21/05/2026
በ16ኛው የቴክኖሎጂ ሳምንት ላቅ ያለ ውጤት ላስመዘገቡ አካላት የምስክር ወረቀት ተበረከተ
አዲስ አበባ —
ግንቦት 2018 ዓ.ም
በ2018 በጀት ዓመት በከተማ አቀፍ በተካሄደው 16ኛው የቴክኖሎጂ ሳምንት ላይ ማዕከሉን ወክለው ተሳትፎ ለነበራቸውና ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላሳዩ የማዕከሉ አሰልጣኞች የዕውቅና እና የምስጋና ወረቀት የመበርከት ሥነ-ሥርዓት ተካሄደ።
በዕለቱ በተከናወነው መርሀግብር ላይ በቴክኖሎጂ ሳምንቱ ላይ የተለያዩ የፈጠራ ፕሮጀክቶችን ለሰሩ እና ላቀረቡ ባለሙያዎች የምስክር ወረቀት የተበረከተላቸው ሲሆን፣ በተመሳሳይ መልኩ በተግባራዊ ጥናትና ምርምር ዘርፍ ላይ ማዕከሉን በመወከል በውድድሩ ላይ ለተሳተፉና ላቅ ያለ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላትም የምስጋና ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።
የዕለቱን መርሀግብር በመምራት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቴክኖሎጂ ልማትና ኢንኩቤሽን ም/ዲን አቶ ተስፋዬ ወርቁ ማዕከሉ በቴክኖሎጂ ሳምንት ላይ ባሳየው እጅግ ከፍተኛ ተሳትፎና ባስመዘገበው ውጤት ምክንያት የዋንጫ ሽልማትና የምስክር ወረቀት እንደተበረከተለት ገልጸዋል።
የመርሀግብሩ ማጠቃለያ ላይ የማዕከሉ ዋና ዲን አቶ አድማሱ በቀለ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ይህ ታላቅ ውጤት ሊመዘገብ የቻለው በግለሰብ ጥረት ብቻ ሳይሆን በማዕከሉ ውስጥ የሚገኙ መላው አካላት በጋራና በህብረት በመስራታቸው መሆኑን አውስተዋል። ዋና ዲኑ አክለውም ይህ ስኬት እንዲመጣ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱ የማዕከሉ አባላት በሙሉ ያላቸውን ጥልቅ ምስጋናና አክብሮት አቅርበዋል።
የልህቀት ማዕከሉ የሶሻል ሚዲያ ፕላት ፎርሞችን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ
Websit ....
https://pice.sims.aatvetb.edu.et/
Telegram Channel …….PICE (https://t.me/pice1962)
YOUTUBE Channel ……. PICE1962
(https://www.youtube.com/)
Facebook Channel ………….PICE
(https://m.facebook.com/edu.pice.et/)
TikTok Channel ………Pice_1962
(https://www.tiktok.com/)
06/05/2026
"የቴክኖሎጂ ልህቀት ለሃገር ብልፅግና"
በሚል መሪ ቃል ለሦስት ቀን ሲካሄድ የቆየው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት በዛሬው እለት ተጠናቀቀ።
ሚያዚያ 28/2018 ዓ.ም
በአዲስ አበባ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ "የቴክኖሎጂ ልህቀት ለሃገር ብልፅግና" በሚል መሪ ቃል በአራዳ ፖርክ ለሦስት ቀን ሲካሄድ የቆየው 16 ኛው ከተማ አቀፍ የቴክኒክና ሙያ ሳምንት በዛሬ እለት የተጠናቀቀ ሲሆን በኤግዚቢሽኑ ላይ በተካሄደው የተለያዩ ውድሮች ማዕከሉ የዋንጫና የምስክር ወረቀት ተበርክቶለታል።
በዚህም በተደረገው ማምረቻ የቴክኖሎጂ ፋብሪኬሽን ኢንጅነሪንግ ውድድር ላይ በማዕከሉ 5 መካኒካል መሃንዲሶች አማካኝነት በለማው የወርቅ ደለል ማጠቢያ ማሽን የልህቀት ማዕከሉ የ3ኛ ደረጃን በመያዙ የምስክር ወረቀት የተበረከተለት ሲሆን በተጨማሪም የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ላይ ለሰራው ስኬት ልዩ የዋንጫ ተሸላሚ በመሆን አጠናቋል።
03/04/2026
የልህቀት ማዕከሉን አሰልጣኞች አቅም መገንባት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ እንደሆነ ተገለጸ፡፡
መጋቢት 25/2018 ዓ.ም
ምርታማነት ማሻሻያ የልህቀት ማዕከል ለቴክኒክና ሙያ አመራሮችና አሰልጣኞች፣ ለኢንዱስትሪ ሙያተኞች የክህሎት ክፍተቶችን ማዕከል ያደረገ አጫጭር ስልጠናዎችን መስጠት አንዱ ተልዕኮው እንደሆነ ይታወቃል በማዕከሉ ውስጥ ብቁ አሰልጣኞችን ማፍራትና ለዘመናዊ አሰለጣጠን ዘዴ ማብቃት ከማዕከሉ የሚጠበቅ ተግባር ነው፡፡
ለቴክኒክና ሙያ አሰልጣኞች፣ ለኢንዱስትሪ ሙያተኞች የክህሎት ክፍተቶችን የመሙላት ትልቁን ድርሻ የሚወስዱት የማዕከሉ አሰልጣኞች ሲሆኑ የልህቀት ማዕከሉን አቅም የመገንባት ስራ ደግሞ ከማዕከሉ ይጠበቃል፡፡
በዚህም የልህቀት ማዕከሉን አሰልጣኞች አቅም መገንባ ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ እንደሆነ የማዕከሉ የአቅም ግንባታ ም/ዲን የሆኑት አቶ መክብብ አሰፋ የገለፁ ሲሆን ለጊዜው በ5 ዋና ዋና ርዕሶች በ2 ዙር ለማዕከሉ አሰልጣኞች እየተሰጠ ያለ ስልጠና እንደሆነ አንስተው ስልጠናው ከፌደራል ቲቬት ኢንስቲትዩት በመጡ አሰልጣኞች እየተሰጠ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡፡፡
የስልጠናው ርዕሶች ከላይ የተጠቀሱት እንደሆኑ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
የልህቀት ማዕከሉ የሶሻል ሚዲያ ፕላት ፎርሞችን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ
Websit ....
https://pice.sims.aatvetb.edu.et/
Telegram Channel …….PICE (https://t.me/pice1962)
YOUTUBE Channel ……. PICE1962
(https://www.youtube.com/)
Facebook Channel ………….PICE
(https://m.facebook.com/edu.pice.et/)
TikTok Channel ………Pice_1962
(https://www.tiktok.com/)