ኢትዮጵያውያን ቅዱሳን Ethio Kidusan

ኢትዮጵያውያን ቅዱሳን Ethio Kidusan

Share

education

Photos from ኢትዮጵያውያን ቅዱሳን Ethio Kidusan's post 05/06/2024

ግንቦት ፴ (30)
፡፡
ወበዛቲ ዕለት፤ በዚህች ግንቦት 30 ቀንም የጻድቋ ዜና ማርያም በዓለ ልደቷ ነው፡፡
ጻድቋ፤
፠ በቅዱሱ ንጉሥ ላሊበላ ዘመነ መንግሥት በጎጃም ምድር ከአባቷ ገብረ ክርስቶስና ከእናቷ ዓመተ ማርያም ግንቦት 30 ተወለደች፡፡
፠ በዋሻ እንድርያስ ገዳም ገብታ ለ25 ዓመት በጾም በጸሎት ተጋደለች፤
፠ ከሦስት ቅዱሳን (አቡነ እንድርያስ ከጣራ ገዳም፤ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከዋሻ ተክለ ሃይማኖትና ቅድስት ዜና ማርያም ከደሪጣ ገዳሟ ሆነው) በጸጋ እግዚአብሔር ከያሉበት ሆነው ይነጋገሩ ነበር፡፡
፠ ቅዱስ ላሊበላ በ11ኛው ክፍለ ዘመን ገዳሟን አንጾላታል፤ ዐፄ ይስሐቅ በ14ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በስሟ ገድሞላታል፡፡

ዜና ታሪኳን በበዓለ ዕረፍቷ ቀን በነሐሴ 30 ቀን በስፋት ጽፈነዋል፡፡
ለእግዚአብሔር ክብር ይሁን፤ እኛንም በጻድቋ ዜና ማርያም ጸሎትና አማላጅነት ይማረን፤ አሜን፡፡
/ / ገጽ

27/05/2024

? ?

ቦታው፤
* ላስታ፥ ላሊበላ (ከላሊበላ ከተማ በእግር በአቋራራጭ 7 ሰዐት፤ በመኪና የ2 ሰዐት ያስጒዛል)፤ ነገር ግን ብዙዎቻችን ላሊበላ ደርሰን ስንመጣ ስለ ቦታው እንኳን መረጃ የለንም!!!

* ተራራው በሀገራችን ከራስ ደጀን እና ከባሌ ተራሮች ቀጥሎ በ3ኛነት ያለ ነው፤
** የቅዝቃዜው ማየል ደንጋዩን ሳይቀር አሸብቶቷታል፤
የቦታው ስም በገዳሙ ስም ይጠራል

* ይህ ገዳምና አካባቢው የገባሬ ተአምራት ወመንክራት የአቡነ ዮሴፍ ዘኢንጂፋት የምናኔ ቦታ ነው፤
* አቡነ ዮሴፍ እንደ ሱራፊ በሰማይ ማዕጠንትን ያጠኑ፣ እመቤታችን ሥጦታን የሰጠቻቸው እና ዝንጀሮን እስከ ምጽአት ድረስ የገዘቱ በመሆናቸው በይበልጥ ይታወቃሉ፤
* ጻድቁ አቡነ ዮሴፍ ዝንጀሮ ሰብል እንዳይበላ የገዘቱበት ነው &ይገርማል ዛሬምጨድረስ ዝንጀሮ ስለተገዘተ ምንም ሰብል ሳይነካ የሚታይበት ነው፤ ሄዶ ማየትም ይቻላል!፨)
** ይህ ገዳም በኢትዮጵያ ከሚገኙ ጥንታውያንና ግንባር ቀደም የሱባዔ መያዣ ገዳማት ይመደባል (ብርዱንና ቅዝቃዜውን፤ ውርጩንና ቁሩን፤ ነፋሱን እና ሽውታውን ለቻለውና ላስቻለው!!)

በ2012 ዓ.ም. በዘመነ ኮሮና በዚህ የሱባዔ ገዳም የተፈጠረውን ነገር ልንተርክላችሁ ወደድን፤ ....

....... ከየት እንደመጡ፤ ትውልዳቸው፥ ቤተሰባቸው የሚገልጽ መረጃ የለም። ብቻ በእግራቸው በበርካታ ገዳማት እንደቆዩና በረከትን እንደሰበሰቡ በእግራቸው መዛል፥ በሰውነታቸው መድከም እና በያዙት ማስታወሻ ላይ የከተቡት ጽሑፍ ይመሠክራል።

ሁለቱም መነኰሳዪያት፤ ገና በወጣትነት ዕድሜ ያሉ፤ አንዷ 21 ዓመት፥ አንዷ የ25 ዓመት የእድሜ ክልል ላይ እንደሚገኙና መጠሪያ ስማቸው ወለተ ትንሣኤና ወለተ አረጋዊ እንደሆነ መታወቂያቸው ይመሰክራል።

ሚያዚያ 30 ቀን 2012 ዓ.ም. የአቡነ ዮሴፍ ዘላስታ (ዘኢንጂፋት) ፍልፍል የዋሻ ቤተ ክርስቲያንን ተሳልመው፤ በዚሁ ቀን ከሰዓት በኋላ ሱባዔ እንደሚይዙና ወደ ሌላ ቦታ እንደማይሄዱ፤ የጕዞ መጨረሻቸው እንደሆነ ከዋልዲቢት ገዳም ወደ ቅዱስ አቡነ ዮሴፍ ይዟቸው ለመጣው ዲያቆን "ከዚህ ገዳም ለቀን ወደ ሌላ ቦታ አንሄድም። ነገር ግን ደግመህ ወደ እዚህ ቦታ ስትመጣ አታገኘነም።" ብለውታል።

? ?

ወደ ገዳሙ በመጡ በነጋታው ግንቦት 1 ቀን 2012 ዓ.ም. በታላቁ የአቡነዮሴፍ ተራራ ወገብ ላይ ካሉት ቀደምት የመነኰሳት ዋሻ ውስጥ ሱባዔ ገቡ። አንድ ሱባዔ አለፈ ከበዓቱ አልወጡም፤
ሁለተኛውም ሱባዔ መጣ አለቀ፥ ከበዓቱ ግን አልወጡም፤ ሦስተኛ ሱባዔ ሞላ፤ 20 ቀናትም ሆነ፡፡

አንድ ሰው በጠዋት ፎቶ ግራፍ ሊያነሳ ወደ ተራራው ልቡን አነሳስቶት ወጣ። በድንገት 2ት መነኰሳትን ከሩቅ አየ፤ ጸሎት ላይ ይሆናሉ ብሎ ላለመረበሽ በቀስታና በዝግታ ወደ እነርሱ መቅረብ ጀመረ፤ ነገር ግን አይንቀሳቀሱም፡፡

በአግራሞት ወደ ዋሽው (በኣት) ሲቀርቀብ የማይንቀሳቀሱ መነኰሳት ሆነው አገኛቸው፤ ትንፋሽ የላቸውም፣ ሲነካቸው ሰውነታቸው ቀዝቅዟል፤ የደም ዝውውራቸው አቁሟል፡፡ ነገር ግን የአካላቸው ጅማት በተኣምር አልደረቀም ፤ ተገረመ።፥ ተደነቀ።፤ በፎቶ እስከዛሬ ሲያነሣቸው አስደናቂ ሁኔታዎች በላይ ነገሩ አስደመመው፤ ከተራራው ግርጌ ወደሚገኘው የአቡነ ዮሴፍ ካህናት ወርዶ ሁኔታውን አሳወቃቸው፤ እነርሱም በመደነቅ (መነኰሳቱ ካረፉ ብዙ ቀናት ቢያስቈጥሩም) ገነዟቸው።
ከዚህ ቀደም ያልታወቀ፣ ያልተለመደ፣ ያልተሸተተ አዲስ ነገር ዋሻቸውን ከሽቶ የበለጠ ልዩ መዐዛ አወደው፤ ከሰውነታቸውም ልዩ የሆነ መዐዛ ሸተተ።

/ጻድቃን፥ የዋሃን ሲያርፉ መላእክተ ብርሃን (እመቤታችን) ከገነት ልዩ መዐዛ ያለበትን አበባ አምጥተው ዕረፍቱ ለተቃረበው ለተመረጠ ሰው ያሸቱታል። በዚህ መሳጭ ፣ ጥዑም መዐዛም ነፍሱ ከሥጋው ትለያለች።
''በጺሐኪ ድንግል ጊዜ ዕረፍትየ፤
ጽጌ ዕፀ ገነት ገሪ ላዕሌየ፤
በመዐዛሁ ትትመሰጥ ነፍስየ፡፡''
እንዳለ አባ ጽጌ ድንግል በማኅሌተ ጽጌ፤ እንዲሁም መንገደ ሰማይ እና ራእየ ማርያም፡፡

2ቱ መነኰሳት፤ በወጣትነት ዕድሜያቸው፣ ሰው ከአውሬ በባስንበት፥ ከእንስሳ ባነሥንበት፤ በዘር ከረጢት በተቋጠርንበት፥ በአስተሳሰብ በላሸቅንበት በዚህ ዘመን፤
እነርሱ ግን በጸሎት ላይ እንዳሉ ፤ በጉልበታቸው እየሰገዱ እንደተበረከኩ ፣ ሁለት እጆቻቸውን ወደ ላይ እንደ ዘረጉ፣ ዓይኖቻቸው ወደ ሰማይ እንዳቀና የዚህን ዓለም አድካሚውን ኑሮ ተሰናብተው ወደ ላይኛው ዓለም ግንቦት 19 ቀን በአቡነ ዮሴፍ በዓለ ዕረፍት ክብረ በዓል ቀን በ2012 ዓ.ም. ተሰናበቱ።

ሻንጣቸው ተፈተሸ፡፡
የተለያየ የስንቅ ዓይነት የለም፣
ገንዘብ የለም፣
አልባሳትም የለም፡፡

** ነገር ግን ትንሽ ጥቂት ለሱባዔ ብቻ የሚሆን ሽንብራ አለ። (ከአበው እንደተማርነው ለቻለ ሱባዔ መግቢያ በቀን በ2ት እጅ እፍኝ ሽንብራ ነወ፡፡)
** ነገር ግን መንፈሳቸውን ለመመገብ አብዝተው በርካታ የጸሎት መጸሐፍት፣ በርካታ ገድላት፣ .... ይዘዋል። በአንዲት ብጫቂ ወረቀት ላይም፤ "መዝሙረ ዳዊቱን ከዚህ ቦታ ላመጣን ዲያቆን... ይሰጠው ተብሎ አድራሻ ተጽፏል፡፡"

በቅዱሱ ስፍራ በአቡነ ዮሴፍ ገዳም በታላቅ ክብርና በሊቃውንት ታጅበው ለአምላክ ብለው መከራ የተቀበሉለት በድነ ሥጋቸው በክብር አረፈ።

[[[የአሁኑ ኢትዮጵያውያን መልካሙን ታሪክ የመጻፍ ልምዳችንን ውሀ በልቶታል!!!!!]]]
Credit©ኢያሱ ዘአቡነ ዮሴፍ

/ኢትዮጵያውያን ቅዱሳን/ ገጽ
/Ethio Kidusan/ page

Photos from ገዳማትና አድባራት Monasteries and Churches's post 26/05/2024

ግንቦት ፲፱፤ በዓለ ዐቢየ እግዚእ፡፡
ወበዓለ አቡነ ዮሴፍ ዘላስታ ኢንጂፋት፡፡
ክብረ በዓላቸው የሚከበርባቸው ፯ ገዳማት እና አድባራት፡፡

Photos from ኢትዮጵያውያን ቅዱሳን Ethio Kidusan's post 17/05/2024

ግንቦት ፱
➻ እንደ አሮን፤ እንደ መልከ ጼዴቅ ንጹሕ ካህን የሆነ፤
➻ እንደ ኢዮብ መከራን የተቀበለ፤
➻ እንደ ጦቢያ አባት ጦቢት ምጽዋትን አድራጊ፤
➻ እንደ ኢሳይያስ ልዑለ ቃል የሆነ፤ እንደ ኤርምያስ አስተማሪ የሆነ፤
➻ እንደ ዘካርያስና ኦርያ ምርጥ ምስክር የሆነ፤
➻ እንደ ዮሐንስ ወንጌላዊ ምሥጢራትን ያያ፤
➻ እንደ ጴጥሮስ ቀኖናን አስተማሪ፤ እንደ ጳውሎስ አዲስ ትእዛዝን ሰባኪ፤
➻ እንደ ከፋሌ ባሕር ኤዎስጣቴዎስ ሕግን ጠባቂ፤
➻ እንደ ዮሐንስ አፈ ወርቅ የሚገሥፅ፤
➻ እንደ አቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ሃሌ ሉያ ተጋዳይ፤ የሆኑ አባት ናቸው፡፡

✧ ፤
፠ ከብዙ ዓመታት የብሕትውናና የማስተማር ኑሮ በኋላ ወደ ምድረ እገላ ሄዱ ደቀ መዛሙርቱ ግን ይህ ቦታ የሽፍቶችና የአጋንንት ሥፍራ ነው ከዚህ እንዴት እንቀመጣለን አሉት፤ አቡነ ብፁዕ አምላክ ግን እንደዚህ አትበሉ ብሎ በመገሰጽ ቦታውን በ4ቱም አቅጣጫ ባርኮ ማኅደረ ቅዱሳን አደረገው፤ ማኅበር አቋቁሞ በ1467 ዓ.ም. ገደመው፡፡
፠ ከጥቂት ዓመታት በኋላ ወደ ሚያርፉበት ገዳመ ደብረ ምዕዋን ሄደው እየተጋደሉ ሳሉ በ75 ዓመት ዕድሜያቸው፤ #በግንቦት 9 ቀን #በ1500 ዓ.ም. ቃል ኪዳንን ከእግዚአብሔር ተቀብሎ በክብር ዐረፈ፤ ደቀ መዛሙርቱም በደብረ ምዕዋንም በክብር ሥጋቸውን ቀበሩት፤ በመቃብራቸውም እስከ ዛሬ ድንቅ ድንቅ ተአምራት እየተደረገ ይገኛል፤ ድውያን ደግሞ በማይ ጠበሉ እየተጠመቁ እየተፈወሱ ይገኛሉ፡፡

✧ ፤
የገደሟቸው 2ት ገዳምት አሉ፡፡ እነርሱም፤
➵፩ኛ) ፤
ከዞባ በስተደቡብ፤ በዱባሩባ መንደር እንዲሁም ጽልማ ጥቁር ደንጊያ ጋራ የሚገኝ ሲሆን፤ ጻድቁ ለ30 ዓመት በጾምና በጸሎት የተጋደሉበትና ሥላሴ የተገለጹለት ቦታ በመሆኑ ተገደመ፡፡ ዓመታዊ በዓሉም በታኅሣሥ 1 እስከ አሁን እየተከበረ ይገኛል፡፡
➵፪ኛ) ፤
የሚገኘው በኤርትራ ሰራዬ አውራጃ ከድማ በስተደቡብ በደቀምሓረ ንኡስ ዞን ከተማ በስተደቡብ ምዕራብ አቅጣጫ ከዕዳጋ ማይ 20 ኪ.ሜ.፤ በ1970 ሜትር ከፍታ (ከባሕር ጠለል በላይ) ይገኛል፤ በዚህ ገዳም የብፁዕ አቡነ አምላክ ደቀ መዝሙርም የአቡነ በኵረ ድንግልም ቤተ ክርስቲያን አብሮ ይገኛል፤ ዓመታዊ ክብረ በዓሉም በግንቦት 9 ይከበራል፡፡፡፡

ወደሳሁ እንዘ ይብላ ለብፁዕ ሰርፀ ጽዮን፤
ደብረ ቢዘን ወደብረ ምዕዋን፤
መኑ ከማከ ዘነሠተ ዘነሠተ ዓረፍተ ደይን፡፡
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፥ እኛንም በጻድቁ አቡነ ብፁዐ አምላክ ጸሎትና ምልጃ ይማረን፥ የገዳመ ኰዳዱና ደብረ ምዕዋን ጸሎት ይርዳን አሜን፡፡
/ /

Photos from ኢትዮጵያውያን ቅዱሳን Ethio Kidusan's post 17/04/2024

ሚያዝያ ፱ (9)
፤ በዓለ ዕረፍታቸው፡፡
✧ ሲወለዱ እንደ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ እና አቡነ ተክለ ሃይማኖት ‹‹ስብሐት ለአብ፥ ስብሐት ለወልድ፥ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ›› ብለው ያመሰገኑ፤
✧ ፷ ዓመት ሙሉ አንዲት ልብስን ለብሰው ይኖሩ ከነበሩ ኪራኮስ ከሚባሉ መምህር የተማሩ፤ ኪራኮስም የእስንፋሰ ክርስቶስ ክብር ተገልጾላቸው ትንቢትን የተናገሩላቸው፤
✧ በዳውንት እግዚአብሔር አብ ዋሻ በጾም በጸሎት የኖሩ፤
✧ እንደ እነ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ከፋሌ ባሕር ሆነው በሐይቅ እስጢፋኖስ ባሕርን ያለ መርከብ የተሻገሩ፤
✧ እንደ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በባሕር ውስጥ ገብተው ለኢትዮጵያ ምሕረትን የለመኑ፤
✧ እንደ ኢያሱ ፀሐይን ያቆሙ፤
✧ እንደ ስማቸው ሀብተ ጣዕመ ምስጋና (የማመስገን ጸጋ) የተሰጣቸው፤ በዚህም ቅዱስ ዳዊት እየተገኘ በገናውን ይዞ መጥቶ የሚደረድርላቸው፤ እመቤታችን ከመላእክት ጋራ መጥታ የምትባርካቸው፤
✧ ገዳማተ ኢትዮጵያን፣ አድባራተ ግብጽን፣ ሀገረ ኢየሩሳሌምን መልአኩ በክንፉ ይዞ ያሳያቸው፤
✧ ዐሥራ ሦስቱን ሕማማተ መስቀል በማሰብ እንባቸውን እያፈሰሱ ጀርባቸውን በጅራፍ እየገረፉ፤ በደንጊያም ደረታቸውን ዐሥራ ሦስት ጊዜ እየመቱ የጌታን ሕማም የሚያስቡ፤
✧ ሀብተ ፈውስ እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ተሰጥቷቸው ዕውራንን እያበሩ፣ አንካሶችን እያረቱ፣ ደዉያንን እየፈወሱ፣ አጋንንትን እያወጡ፣ ሙታንን እያስነሡ የኖሩ፡፡
✧ ለዐሥረኛው መአርግ ለከዊነ እሳት በመድረሳቸው ለጸሎት እጃቸውን በሚዘረጉበት ጊዜ ዐሥሩ ጣቶቻቸው ኹሉ እንደ መብራት ያበራ የነበረ፤ እንደ እነ ኢሳይያስም እስከ መንበረ ጸባኦት ድረስ ተገልጦላቸው ይመለከቱ የነበረ፤
✧ የኢትዮጵያ ሰዎች ሁሉ እየሄዱ በረከትን እንዲቀበሉ የዐፄ ፋሲለደስ ልጅ ዐፄ ዮሐንስ በማስደረጉ፤ ቦታው ‹‹ደብረ አስጋጅ›› የተባለላቸው፤
✧ መካን የሆኑ በስማቸው ቢማጸኑ ልጅ እንደሚሰጥ ጌታችን ቃል የገባላቸው ናቸው፡፡

ለብዉ! ሚያዝያ 9 ብዙ ጊዜ ዐቢይ ጾም ላይ ስለሚውል ሐምሌ 9 በልዋጭ በዓለ ዕረፍታቸው ይከበራል፡፡

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ እኛንም በጻድቁ በአቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ አማላጅነት ይለመነን፤ በረከት ረድኤት ይከፈለን፤ ይፈውሰን፥ ይባርከን፤ በጸሎቱም ይማረን፤ አሜን፡፡
/ /

Photos from ኢትዮጵያውያን ቅዱሳን Ethio Kidusan's post 26/03/2024

መጋቢት ፲፯ (17)
( ) ዕረፍቱ፡፡
✧ ከሕቱም መቃብራቸው ላይ ዛሬም ድረስ ዘይተ ሰሊሆም የሚያፈልቁ፤ ይህንንም በተመለከተ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በመጽሐፈ ሰዐታት ላይ በግጥም
(ዮናስ አቡነ ማኅቶተ ገዳም፤
ዘታፈለፍል ዘይተ ሰሊሆም፤
እምከርሠ መቃብር ሕቱም፡፡) ብሎ የደረሰላቸው፤
✧ በሕፃንነታቸው በጎች እየጠበቁ ሳለ እንደ ቅዱስ ዳዊት መንፈስ ቅዱስ ያደረባቸው፤
✧ ፭ ፍሬ ‹‹ዳዕሮ›› ይመገቡ የነበረ፤ በዚህም መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ኀብስተ አኰቴትን፥ ጽዋዕ በረከትን ከሰማይ ያወረደላቸው፡፡
✧ ባሕር(ሐይቅ) ውስጥ ገብተው ሲጸልይ 10ሩም የእጃቸው ጣት እንደ ፋና ፥ እንደ ፋኖስ መብራት የሚያበራላቸው፤
✧ በቊርባን ጊዜ ወደ ኢየሩሳሌም በሠረገላ መንፈስ ደርሰው አስቀድሰው፤ ዕለቱን በሠረገላው ከገዳማታቸው አንዱ ወደሆነው ደብረ ጽጌ ተመልሰው ገብተው መክፈልት የሚቀምሱ፡፡
✧ ይይዙት የነበረው ‹‹አንብዕ መስቀል›› የተባለና ያነባ የነበረ መቋሚያቸው በውኃ እየታጠበ ውኃው በጣም ለታመሙ ሰዎች እየተሰጠ በቶሎ ከበሽታቸው ይድኑበታል፣ የማይድኑም ከሆነ ቶሎ በሞት ያርፋሉ፡፡
✧ በዓለ ዕረፍታቸው መጋቢት ፲፯ ሲሆን በዐቢይ ጾም ምክንያት ወደ ጥር ፳፩ ቀን ተዛውሮ በሁሉም ገዳማቸው ውስጥ በታላቅ ክብረ በዓል ይከበራል፡፡

✧ ፡፡
ጻድቁ በስማቸው ፭ት የተገደሙ ገዳማት አሏቸው፡፡ እነርሱም፤
ሀ. ደብረ ድኁኃን ቆሓይን፣ (ዐፅማቸው ያረፈበት)
ሁ. ደብረ ጽጌ ትምዛእ፣ (ኤርትራ ሠራዬ መንደፈራ ተከላ)፤ ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ትልቅ ርስት የሰጡት፡፡ (ዘይት የሚፈልቅበት)
ሂ. ደብረ ጽዮን ዓዲ ውስኽ፣
ሃ. ደብረ ጸሪቅ ትግራይ ተምቤን፣
ሄ. ሙራደ ቃል ደብረ ሣህል ዓረዛ ይባላሉ፡፡ (ይጸልዩበት የነበረው ዋሻና የእግራቸው አሻራ እንዲሁም ዘይት የሚፈልቅበት)

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ እኛንም በጻድቁ በአቡነ ዮናስ ፈውሰ በረከት ይፈውሰን፥ ይባርከን፤ በጸሎቱም ይማረን፤ አሜን፡፡
/ /

Photos from ኢትዮጵያውያን ቅዱሳን Ethio Kidusan's post 18/03/2024

መጋቢት ፲
( #በኪሞስ) ( #ድማኅ)
✧ #ልደትና ✧
አቡነ ተከሥተ ብርሃን ሰሜን ሸዋ መንዝ ከአባታቸው መልከ ጼዴቅና ከእናታቸው ድል በኢየሱስ ተወለዱ፤ የመጀመሪያ ስማቸውም በኪሞስ ይባል ነበር፡፡ ኋላ እንደ አቡነ ሰላማ ‹‹ከሣቴ ብርሃን›. እንደተባሉት በኪሞስም ለመላ ጎጃምና ኢትዮጵያ በወንጌል ትምህርት ብርሃንን ከሥቷልና እስከ ማታ ድረሰም 9999 ሰዎችን አጥምቋልና ‹‹ተከሥተ ብርሃን›› ተባለ፡፡
አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከወለዷቸው በርካታ ዐበይ ቅዱሳን መካከል፤ አቡነ ፊልጶስና አቡነ አኖሬዎስ ይገኙበታል፤ አቡነ አኖሬዎስ ተከሥተ ብርሃን የተባለ በኪሞስን ወለደ፤
✧ ፤
ዐፄ ዐምደ ጽዮን ብዙ ውጊያዎችን ከአረማውያን ጋር በማድረጉ፤ ከእነርሱ የተማራቸው ብዙ ባህሎች ነበሩት፤ በዚህም ምክንያት የእንጀራ እናቱን እስከ ማግባት ደረሰ፡፡
በዚህን ጊዜም ዮሐንስ መጥምቅ ሔሮድስን እንደተቃወመው፤ በአባታችን በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ወንበር ተቀምጦ (3ኛ ዕጨጌ) የነበረው አቡነ ፊልጶስም ፊት ለፊት ንጉሡን ሳይፈራና ሳያፍር ተቃወመው፡፡ ንጉሡም ከስህተቱ ከመመለስ ይልቅ ዕጨጌ አቡነ ፊልጶስን ‹‹ወንጂ›› በተባለ ከተማቸው ደሙ እስኪወርድ ድረስ አስደብድቦ ወደ ትግራይ አጋዘው (አሰደደው)፤ ከአቡነ ፊልጶስ ጋርም ተባብራችኋል ተብለው እነ አቡነ ተከሥተ ብርሃንም ተጋዙ፡
በስደትም እያሉ ዕጨጌ ፊልጶስ የአቡነ ተከሥተ ብርሃንን ዕጣ ክፍላቸው ምድረ ጎጃም እንደሆነች አውቆ፤ ‹‹ሐዲስ ሐዋርያ ቀዳማዊ መምህረ ጎጃም›› ብሎ ሾማቸው፤ አቡነ ተከሥተ ብርሃንም ‹‹ደብረ ዕንቊ›› (ደቡብ ጎንደር የምትገኝ) ላይ ሱባዔ በመግባት፤ በቦታው ላይ የመምህራቸውን የእጅ መስቀል ለምልክት አስቀምጠው፤ በሞጣ አድርገው ወደ ዲማ በ1297 ዓ.ም. በዐፄ ዐምደ ጽዮን ዘመነ መንግሥት(1380-1412ዓ.ም.) መጥተዋል፡፡
ዲማ (ደመወ ቀይ ማለት ነው) ቀይ አፈር፣ የሚያብለጨልጭና ትልቅ ዲማ የሚባል ቀይ ዛፍ የሚኖርበት ሲሆን፤ በገዳም መልክና ሥርዐት ይዞ፥ ከቆላው ወደ ደጋው ወጥቶ፥ ስሙ ዲማ ጊዮርጊስ (ደብረ ድማኅ /መሃል ራስ/) ተብሎ የተገደመው ግን በዐፄ ይስሐቅ ዘመነ መንግሥት (1413-1430 ዓ.ም.) ነው፡፡
ከደብረ ዕንቊም አሁን ዲማ ገዳም ካለበት በስተሰሜን ‹‹ማርያም ጉብታ›› ተብሎ በሚጠራው ቦታ ላይ ትልቅ ዋሻ አገኘ፡፡ ይጸልይባት የነበረችውን ታቦተ ማርያምንና ንዋየ ቅድሳትን በዋሻው አስቀምጦ በግማሹ የሰሌን መጋረጃ ጋርዶ ‹‹ቀዳሚት ማርያም››ን (ዲማ ምርያምን) መሠረተ፡፡ ከመንፈሳውያን ልጆቹ ጋር እየኖረ፤ በጎጃም አውራጃ ሁሉ እየወጣ እየወረደ፥ እየተዘዋወረ አስተማረ፡፡ ከዕለታት በአንድ ቀንም እነሴና እነብሴ በሚገኘው ነድ አጹራ ማርያም በሚባለው ቦታ ሲያስተምር 9999 ሰዎችን እያጠመቁ ቀኑ መሽቶ ስለነበረ ‹‹ተከሥተ ብርሃን›› የሚል ስም ተሰጠው፡፡
ለ2ኛ ጊዜም ዐፄ ሰይፈ አርዕድ ስላሳደደው፤ ደብረ ግሸና (ደቡብ ጎንደር በጌምድር ) ተቀምጦ አስተማረ፡፡ ከዚያም ተመልሶ በቅዱስ ሚካኤል ስም ቤ/ንን ተክሎ 9 ዓመት አስተምሯል፡፡ በተለያዩ ቦታዎችም እየተዘዋወረ አቀዋርጦት የነበረውን ሐዋርያዊ ሥራውን በመቀጠል ምዕመናን በማጥመቅ እንደ ጮለሚት ማርያም (ብቸና አካባቢ) መሥርተዋል፡፡ በአዴት፣ በሳርካ፣ በአመዳሚት (ወሰን አምባ) እየተዘዋወሩም ሌሎች አብያተ ክርስቲያናትን እያነጹ ብዙ ሕዝብ አስተምረዋል፡፡

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፥ እኛንም በጻድቁ አቡነ ተከሥተ ብርሃን ጸሎትና ምልጃ ይማረን፡፡
/ /

Photos from ኢትዮጵያውያን ቅዱሳን Ethio Kidusan's post 13/03/2024

ጥቅምት ፭
፡፡ ( #አቦ፥ #አቡዬ) ( ) ፤
(ስዕሉ ላይ የምታዩት ገደል፤ አቡዬ የሰነጠቁት ገደል ነው፤ ስሙም ‹‹ ›› ይባላል፡፡

፠፠፨፠፠ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፤
➻ እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ብርሃነ ዓለም የኾኑ፤
➻ እንደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ጸጋንና ክብርን የተሞሉ፤
➻ ኰከበ ገዳም፥ መናኔ ዓለም፥ ምድራዊ መልአክ፤
➻ ስማቸውን ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ያወጣላቸው፤
➻ በአክናፈ መባርቅት ተጭነው የሚጓዙ፤
➻ 60 አናብስትና፥ 60 አናምርት ይታዘዙላቸው የነበሩ፤ የእግራቸው ትቢያ ለአራዊቶቹ ምግብ የኾነላቸው፤
➻ ለብዙ አእላፍ ቅዱሳን ወላዴ የኾኑና በረከትን የሰጡ ታላቅ አባት፤ (ለአብነትም፤ ለቅዱስ ላሊበላ፥ ለአቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ፥ ለአባ አንበስ ዘደብረ ሐዘሎ፥ ለአባ ብንያም ዘግብፅ)
➻ የምድራችን ሐዋርያ፥ ሐራሴ ወንጌል፥ ሰዳዴ አጋንንት አባ ገብረ ሕይወት፡፡
➻ ይህን ዓለም ንቀው፤ በጸሎት ተግተው፤ በተጋድሎ ጸንተው፤ በቅድስና አሸብርቀው፤ በእግዚአብሔር ክብር ደምቀው መጋቢት 5 በምድረ ከብድ አርፈዋል፡፡ ነገር ግን ወቅቱ ዐቢይ ጾም ላይ ስለሚውል የልዋጭ (ምትክ) በዓሉ ጥቅምት 5 ይከበራል፡፡

✧ ፤ ፠፨፠ አረ እንዴት ነው አቡዬ፤ አረ እንዴት ነው ጻድቁ፡፡ (፪)

ተራራ(ገደል) እንደ አክርማ፥ የሚሰነጥቁ፤
አረ እንዴት ነው አቡዬ፥ አረ እንዴት ነው ጻድቁ፡፡
የሌጌዎን ጭፍሮች(ሠራዊት)፥ በስምህ አለቁ፤
አረ እንዴት ነው አቡዬ፥ አረ እንዴት ነው ጻድቁ፡፡
በጾም፥ በጸሎትህ፥ በመብረቅ ወደቁ፤
አረ እንዴት ነው አቡዬ፥ አረ እንዴት ነው ጻድቁ፡፡

ገድሉ አንፀባራቂ፥ ተአምሩ የገነነ፤
አረ እንዴት ነው አቡዬ፥ አረ እንዴት ነው ጻድቁ፡፡
በረከት ያገኛል(ስዕለትን ይሰማል)፥ ኪዳኑን ያመነ፤
አረ እንዴት ነው አቡዬ፥ አረ እንዴት ነው ጻድቁ፡፡

እናቱ አቅሌስያ፥ አባቱ ስምዖን፤
አረ እንዴት ነው አቡዬ፥ አረ እንዴት ነው ጻድቁ፡፡
ምግቡ ምስጋና ነው፥ ተሰጥቶታል ኪዳን፤
አረ እንዴት ነው አቡዬ፥ አረ እንዴት ነው ጻድቁ፡፡

ስእለትን ይሰማል፥ ጸበሉ ፈዋሽ ነው፤
አረ እንዴት ነው አቡዬ፥ አረ እንዴት ነው ጻድቁ፡፡
ገብረ መንፈስ ቅዱስ (የዝቋላው አቦ)፥ ለጠሩት አባት ነው፤
አረ እንዴት ነው አቡዬ፥ አረ እንዴት ነው ጻድቁ፡፡

አቡዬን(ጻድቁን) ጥሩልኝ፥ እኛን ባለ ጭራ፤
አረ እንዴት ነው አቡዬ፥ አረ እንዴት ነው ጻድቁ፡፡
ያወጡ የለም ወይ፥ ከሲኦል መከራ፤
አረ እንዴት ነው አቡዬ፥ አረ እንዴት ነው ጻድቁ፡፡

ገብረ መንፈስ ቅዱስ የዳንኤል ልጁ፤
አረ እንዴት ነው አቡዬ፥ አረ እንዴት ነው ጻድቁ፡፡
አንበሳን እንደ ድመት የዳሰሰ በእጁ፡፡
አረ እንዴት ነው አቡዬ፥ አረ እንዴት ነው ጻድቁ፡፡

ገብረ መንፈስ ቅዱስ(አቡዬ አባታችን)፥ እንደኛ ሰው ናቸው፤
አረ እንዴት ነው አቡዬ፥ አረ እንዴት ነው ጻድቁ፡፡
መስቀል ከሰማይ ላይ፥ የወረደላቸው፤
አረ እንዴት ነው አቡዬ፥ አረ እንዴት ነው ጻድቁ፡፡
ጸበል ከጭንጫ ላይ፥ የፈለቀላቸው፤
አረ እንዴት ነው አቡዬ፥ አረ እንዴት ነው ጻድቁ፡፡
መብረቅ እንደ ንስር፥ የሚያጓጉዛቸው፤
አረ እንዴት ነው አቡዬ፥ አረ እንዴት ነው ጻድቁ፡፡

አንበሳና ነብር፥ የታዘዙላቸው(የሰገደላቸው)፤
አረ እንዴት ነው አቡዬ፥ አረ እንዴት ነው ጻድቁ፡፡
ለዝቋላው አቦ (ለምድረ ከብዱ፥ ለገዛዛው) (ለጻድቁ አቡዬ)፥ እልል በሉላቸው፤
አረ እንዴት ነው አቡዬ፥ አረ እንዴት ነው ጻድቁ፡፡

፠፨፠ ወተቀበልዎ መላእክት፥ በስብሐት ወበማኅሌት፤
ወአብዕዎ ኢየሩሳሌም ሰማያዊተ አብዕዎ ገብረ ሕይወት፡፡

ለእግዚአብሔር ክብር፥ ምስጋና ይሁን፤ እኛንም በጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ምልጃ ይማረን፥ ይቅር ይበለን፤ አሜን፡፡
/ /

Photos from ኢትዮጵያውያን ቅዱሳን Ethio Kidusan's post 11/03/2024


¤ ጽዮንና በጣም የሚወዱ፤ ከዚህም የተነሣ ሲጠሩ ‹‹ ›› ተብለው የሚጠሩ፡፡
¤ በጉንደትና ጉራዓ ጦርነት ግብጽን ድባቅ የመቱ፤
¤ ዋልድባ ገዳምን በጣም የሚያከብሩ፤ ከማክበራቸውም የተነሣ በግብር ጊዜ የዋልድባን መምህር ከሁሉም ገዳማት በላይ ከፍ ባለ ወንበር ያስቀምጡ የነበሩ፤ በቦታ ስፋት በኢትዮጵያ ትልቁ የሆነውን ዋልድባ ገዳም በአጥር ሊያጥሩ ሥራ በጀመሩ ጊዜ የገዳሙ አበው ገዳሙ በ4ቱም አቅጣጭ ወንዞች አጥር እንደሆኑት ይቀጥል ያሉት፡፡
¤ የሃገራችንን ታላቅነት ለመመለስ፤ አንድነቷን ለማጽናት በበዙ የተጉ፤
¤ የተዘረፉ መዛግብትን ለማስመለስ የደከሙ፤
¤ የኢትዮጵያን ዳር ድንበር ደፍሮ ጎንደር ድረስ የመጣውን ድርቡሽ አባርረው፤ መተማ ላይ ለሃገራቸው ሲሉ የተሰዉ፤ በዚህም ቦታው መተማ ዮሐንስ እየተባለ የሚጠራላቸው፡፡

ከተናገሯቸው ዘሠፈመን አይሽሬ ንግግሮች መሃል፤
** "....በዓይነ ኅሊናዬ እንደ ዳዊት እያገላበጥሁ የምደግማትን አገሬን ኢትዮጵያን ሲነኩብኝ ደሜ ይፈላል፤
የሚገዙትን መሬት ብቻ ኢትዮጵያ ብለዉ የሚጠሩ የአገሬ መኳንንት ከዚህ ጠባብ ሓሳባቸው ወጥተው አንዲት ታላቅ ኢትዮጵያ እንዳለች ሊያውቁ ይገባል፡፡
ጠላትን በሩቁ የምንመለከተው መሬት ስለሚቀማን ብቻ አይደለም፤ ይልቁኑ በአገሬ እምነት፣ ወግ እና ባህል ላይ ሌላ ዲቃላ የሆነ መጤ ባህል እንዳይፈጠር ጭምር በመስጋት ነው ...." ዐፄ ዮሐንስ አራተኛ

** "ኢትዮጵያ የተባለችው አንደኛ እናትህ ናት! ሁለተኛ ዘውድህ ናት! ሦስተኛ ሚስትህ ናት! አራተኛ ልጅህ ናት! አምስተኛ መቃብርህ ናት!፡፡ እንግዲህ የእናት ፍቅር፣ የዘውድ ክብር፣ የሚስት ደግነት፣ የልጅ ደስታ፣ የመቃብር ከባቴነት እንደዚህ መሆኑን አውቀኸው ተነሳ!”


ራሳቸውን አንሳር(አሸናፊዎች) በሚሉና የሱፊ እስልምና ተከታይ በሆኑት የሱዳን መሐዲስት ደርቡሾች በተደጋጋሚ 3ት ጊዜ የማኅበረ ሥላሴን ገዳም ጥፋትን አደረሱበት፤
* ከ1659-1674ዓ.ም. የመጀመሪያው ጥፋት፤
* በዐፄ ቴዎድሮስና በዐፄ ዮሐንስና ዘመን /በጥር 27 ቀን 1877ዓ.ም. የጎንደርና የደምቢያውን ሀገረ ገዢ ዳኅና ፈንታን ገደሉ ገዳሙን አቃጠሉ፥ መነኰሳቱን ፈጁ/
* በ1880 ዓ.ም. ጎንደር አካባቢ ያሉትን አብያተ ክርስቲያናት አቃጠሉ
* ጥር 10 1880 ዓ.ም. ከንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ጋር ተዋጉ፤ ልጃቸው ምንትዋብ ተማረከች አልሰልምም ብላ በረሃብ ሞተች፤ ባለቤቷ ደጃች ጀምበሬ ሞቱ፡፡
* ነሐሴ 23 1880 ዓ.ም. ጎንደር ገብተው ከ44ቱ ደብራት 40ውን አቃጠሉ፤
* መስከረም 25 1881 ዓ.ም. ጎንደርን አቃጠሉ፤ ቀሪዎቹን 3ት ደብራት ሠለስቱ ምዕትን ግምጃ ቤት ማርያምን አቃጠሉ፤ የግምጃ ቤት 9ኝ የመጻሕፍት መምህራንን (ዛሬ የምንገለገልበትን አንድምታ ከመምህር ኤስድሮስ በኋላ ያቀኑትን እነ መምህር ወልደ ሚካኤልን) በቤተክርስቲያኑ መውጫ በርላይ ከነተማሪዎቻቸው ሰየፏቸው፡፡ ጩጊ ማርያምንም አቃጠሉ፡፡ ….. ዐፄ ዮሐንስ እየመጡ መኾኑን ሲሰሙ ወደ መተማ ሸሹ፡፡
ዐፄ ዮሐንስ ወደ ማኅበረ ሥላሴ በመግባት ገዳማውያኑን በማጽናናት፤ የብራና ተአምረ ማርያምና ሌላም መብዓ በመስጠት በየካቲት 27/1881 ዓ.ም ወደ መተማ ወርደው ተዋጉ፤ በውጊያው ግን ንጉሣችን ተመትተው ቆሰሉ፤ ጦሩም ንጉሡን ይዞ ወደ ማጠቢያ (ጻድቁ ዐምደ ሥላሴ ልብስ ያጠቡበት በመሆኑ ይህን ስም አግኝቷል) ሸሸ፤ ጠላት ኃይሉን አጠናክሮ በመጋቢት 2(3)/1881ዓ.ም. ደርሶ ንጉሣችንን ገደለ፤ ንጉሣችንን አናስነካም ያሉ በርካታ ካህናትና ምዕመናንም እንዲሁም የማኅበረ ሥላሴ መነኰሳት በሰማዕትነት አለፉ፤ የንጉሡንም ራስ ከአንገት ላይ ቈርጠው ወሰዱ፡፡

ከተገጠመላቸው የኀዘን እንጉርጉሮ መካከልም፤
ዓፄ ዮሐንስ ሞኝ ናቸው፤
እኛም ሁላችን ናቅናቸው፡፡
ንጉሥ ቢሏቸው በመኃሉ፤
ወሰን ጠባቂ ልሁን አሉ፡፡

በደምቢያ መታረድ አዝኖ ዮሐንስ፤
ደሙን አፈሰሰ እንደ ክርስቶስ፡፡

እንዳያምረው ብሎ ደሃ ወዳጁን፤
መተማ አፈሰሰው ዮሐንስ ጠጁን፡፡

የጎንደር ሃይማኖት ቆማ ስታለቅስ፤
አንገቱን ሰጠላት ዳግማይ ዮሐንስ።

እጅግ ደስ ይለኛል ያንተ ስም ሲነሳ፤
የቁና ዓፈር ንፉግ አንተ ነህ ወይ ካሳ።

ዓፄ ዮሐንስ ይዋሻሉ፤
መጠጥ አልጠጣም እያሉ፤
ሲጠጡ አይተናል በርግጥ፤
ራስ የሚያዞር መጠጥ፡፡
/© /

Photos from ኢትዮጵያውያን ቅዱሳን Ethio Kidusan's post 06/03/2024

የካቲት 27 ፤ ታላቁ ገዳም፡፡
፥ ፥ ፡፡
(ብዙዎች ግን የማያውቁት)፡፡

፠ የጌታችን ልደት በዕለቱ በሃገራችን ኢትዮጵያ በቶራ አማካይነት ለአንድ ባሕታዊ የተገለጠበት፤
፠ የበረሃው ውዕየትና ግለት የሚያይልበት፤ (ከእሳቱ ግለት የተነሣ ድንጋዩ ተልባ ያስቆላላ የተባለለት)
፠ አቡነ ዐምደ ሥላሴና ሌሎችም ቅዱሳን (እነ አቡነ ክፍለ ማርያም፥ አቡነ ገብረ ክርስቶስ ዘቋራ፥ ፯ቱ ዘሥላሴ በመባል የተጠሩ ቅዱሳን፣ አርከ ሥሉስ /የአርኬና የመልክአ ቊርባን ደራሲ/፥ …) የተጋደሉበት፤
፠ የበቁ ባሕታውያንና ግሑሳን የሚኖሩበት፤
፠ እንኳን ሰዉ ከብቱ ሥርዐት ወደሚጠቅበት፤ (ከብቶቹ ‹‹አጎዶ (ወገን ወገን) ሲባከሉ በጾታ ተለይተው የሚያድሩበት)
፠ ብዙ ከብቶች ገዳሙ እያለው ሥጋ የማይበላበት፤
፠ የላመ የጣመ፥ የጣፈጠ የማይበላበት፤ የሞቀ፥ የደመቀ፥ የተዋበ የማይለበስበት፤
፠ ከዓመት እስከ ዓመት አንድ ዓይነት ምግብ (መኰሪታ) የሚበላበት፤
፠ ታላላቅ ነገሥታት የነገሡበት፤
(አብርሃ ወአጽብሃ ዳሩ እሳት መሐሉ ገነት ይሁን ብለው የገደሙት፤
አፄ ቴዎድሮስ የተማሩበትና ኋላም የተቀበሩበት፤
አፄ ዮሐንስ ለሃገራቸው ሲሉ መተማ ሄደው ከማረፋቸው በፊት መጥተው የተሣለሙት፤
ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ብዙ ንዋያት ወደ ሰጡት፤
፠ የበቁ አባቶች ወደሚኖሩበት፤ (ከብቃታቸው የተነሣ ጣሊያን የገዳሙን የውኃ ገንዳ በአውሮፕላን በቦንብ ብታጋየውም፤ ወዲያው አውሮፕላኗን በጸሎት እዚያው በረሃ ላይ በጸሎት ዶግ አመድ አድርገው የከሰከሱበት)
፠ የምዕራብ ጎንደርን መልክአ ምድር በማየት አእምሮውን የሚያድሱበት፤
፠ በየቀኑም በቅዳሴያችን ይህን ታላቅ ገዳም እንዲህ እያልን እናነሳዋለን፥ እናወድሰዋልን፤
‹‹ሰላም ለክሙ ጻድቃነ ዛቲ ዕለት ኵልክሙ፤
ዕድ ወአንስት በበአስማቲክሙ፡፡
ቅዱሳነ ሰማይ ወምድር አንትሙ፤
ዝክሩነ በጸሎትክሙ በእንተ ማርያም እሙ፤
ተማኅጸነ ለክርስቶስ ሥጋሁ ወደሙ፡፡
፠ በየካቲት 27 ፣ በጥር 7ና ሐምሌ 7 ካልሆነ ወደ ማኅበረ ሥላሴ ገዳም ለመግባት ከግዝት በር ላይ 7ት ቀናት የሚጠበቅበት፤
፠ የካቲት 27ም ጽድቃቸውና ቃልኪዳናቸው እንደ ምድር አሸዋ የበዛው፥ እንደ ሰማይ ከዋክብት ለመቊጠር የሚያስቸግረው የጻድቁ ዐምደ ሥላሴ ዘማኅበረ ሥላሴ ልደታቸውም እረፍታቸው የሚከበርበት ነው፡፡
 ብፁዕ አባ አቡነ ዐምደ ሥላሴ ንብረቱ ገዳም ውስተ ሀቌሁ ቅንአቱ ዘአዲም፤
ያስተጋብእ ጽድቀ ዘእምኵሎሙ ቅዱሳን በጾም ወበጸሎት፤
ሀለወ በክብር ወበሰላም፡፡ /መሐረነ አብ/
/ምንጭ፤ ዋልድባ ዋሊ/
ለእግዚአብሔር ክብር፥ ምስጋና ይሁን፤ እኛንም በጻድቁ ዐምደ ሥላሴ ምልጃ ይማረን፥ ይቅር ይበለን፤ ከማኅበረ ሥላሴ ገዳም ረድኤት በረከት፤ ከአበው አንድነት፤ ከሥላሴ ልጅነት አያናውጸን፨
/ /

Photos from ኢትዮጵያውያን ቅዱሳን Ethio Kidusan's post 23/02/2024

#የካቲት #፲፮
( #ሀርቤ) (የቅዱስ ላሊበላ ወንድም) /ከ1124 -1157 ዓ.ም./፡፡
✧ ፡፡
✧ የካቲት 16 ልደቱ፥ ክህነትን የተቀበለበትና የነገሠበት፥ ያረፈበት ዕለት ነው፡፡
✧ የፋርስና የባቢሎን ነገሥታት ግብጽንና የግብጽን ገዳማት በመውረራቸው ዘምቶ አሳፍሮ፤ የወሰዱትን ንብረት አስመልሶ፥ ያፈረሱትን አሰርቶ፥ የግብጽ ክርስቲያኖችና ሰዎች በሰላም እንዲኖሩ ያደረገ፡፡
✧ ግብጽ ዘምቶ ሲመለስ ግብፅ ላይ እንዳለ 7 ቀናት ሙሉ ሳያቋርጥ ዝናብ ዘነቦላቸው የዘሩትን አዝመራ ለ7ት ዓመታት ያህል ቀለብ የኾነላቸው፡፡
✧ በጀግንነቱና በቅድስናው የግብፅ ጳጳሳት መሪዎች ሸልመው የአርበኞች አርበኛ ነህ ሲሉ #ያርብሃዊ ብለው ስም ያወጡለት፤
✧ የዐባይን ወንዝ የገደበ፡፡
/ /

Photos from ኢትዮጵያውያን ቅዱሳን Ethio Kidusan's post 11/08/2023

ነሐሴ ፭ (5)
( ) #ዕረፍታቸው፤
➻ የታላቁ ገዳም ደብረ ቢዘን ዕንቊ፤
➻ ውኃን እንደ ሣር ነገሥታቱ ሳይቀር እስኪደነቁ በተአምራት ያቃጠለ፤ ይህንንም በተመለከተ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በመጽሐፈ ሰዓታቱ ላይ፤
‹‹ፊልጶስ አቡነ ገባሬ መንክር፤
ዘአንደድከ ማየ ከመ ሣዕር፤
እስከ ያነክሩ ነገሥታተ ምድር፡፡›› ብሎ ያመሰገነው፡፡
➻ ስለ ቀዳሚት ሰንበት ምስክርና ሰማዕት የሆኑ፤
➻ በአውራሪስ ላይ ይጫን የነበረ፤ አጋዘን የሰገደለት፤ 2ት ዝሆኖች የተሸከሙት፤ አንበሳ ጉድጓድ የቆፈረለት፤ በጥላው ሕሙማንን ያስነሰ፤ ተማሪውን ከሞት ያስነሣ፤ ገባሬ ተአምራት ወመንክራት የሆነ፤
➻ ገዳማትን ያቀኑ፤ መነኰሳትን የሰበሰቡ፤ በማስተማርና በተጋድሎ የጸኑ፤
➻ ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን የሆኑ (የታወቁና በስማቸው ገድል ተጽፎላቸው፥ ቤተ መቅደስ የታነጸላቸው የ16 ታላላቅ ቅዱሳን አባት)፡፡
☨ አቡነ ዮሐንስንም እጁን ጭኖ ባረከው፤ ደቀ መዛሙርቱም እንዲታዘዙት ነገራቸው፡፡ ክብርት ነፍሱ ከሥጋው ተለየች፤ ነፍሱንም ከልጅነት ጀምሮ የሚራዳው መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ወደ ገነት አሳረገው፤
/ /
✧ ፤
ታላቁ ገዳማቸው ደብረ ቢዘን ሲባል፤ በኤርትራ፥ በሐማሴን አውራጃ፥ ከአስመራ ከተማ በስተምሥራቅ 25 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ ይህ ገዳምም በኢትዮጵያ (ኤርትራ ሀገር ሳትሆን በፊት) ከሚታወቁ ዐበይት ገዳማት አንዱ ሲሆን፤ ኢትዮጵያ የራሷ ዘመን አቈጣጠር እንዳለት ማስረጃ ከሆኑት ውስጥ አንዱ ‹‹ሐሳበ ደብረ ቢዘን›› ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ‹‹ሐሳበ ጕንዳጕንዶ›› ነው፡፡

✧ ፤
ሰላም ለፊልጶስ እንተ ክህለ ያዕዱ፤
ለዘጸውዖ ብእሲ ለውኂዘ ክረምት እምነ ሞገዱ፡፡
ወእምኔሁ አብ እለ በመንፈስ ተወልዱ፤
እንዘ ይዜንዉ ኃይሎ ወምግባረ ጽድቁ ይንዕዱ፤
ስሙዓቲሁ ወጽአ ለዓለም በዐውዱ፡፡

ለእግዚአብሔር ክብር ይሁን፤ እኛንም በጻድቁ በአቡነ ፊልጶስ ጸሎትና ምልጃ ይማረን፥ ይቅር በለን፤ ገዳሙ ደብረ ቢዘንንም በረድኤት በቸርነት ይጎብኝልን፤ አሜን፡፡
/ /

Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Category

Website

Address


Addis Ababa