪዎችን የምታውቁ ማለትም በእሸት ቅደመ አንደኛ ደረጃና የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ተምረው ያጠናቀቁ በማንኛውም ቀን ተገኝተው ቢሮ ሪፖርት እድያደርጉልን ጥሪያቸውንን እናቀርባለን።
በውጭ የሚገኙ ከሆነም በሌሎች አማራጭ የምናገኝበት መንገድ ስላለ እንድታሳውቁልን እናሳስባለን።
እኔ የእሸት ውለታና ትዝታ አለብኝ የሚል ሸር ሸር ያድርግ
የቀድሞ ተማሪዎች
የቀድሞ ተማሪዎች
የቀድሞ ተማሪዎች
የቀድሞ ተማሪዎች
የቀድሞ ተማሪዎች
የቀድሞ ተማሪዎች
የቀድሞ ተማሪዎች
የቀድሞ ተማሪዎች
የቀድሞ ተማሪዎች
የቀድሞ ተማሪዎች
የቀድሞ ተማሪዎች
የቀድሞ ተማሪዎች
የቀድሞ ተማሪዎች
የቀድሞ ተማሪዎች
የቀድሞ ተማሪዎች
የቀድሞ ተማሪዎች
የቀድሞ ተማሪዎች
የቀድሞ ተማሪዎች
የቀድሞ ተማሪዎች
የቀድሞ ተማሪዎች
እያለች እሸት ትጣራለች አቤት የሚላት ትፈልጋለች
ሁሉም ሸር ሸር በማድረግ 1 ሰው ቢያንስ ለ5 ሰው እንድያሳውቅ በትንሹ እናሳስባለን።