02/05/2026
የቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 01 ትምህርት ጽ/ቤት የ2018 የ2ኛ ሴሚስተር የ6ኛ የ8ኛ ክፍሎች በአማርኛ ቋንቋ የጥያቄና መልስ ውድድር አካሄደ፡፡
በውድድሩ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቦሌ ወረዳ 01 ት/ርት ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ አሚና ዎሸ ሲሆን ለተማሪወቹ ያስተላለፉት መለዕክት በዛሬው እለት በዚህ ውድድር ተሳትፋችሁ ከ1ኛ እስከ 3ኛ ደረጃ የምትወጡ ተማሪወች በቀጣይ በክ/ከተማና በከተማ ደረጃ በሚካሄደው ውድድር ወረዳውን እና ት/ቤታችሁን ወክላችሁ ትሳተፋላችሁ፡፡
በዚህ መሰረትም መምህራኖቻችሁ ለእናንተ ይመጥናል ብለው ያዘጋጁላችሁን ጥያቄ በጥሩ ሁኔታ ተረጋግታችሁ እንድትመልሱ ሲሉ አሳስበዋል፡፡
በውድድሩ ላይ የተሳተፉት የቦሌ ቃለሕይወት 1ኛ ደረጃ ት/ቤትና የአየር አምባ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪወች ሲሆኑ ተማሪወቹም በየተመደበላቸው የመወዳደሪያ ክፍል በመግባት ውድድራቸውን አካሂደዋል፡፡
በመጨረሻም ከውድድሩ መጠናቀቅ በሗላ በየክፍላቸው ከ1 እስከ 3 ለወጡት ተማሪወች የመጽሀፍና ሰርትፍኬት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡ከዚህ ጋር ተያይዞ ጽ/ቤቱ ይህ ውድድር እንዲያካሄድ የበኩላቸውን ድጋፍ ላደረጉ ተቋማት የእውቅና ሽልማት በመስጠት የእለቱ ዝግጅት ተ ናቋል፡፡
መረጃዎቻችንን በተለያየዬ አማራጮች ለማግኘት
https://linktr.ee/Boleworeda01
ቦሌ ወረዳ 01 ኮሙኒኬሽን
ሚያዝያ 22/2018 ዓ.ም
Boleworeda01 | Instagram, Facebook, TikTok | Linktree Linktree. Make your link do more.
02/05/2026
13/04/2025