07/03/2026
ዜና ዕረፍት፦ ታዋቂው የወንጌል መምህር ዘለዓለም ወንድሙ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለበርካታ ዓመታት በታማኝነትና በትጋት ሲያገለግሉ የቆዩት መምህር ዘለዓለም ወንድሙ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸው ተሰምቷል።
መምህር ዘለዓለም ወንድሙ ከገጠር እስከ ከተማ፣ ከሀገር ውስጥ እስከ ውጭ ሀገራት ድረስ በመዘዋወር ቅዱስ ወንጌልን ያለ ዕረፍት ያስተማሩ ታዋቂና ተወዳጅ መምህር ነበሩ። በወንጌል ስርጭት አገልግሎታቸው በርካታ ምዕመናንን ያጽናኑና የቀረጹ ታላቅ የቤተክርስቲያን ባለውለታ መሆናቸው ይነገራል።
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ አገልግሎት መምህሩ ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸውን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ፤ መምህር ዘለዓለም ያበረከቱትን መንፈሳዊ ተጋድሎ በታላቅ አክብሮት አስታውሷል።
ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው፣ ለተማሪዎቻቸው እንዲሁም ለመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አማኞች በሙሉ መጽናናትን እንመኛለን።
Via የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ አገልግሎት
12/02/2026
ዛሬ በኳታር ዶሃ የቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን::
በኳታር ለምትኖሩ ኦርቶዶክሳውያን በሙሉ፦
ታሪካዊው ዕለት ደረሰ — የቤተክርስቲያናችን የምርቃት በዓል ጉዞ በይፋ የምናበስርበት ስነስርዓት ዛሬ ይካሄዳል።
ዶሃ፣ ኳታር — ለብዙ ዓመታት በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውና የብዙዎች ጸሎትና ድካም ውጤት የሆነው የቤተክርስቲያናችን የምርቃት በዓል ጉዞ በይፋ የምናበስርበት ስነስርዓት ድምቀት ይከናወናል።
በዚህ ታሪካዊ የታላቅ ብሥራት አካል እንዲሆኑና በበረከቱ እንዲሳተፉ ጥሪ ተላልፏል።
የዛሬው መርሃ-ግብር፦
* ክስተት የቤተክርስቲያን የምርቃት በዓል
* ምሽት : 12:30 / 6:30Pm
* ቦታ፦ ዶሃ ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን
* ጥሪ፦ በኳታር የምትገኙ ኦርቶዶክሳውያን በሙሉ እንዳትቀሩ ተጋብዛችኋል።
ይህ የምርቃት ቀን ለምዕመናን የመንፈሳዊ ጥንካሬ እና የአንድነት ተምሳሌት ነው።
ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ!
ይህንን መረጃ በማጋራት በኳታር የሚገኙ ወንድም እህቶቻችን በዚህ ታላቅ በረከት እ
27/01/2026
በረከታቸው ትድረሰን
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የገዳማት መምሪያ የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዕንባቆም ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ።
ብፁዕነታቸው በሀገር ውስጥ እና በኢየሩሣሌም የኢትዮጵያ ገዳማት ሊቀ ጳጳስ በመሆን ሰፊ አገልግሎት አበርክተዋል::
22/01/2026
ጻድቁ ገድላቸውን የፈጸሙት በኢትዮዽያ ቢሆንም ሃገረ ሙላዳቸው የጥንቱ የሮም ግዛት የሆነችው ታናሽ እስያ ናት፡፡
አቡነ አረጋዊ ከዘጠኙ ቅዱሳን አንዱ ናቸው፡፡ ዘጠኙ ቅዱሳን ዘራቸው ከቤተ መንግስት ሲሆን ተወልደው ያደጉት በአንድ የሮም ግዛት ሥር በተለያየ ቦታ ነው፡፡ አንድ ያደረጋቸው መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ ቅዱሳት መጻሕፍትን በሚገባ ያጠኑት እነዚህ አበው ሰማያዊውን ክብር መርጠው ክርስቲያኖች በሚሳደዱበት በ5ኛው ክፍለ ዘመን በቅድሚያ አባ ዸንጠሌዎንና አቡነ አረጋዊ ከዚያም ሌሎቹ ከሮም ወደ ግብጽ በርሃዎች፣ በ470ዎቹ ዓ.ም አልዓሜዳ በኢትዮዽያ ነግሦ ሳለ በአረጋዊ መሪነት ወደ ኢትዮጵያ በምናኔ መጥተዋል፡፡
ንጉሡም በመልካም ተቀብሎ በአክሱም ቤተ ቀጢን ማረፊያ ቦታ ሰጣቸው፡፡ እነርሱም የግዕዝ ቋንቋ ተምረው እዛው አክሱም አካባቢ በአቡነ ሰላማ፣ በአብርሃ ወአጽብሐና በአቡነ ሙሴ ቀዳማዊ የተቀጣጠለውንና በተወሰነ መንገድ ተቀዛቅዞ የነበረውን ክርስትና እንደገና አቀጣጠሉት፤ ለዓመታትም ወንጌልን ሰበኩ በርካታ መጻሕፍትንም ተረጎሙ፡፡ በኋላም የየራሳቸው የምናኔ ቦታ በመምረጥ ወንጌልን እየሰበኩና ስለሀገራችን እየጸለዩ ኖረዋል፡፡
አባታችን አቡነ አረጋዊ በደብረ ዳሞ ታላቅ ገድል ፈጽመዋል፡፡ ማኅሌታዊው ቅዱስ ያሬድና አፄ ገብረ መስቀልም ወዳጆቻቸው ነበሩ፡፡ ጻድቁ ተጋድሏቸውን ፈጽመው በተወለዱ በ99 ዓመታቸው ተሰውረው ብሔረ ሕያዋን ገብተዋል፡፡
ጌታም የምሕረት ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል፡፡ ጥር 14ም ጻድቁ የተወለዱበት ቀን ነው፡፡
መናንያንና ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ስለ ክርስቶስ ፍቅር ብዙ ዋጋ ከፍለዋል፡፡ የወንጌል ብርሃን እንዲበራ፣ ትልቅ ሥራ ሰርተዋል፡፡ ጸሎታቸው አሁንም ተአምር ያደርጋል፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
18/01/2026
በኮዬ ፈጬ የከተራ በዓል አከባበር ላይ በደረሰ የኤሌክትሪክ አደጋ የአራት ወጣቶች ሕይወት አለፈ
ዛሬ ጥር 10 ቀን 2018 ዓ.ም በሸገር ከተማ አስተዳደር፣ በኮዬ ፈጬ ክፍለ ከተማ በሚገኘው የፋንታ መድኃኔዓለም ደብር የጥምቀት ከተራ በዓል አከባበር ላይ አሰቃቂ የኤሌክትሪክ አደጋ ተከስቷል። በዓሉን በታላቅ ድምቀት ለማክበር ታቦተ ሕጉን አጅበው ሲጓዙ የነበሩ አራት ወጣቶች፣ ባልታሰበ ሁኔታ በደረሰባቸው የኤሌክትሪክ ንክኪ ወዲያውኑ ሕይወታቸው አልፏል። ይህ ድንገተኛ አደጋ በበዓሉ ታዳሚዎች እና በነዋሪው ዘንድ ከፍተኛ ድንጋጤንና ጥልቅ ሀዘንን ፈጥሯል።
አደጋው የተከሰተው የቤተክርስቲያኑ ምዕመናን ታቦተ ሕጉን አጅበው ወደ ባሕረ ጥምቀት በማቅናት ላይ እያሉ ነው። ወጣቶቹ ታቦቱ የሚቀመጥበትን ሰረገላ በከፍተኛ መንፈሳዊ ተነሳሽነት እየመሩ ሳለ፣ የሰረገላው የላይኛው ክፍል በመንገድ ላይ ከተዘረጉ የከፍተኛ ኃይል የኤሌክትሪክ መስመሮች ጋር በመነካካቱ አደጋው ሊከሰት ችሏል። የኤሌክትሪክ ኃይሉ በሰረገላው ብረት በኩል በቀጥታ ወደ ወጣቶቹ በመተላለፉ ለህልፈታቸው ምክንያት ሆኗል።
በአደጋው ሕይወታቸውን ያጡት ወጣቶች በደብሩ የሰንበት ትምህርት ቤት እና በበጎ ፈቃድ አገልግሎት በንቃት የሚሳተፉ፣ ለቤተክርስቲያኗም ትልቅ ተስፋ የነበሩ መሆናቸውን የአካባቢው ምንጮች ገልጸዋል። በወቅቱ የነበሩ የዓይን እማኞች እንደሚሉት፣ አደጋው በጣም በፍጥነት በመከሰቱ ወጣቶቹን ለማዳን የተደረገው ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል።
ሌሎች በጥቂቱ የተጎዱ ሰዎችም በአቅራቢያው ወደሚገኝ የጤና ተቋም ተወስደው አስፈላጊው ሕክምና እየተደረገላቸው ይገኛል።
የሸገር ከተማ ፖሊስ እና የሚመለከታቸው የደህንነት አካላት በአደጋው ስፍራ ተገኝተው ምርመራ እያካሄዱ ነው። መሰል አደጋዎች በበዓላት ወቅት እንዳይደገሙ የኤሌክትሪክ መስመሮች የሚገኙባቸውን አካባቢዎች አስቀድሞ መመርመር እና ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባም አሳስበዋል።
በተለይም ከፍተኛ ርዝመት ያላቸውን ሰረገላዎችና የድምፅ ማጉያዎችን በሚጠቀሙበት ወቅት ከኤሌክትሪክ ገመዶች ጋር ያለውን ርቀት ማረጋገጥ ለደህንነት ወሳኝ መሆኑን ባለሙያዎች ይገልጻሉ።
06/01/2026
አእላፍ ዝማሬ__2018
እንኳን አደረሳችሁ
18/12/2025
የባንክ ሰራተኛን በመግደል የተጠረጠረው ግለሰብ እየታደነ ነው።
በሰንዳፋ በኬ ከተማ ታህሳስ 6 ቀን 2018 ዓ.ም አንዲት የባንክ ሰራተኛ ላይ ዘግናኝ የነፍስ ግድያ መፈጸሙን ፖሊስ አስታወቀ። ሟች አዳነች ኩምሳ ትባላለች፤ በአላልቱ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ ሰራተኛና የሰንዳፋ በኬ ነዋሪ ነበረች።
የክስተቱ ዝርዝር
#ግድያው፦ ሟች እና ተጠርጣሪው አቶ ፀጋዬ አሳሊፎ የፍቅር ግንኙነት የነበራቸው ሲሆን፣ በዕለቱ ምሽት በሆቴል ውስጥ ምግብ ሲመገቡ ተጣልተው ሟች ጥላ በመውጣቷ ግድያው ተከስቷል።
#አፈጻጸሙ፦ ተጠርጣሪው በመኪና ተከታትሎ መኪናው ውስጥ ካስገባት በኋላ "ጎማጣ" ተብሎ በሚጠራ አካባቢ በሽጉጥ ገድሏታል።
አሰቃቂ ሁኔታ፦ ተጠርጣሪው ሬሳውን ጥሎ በመጥፋቱ፣ የአዳነች አስከሬን በዱር አራዊት ተበልቶ መገኘቱን የሰንዳፋ በኬ ፖሊስ የምርመራ ክፍል ኃላፊ ኮማንደር ንጋቱ አለሙ ለቢቢሲ ገልጿል ገልጸዋል።
የፖሊስ ምርመራ
ተጠርጣሪው ወንጀሉን የፈጸመበትን መኪና እና ሽጉጥ በአላልቱ ከተማ ጥሎ መሰወሩ ታውቋል። ፖሊስ በመኪናው ውስጥ የደም ዱካ እና ሽጉጡን እንደ ማስረጃ ያገኘ ሲሆን፣ ግለሰቡን በቁጥጥር ስር ለማዋል ክትትል እያደረገ መሆኑን ገልጿል።
የሟች አስከሬን ለምርመራ ወደ ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ከተላከ በኋላ በቤተሰቦቿ የቀብር ስነ-ስርዓቱ ተፈጽሟል።
©ፋስት መረጃ
04/12/2025
በድንገት ህይወቱ ያለፈው የኮሜዲያን ወንድወሰን አውራሪስ ብቸኛ ሴት ልጅ ፈጣሪ ያጽናናሽ 🙌
04/12/2025
የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የስራ ቅጥር ማስታወቂያ
ብዛት: 170
የስራ መደብ: እጩ ዳኛ
የትምህርት ዝግጅት: የመጀመሪያ ዲግሪ በህግ
የስራ ልምድ: 0 ዓመት
የስራ ቦታ: ክልሉ ላይ ባሉ ወረዳዎች
የምዝገባ ጊዜ: እስከ 08/04/2018