04/11/2023
ውድ ወላጆች
ትናንት ዓርብ 24/2016ዓ.ም በለሚ ኩራ
ክ/ከተማ ወረዳ 14 ትምህርት ፅ/ቤት አመቻችነት በወረዳው የሚገኙ የግል እና የመንግስት የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤቶች በትምህርት ቤታችን በመገኝት የልምድ ልውውጥ ያደረጉ ሲሆን ይህም ሊሆን የቻለው ት/ቤታችን በወረዳው ከሚገኙ
ት/ቤቶች መካከል በሞዴልነት በመመረጡ መሆኑን እየገለፅን ሁሉንም የት/ቤት ማህበረሰብ እንኳን ደስ አላችሁ።
የት/ቤቱ አስተዳደር
10/10/2023
ውድ ወላጆች:
👆ከላይ የምትመለከቱት ለሁሉም የክፍል
ደረጃ ለሚገኙ ተማሪዎች የተዘጋጀ
የስፖርት ልብስ ነው።
ዋጋ: 1,900 ብር
የሚከፈልበት የባንክ ቁጥር :15664444
Bezawit Asrat Abyssinia
የሚገኝበት ቦታ: ለሃያት KG ተማሪዎች
በሃያት ግቢ ሲሆን
ለገደራ ሁለተኛ ደረጃ፣ለአንደኛ ደረጃ እና
ለKG ተማሪዎች ደግሞ ገደራ በሚገኘው
ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት መሆኑን እየገለፅን
ከዛሬ ከመስከረም 29/2015 ዓ.ም
ጀምሮ የከፈላችሁበትን ደረሰኝ ይዞ
በመምጣት መውሰድ የምትችሉ መሆኑን
እናሳውቃለን።
የት/ቤቱ አስተዳደር
27/09/2023
ለመላው የኦዞን ት/ቤት የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ።
በዓሉም የደስታ ፣ የሰላም ፣ የፍቅር ፣ የመተባበር እና የጤና እንዲሆንላችሁ እንመኛለን፡፡
+ እሰይ እልል በሉ
ተገኘ መስቀሉ +
መልካም የመስቀል በዓል!
26/09/2023
ለመላው የኦዞን ት/ቤት የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1498ኛው የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
በዓሉም የደስታ ፣ የሰላም ፣ የፍቅር ፣ የመተባበር እና የጤና እንዲሆንላችሁ እንመኛለን፡፡
መልካም የመውሊድ በዓል!
ዒድ ሙባረክ!
22/09/2023
ውድ የተከበራችሁ ወላጆች :-
ከሰኞ መስከረም 14/2016 ዓ.ም ጀምሮ
ትምህርት የሚሰጠው ሙሉቀን መሆኑን
እየገለፅን የተማሪዎች የደንብ ልብስ
(uniform ) ስለተዘጋጀ ሃያት የሚገኘው
ቅርንጫፍ በመሄድ መረከብ የምትችሉ
መሆኑን ት/ቤቱ ይገልፃል።
የት/ቤቱ አስተዳደር
14/09/2023
ውድ ወላጆች እንኳን 2016ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሰላም አደረሳችሁ
* የ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የሚጀምረው ሰኞ መስከረም 07/2016ዓ.ም ሲሆን ከስኞ እስከ ዓርብ ትምህርት የሚስጠው ለግማሽ ቀን ይሆናል።
◻️◻️◻️◻️◻️◻️◻️◻️◻️◻️◻️◻️◻️◻️
* የጀማሪ(Nursery) ፣ የ1ኛ ክፍል እንዲሁም
የ9ኛ እና የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች ትምህርት
የሚጀምረው መስከረም 14/2016ዓ.ም
ሲሆን ትምህርት የሚሰጠውም ሙሉቀን
ይሆናል ።
◻️◻️◻️◻️◻️◻️◻️◻️◻️◻️◻️
* የ2015ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ተፈታኝ
ተማሪዎች የውጤት መግለጫ ካርድ
ስለመጣ የተሰጡ/ የወሰዳችሁትን
የመማሪያ መፅሃፍትን በመመለስ
ውጤታችሁን ከነገ መስከረም
04/2016ዓ.ም ጀምሮ መውስድ
ትችላላችሁ።
◻️◻️◻️◻️◻️◻️◻️◻️◻️◻️◻️◻️◻️
* የ2016ዓ.ም የትምህርት ዘመን መታወቂያ
ካርድ ስለተዘጋጀ ልጆቻችሁ በሚማሩበት
ቅጥር ግቢ ከነገ ጀምሮ በመገኘት
እንደትወስዱ ፎቶግራፍ ያላመጣችሁ
ወላጆች ፎቶግራፍ ይዛችሁ እንድትመጡ
ትምህርት ቤቱ ያሳስባል።
የት/ቤቱ አስተዳደር
03/09/2023
ውድ የኦዞን ት/ቤት የ 2016 ዓ.ም ተማሪዎች እና ወላጆች:-
~ ት/ቤታችን የተማሪዎችን የ2016 ዓ.ም
መታወቂያ ካርድ እያዘጋጀ ይገኛል።
ስለዚህ ለነባር ተማሪዎች ለእያንዳንዳቸው
ሁለት ጉርድ ፎቶግራፍ እስከ ጰጉሜ 4፣
2015 ዓ.ም ገቢ እንድታደርጉ በትህትና
እና በማክበር እናሳስባለን።
የት/ቤቱ አስተዳደር
31/08/2023
ውድ የኦዞን ት/ቤት የ 2016 ዓ.ም የ9ኛ እና 10ኛ ክፍል ተማሪዎች እና ወላጆች:-
~ከሰኞ ነሐሴ 22ቀን፣2015 ዓ.ም ጀምሮ
የ 2016 ዓ.ም የ9ኛ እና 10ኛ ክፍል
ተማሪዎች ምዝገባ ይጀምራል።
በመሆኑም
~ክፍያው ገቢ የሚሆነው በአቢሲኒያ የባንክ
ቁጥር 150548659 ይሆናል።
~ከክፍያ በኋላ ወላጆች ደረሰኝ ይዘው
ት/ቤት በመምጣት የምዝገባ ቅፅ መሙላት
ይኖርባቸዋል።
~የምዝገባ ቅፅ ለመሙላት:-
ሀ. ለነባር ተማሪዎች የተማሪዎች 2 ጉርድ
ፎቶግራፍ ፤
ለ. ለአዲስ ተማሪዎች
~የተማሪዎች 2 ጉርድ ፎቶግራፍ
~የእናት እና የአባት አንድ አንድ ጉርድ ፎቶ
~የልደትና የክትባት ሰርተፍኬት ኮፒ
~የእናት እና የአባት መታወቂያ ኮፒ
~ያለፈው አመት የትምህርት ዘመን
ሰርተፍኬት ኮፒ እና ከነበሩበት ትምህርት
ቤት መሸኛ ይዘው መምጣት
ይኖርባቸዋል።
የት/ቤቱ አስተዳደር
01/08/2023
በ2015 ዓ.ም. አገር አቀፍ ብሄራዊ ፈተና ወስደዉ ከፍተኛ ዉጤት ያሰመዘገቡ የ8ኛ ክፍል ብርቅዬ የኦዞን ት/ቤት ተማሪዎች::