12/04/2026
ከሆሳዕና እስከ ኢየሩሳሌም ከኢየሩሳሌም እስከ ጎልጎታ፡ ዝንፍ ያላለው መለኮታዊ የክርሰቶስ ተልእኮ
፬፬፬፬፬፬፬፬፬፬፬፬፭፬፭፬፬፬፬፬፭፭፭፭፭፭፭፭፭፭፭፭፭፭፭፭
በክርስትና አስተምህሮ ውስጥ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የማዳን ጉዞ ፍጻሜውን ያገኘበት "የሕመም ሳምንት" (ሰሙነ ሕመማት) የሰው ልጅ ታሪክ የተቀየረበት የታላቅ ተልእኮ ምዕራፍ ነው። ይህ ጉዞ በሥጋዊ መለኪያ ጥቂት ኪሎ ሜትሮችንና ጥቂት ሰዓታትን የፈጀ ቢመስልም፣ በመንፈሳዊ መለኪያ ግን ከአዳም ውድቀት እስከ ዳግም ምጽዓት ያለውን የሰው ልጅ ዕዳ የዘጋበት መለኮታዊ ጉዞ ነው።
ጌታችን ወደ ኢየሩሳሌም በክብር ከገባበት (ሆሳዕና) አንስቶ በጎልጎታ ሕይወቱን አሳልፎ እስከሰጠበት (ዓርብ) ድረስ ያለው ጊዜ 120 ሰዓታት (አምስት ቀናት) ገደማ ነው። እያንዳንዱ ሰከንድ፣ እያንዳንዱ እርምጃ፣ እያንዳንዱ የሆታና የግርፋት ድምፅ በነቢያት የተነገረውን The Divine Timetable "መለኮታዊ የጊዜ ሰሌዳ" ጠብቆ የተከናወነ ነበር። ይህም ጌታችን በታሪክ ማዕበል ውስጥ ዝም ብሎ የተነዳ ሳይሆን፣ ዓለምን የማዳን ዓላማውን ዝንፍ ሳይል እየመራ እንደነበረ ያሳየናል።
ኢየሩሳሌም የንጉሡ ከተማ ናት፤ ጎልጎታ ደግሞ የሞት ስፍራ ናት። ጌታችን ከከተማው ክብር ወጥቶ ወደ ቆሻሻውና ወደ ተናቀው የራስ ቅል ስፍራ (ጎልጎታ) መጓዙ፣ የሰውን ልጅ ከውርደት ወደ ክብር ለማውጣት የከፈለው መለኮታዊ ልውውጥ ነው። በመንገዱ ላይ ሁለት ተቃራኒ አቀባበሎች ገጥመውታል፦
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ የነበረው አቀባበል በእልልታ፣ በሆታ እና "የክብር ንጉሥ ሆይ፤ አሁን ናና አድን! ሀሆሳእና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው ሆሳእና በዓርያም" በሚሉ የሆሳዕና ድምጾች የታጀበ ነበር። ይህ አቀባበል በሰውኛ እይታ ሲታይ፣ የድልና የክብር ሰካር ውስጥ በመቅረት ቀጣዩን ምዕራፍ—ማለትም ስድብ፣ ግርፋትና ሽሙጥ የሞላበትን የመስቀል ጎዳና—ለመሸሽ የሚያስገድድ "አማላይ ፈተና" ሊሆን ይችል ነበር።
በእርግጥም የሆሳዕናው ዝማሬና "ንጉሥ ነህ፣ አዳኝ ነህ" የሚሉት ድምጾች ለእርሱ የተገቡና እውነተኛ ነበሩ። እነዚህን ቃላት "የሐሰት ውዳሴ አይደሉም" የምንልባቸው ሦስት ዓበይት ምክንያቶች አሉ፦
1. የትንቢት ቃል ፍጻሜ መሆኑ፦ ነቢያት ቀድመው የተናገሩት ቃል በዝርዝር የተፈጸመበት በመሆኑ።
2. እያንዳንዱ የምስጋና ቃል ለባሕርይ አምላክነቱና ለክብሩ የሚመጥን በመሆኑ።
3. ጌታ ምስጋናውን በጸጋ መቀበሉና ትክክለኛነቱን ማረጋገጡ።
የካህናት አለቆችና ጻፎች ቅናት አድሮባቸው "ዝም አሰኛቸው" ባሉት ጊዜ፣ ጌታ የሰጠው ምላሽ "እነዚህ ዝም ቢሉ ድንጋዮች ይጮኻሉ።" ይህ የሚያሳየው ፍጥረት ሁሉ ለፈጣሪው ምስጋና ማቅረብ ተፈጥሯዊ ግዴታው መሆኑን ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ፣ የዕለቱ ውዳሴ "ከንቱና ግብዝ" ነበር ሊባል የሚችልባቸው አሳማኝ ምክንያቶች አሉ። ይህም የሕዝቡ የትንቢት አረዳድ ከተንሸዋረረ አመለካከት የመነጨ በመሆኑ ነው። እርሱ የዋህ ንጉሥ ሆኖ ሊያድን ሲመጣ፣ ሕዝቡ ግን ንግሥናውንና አዳኝነቱን የተረዱበት መንገድ ፍጹም ለየቅል ነበር።
ጌታ ግን በተደረገለት ደማቅ አቀባበል ተመስጦና ተደምሞ ወንበዴዎችን ከመቅደሱ ጠርጎ ከማውጣት ወደ ኋላ አላለም። ይህም ክብሩ ከሰው ምስጋና ሳይሆን ከቅድስናው እንደሚመነጭ ማሳያ ነው። ጌታ አዳኝነቱን ሊገልጽ የፈለገው በዘንባባ ዝንጣፊ፣ በሆታና በእልልታ "አሸሼ ገዳሜ" በማለት ሳይሆን፤ የእሾህ አክሊል ደፍቶ፣ በጎልጎታ ኮረብታ ላይ፣ በጣር ድምፅ "ተፈጸመ" በሚል ታላቅ ድል ነበር።
የሰው ልጅ ተለዋዋጭነት የሚገለጠው እዚህ ላይ ነው፦
• በኃጢአተኞች ክንድ ሲያዝ፣ ገላው በጅራፍ ሲተለተል፣ በኢየሩሳሌም አደባባይ የድል ምልክት የነበሩት ዘንባባዎች ረገፉ።
• በዘንባባው ፋንታ የእሾህ አክሊል ሲደፋ፣ የሕመም ምልክት የሆነውን መስቀል ሲሸከም እና እጆቹ በችንካር ሲቸነከሩ፣ ያ "ሆሳዕና" የሚለው ድምፅ ወደ "ድንቄም አዳኝ" ሽሙጥ ተቀየረ።
በሳምንት ጊዜ ውስጥ ምንጣፉን የሚያነጥፍለት የነበረው ያ መንጋ፣ ራሱን ከሮማውያን ቀንበር የሚያላቅቅ ምድራዊ ፖለቲከኛ ፈላጊ ነበር። ጥቅሙ ሲነካና የጠበቀው ምድራዊ ድል ሲዘገይ፣ ሳይታክት "ሆሳዕና" ይል የነበረው አንደበት "ይሰቀል! ይሰቀል!" ወደሚል ጩኸት ተለወጠ። "በርባንን ፍታልን" በማለትም የወንበዴ ወዳጅ ለመሆን አላፈረም።
ነገር ግን ክርስቶስ በሰው ድጋፍ አልነገሠም፣ በሰው ተቃውሞም ከዙፋኑ አልወረደም። ሲያነግሱት ንጉሥ ነበር፣ ሲሰቅሉትም ያው ንጉሥ ነው። የእርሱ ዓላማ በሰው ውዳሴ ላይ የተመሠረተ ሳይሆን፣ በሰማያዊው የአባቱ ፈቃድ ላይ የቆመ ስለነበረ።የወደቀባቸው ጎዳናዎች ሁሉ የሰው ልጅ በኃጢአት ምክንያት የወደቀበትን ጥልቅ ጉድጓድ የሚደፍኑ ነበሩ።"እርሱ በሥጋ እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ፥ ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ።" (ፊልጵስዩስ 2:8) ክርስቶስ እውነተኛውን የድል አክሊል የተቀዳጀው በዘንባባው አቀባበል ሳይሆን በመስቀሉ መሥዋዕትነት ነው።
ሕይወት ሁልጊዜ የዝንባባ ዝማሬና የ"ሆሳዕና" እልልታ ብቻ አይደለችም። ከክብር መግቢያው ጀርባ የጎልጎታ አቀበት፣ የግርፋት ድምፅና የችንካር ሕመም አለ።
እውነተኛው ፈውስና ትንሳኤ የሚገኘው በመስቀሉ መንገድ፣ በስቃይና በይቅርታ ውስጥ ነው። ለጠላት "ሞት" የሚመስለው የመስቀል መንገድ፣ ለእኛ ግን የእግዚአብሔር የድነት በር ነው።
"ተፈጸመ" ሲል፣ ሰዓቱ መቆሙን ሳይሆን፣ የተሰጠው መለኮታዊ ተልእኮ አብ የጠየቀው የጽድቅ ጥያቄ የሰውልጅ የዘመናት የሀጢያት እዳ ምንም ሳይቀረው ተከፍሎ በድል መጠናቀቁን ማብሰሩ ነበር።
ዛሬም ጥያቄው፦ "ጌታ እንዴት እንዲያድነን ነው የምንጠብቀው?"
ዛሬ እኛ እግዚአብሔርን እንዴት እንዲፈውሰንና እንዴት እንዲያድነን ነው የምንጠብቀው? "አዳኝ ነው" ብለን ዘምረን፣ እርሱ ግን እንዴት እንደሚያድን ካላወቅን ታላቅ ስህተት ላይ ነን። እውነተኛው ድኅነት ከመስቀሉ መንገድ ውጭ ሌላ አማራጭ የለውም።
መስቀሉ የግል ሕይወታችንን ብቻ ሳይሆን፣ የዓለም እይታችንን (Worldview)፣ ርዕዮተ-ዓለማችንንና ፖለቲካችንን ጭምር የሚፈውስ ኃይል ነው። ዛሬ በሀገራችን ላለው መባላት፣ መነካከስና እልቂት እውነተኛ ፈውስ የምናገኘው በዚሁ በመስቀሉ መንገድ በትሕትና፣ ራስን በመስጠትና በይቅርታ መንገድ ብቻ ነው።
መስቀሉ ወደ ትንሣኤ ክብርና ወደ ብርሃኑ ዓለም መሸጋገሪያ ድልድያችን ነው። እርሱ መድኃኒታችን፣ ኃይላችንና ሰላማችን ነውና። መልካም አውድዓመት!!
13/12/2025
EECMY–CES has joyfully ordained 49 ministers to the Ministry of Word and Sacrament.
We give thanks to God for this significant milestone in the life of the Church. May the Lord graciously help these ministers remain faithful to their calling, empowering them to rightly proclaim the Word and faithfully administer the Sacraments for the building up of Christ’s Church .
Our College is also delighted to have contributed to such vibrant ministers for the Church and the proclamation of God’s Kingdom. Congratulations—march on in faith and faithful service! Website
https://eecmycestc.org
Address
/https://maps.app.goo.gl/KVyWN4rnN4hRDqrH7?g_st=atm
08/12/2025
It was a truly wonderful graduation day in Harere on Sunday, 7/2005 E.C. At the Harere Mekane Yesus Congregation, 25 students from the Dire Dawa Center completed their degree and diploma Theological programs with great joy. The celebration was a powerful testimony to God’s work in Eastern Ethiopia.
We witnessed vibrant, dedicated student men and women who carry great hope for their communities ready to serve and willing to sacrifice for the sake of the Gospel. The testimonies shared and the joyful atmosphere among the graduates, families, and church leaders clearly revealed the abundant harvest God is raising in the East.
09/11/2025
Today, on November 9,2025 50 students graduated with a Diploma from the Mojo Training Center.
It was a wonderful and joyful celebration of God’s faithfulness. Congratulations to all the graduates for their hard work, dedication, and achievement! May the Lord continue to bless and guide you as you serve Him in your ministries.
🎉🎉🎉🎉
09/10/2025
On September 5, 2025, the EECMY - CES Theological College celebrated the graduation of 23 students from our Weleso Center! It was a truly wonderful and amazing time of praise and thanksgiving.
We pray that God will empower our graduates to stay focused on their mission and diligently put into practice what they have learned during their studies. May they shine the light of the Gospel wherever they go!
11/09/2025
Congratulations to Our Graduates!
On September 1, EECMY-CES Theological College celebrated the graduation of our students who have faithfully completed their studies and are now ready to serve the Lord and His church. We give glory to God for this milestone and extend our heartfelt congratulations to all graduates. May your ministry bear much fruit in the Kingdom of God. 🙏
As we also step into a new season, we wish you all a Happy Ethiopian New Year! May this year be filled with peace, blessings, and renewed strength for all our students, staff, graduates, and partners in ministry.
“The one who calls you is faithful, and he will do it.” (1 Thessalonians 5:24)
02/09/2025
Announcement
We are excited to announce that on September 6, 2025 (2017 E.C.) from 10:00 am -1 pm EECMY-CES Theological College will celebrate the graduation of our students!
The ceremony will take place at the Korean Hospital Chapel, GNC /Gerji. /🙏 We are truly grateful to the Korean Christian community for their generosity in hosting us and allowing the use of their church building.
Join us in giving thanks to God for this milestone and in praying for our graduates as they step into the mission field for the expansion of God’s kingdom. 🌍✝️
28/08/2025
What a truly wonderful way to end our summer academic ! We were so blessed to have Professor Park Byung with us for an intensive lecture on the Theology of Mission. His passion and deep knowledge were so inspiring; our students left feeling encouraged, joyful, and spiritually refreshed.
We wrapped things up with a special Community Day that brought us all closer together. We expressed our fellowship by working together to clean the college grounds—a perfect act of service and unity. The day culminated in a beautiful Holy Communion service. It was a powerful time to share in our forgiveness and to strengthen our faith and bond as a community in Christ. We were so grateful for Dr. Tebebu, who shared a strong and meaningful message on our Lutheran doctrine on Holy communion
What a beautiful reminder of our purpose and our unity as we move forward!