31/10/2025
Bethlehem Youth Academy
We strive for virtue and quality of education!!
31/10/2025
25/10/2025
ቅዳሜ፣ ጥቅምት 15፣ 2018 ዓ.ም
የምስጋና መልዕክት!!
ለተከበራችሁ ለቤተልሔም ዩዝ አካዳሚ የቅድመ አንደኛ ደረጃ የተማሪ ወላጆች/አሳዳጊዎች:-
በዛሬው ዕለት ባደረግነው ውይይት ለመካፈል አስቀድመን የላክነውን የክብር ግብዣ ተቀብላችሁ ሰዓቱን አክብራችሁ በመገኘት የውይይታችን ተሳታፊ ለነበራችሁ ወላጆች ሁሉ ከልብ የመነጨ ምስጋናችንን እናቀርባለን። ያደረግነው ውይይት እጅግ አስፈላጊ እና በልጆቻችን የወደፊት ዕጣ ፈንታ ላይ ጉልህ አስተዋፅዖ የሚያበረክት እንደሆነ እናምናለን። በቀጣይ ያደረግነውን ፍሬያማ ውይይት ወደ ተግባር ቀይረን እንደምናሳይ ልናረጋግጥላችሁ እንወዳለን። ሁሌም ስለምታደርጉልን ቀና ትብብር ልናመሰግን እንወዳለን።
የት/ቤቱ አስተዳደር
27/09/2025
የሂሳብና እንግሊዘኛ ማጠናከሪያ ትምህርቶችን ከዛሬ ጀምሮ በቴሌቭዥን መስጠት ይጀምራል
********************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ከአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ጋር በመተባባር የሂሳብና እንግሊዘኛ ማጠናከሪያ ትምህርቶችን ከዛሬ ጀምሮ በቴሌቭዥን ስርጭት መስጠት መጀመሩን አስታውቋል።
የቢሮው ሀላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ከተማ አስተዳደሩ የትምህርት ጥራትን ለማምጣት በልዩ ትኩረት እየሰራ ነው። ከተያዙ ስትረቴጂ ግብ ውስጥ አንዱ ትምህርት በቴሌቪዥን የማሰራጨት መሆኑን ነው የገለፁት።
የትምህርት ሥርጭቱ ከየካቲት 25 ጀምሮ በኤኤምኤን ፕላስ ከሰኞ እስከ አርብ ከ11 እስከ 2 ሰዓት እንዲሁም ቅዳሜና እሁድ ጠዋት 2 እስከ 6 ሰዓት እንደሚሰጥ ገልጸዋል።
በሥርጭቱ የእንግሊዝኛና ሂሳብ ትምህርቶችን በእንግሊዘኛ በአማረኛና አፋን ኦሮሞ ቋንቋዎች እንደሚሰጥ ተናግረዋል።
ትምህርቱ ከ4 እስከ 8ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ በመግለጽ ሥርጭቱ 13 ዘርፎች ላይ ትምህርት እንደሚሰጥ ጠቁመዋል።
የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ዋና ሥራ አቶ ካሳሁን ጎንፋ በበኩላቸው፣ የትምህርት ስርጭቱ ከ4ኛ እስከ 8ኛ ክፍል ተማሪዎች በ2 የትምህርት አይነቶች፤በ3 የማስተማሪያ ቋንቋዎች እና በ13 ዘርፎች ላይ ይከናወናል።
በኤኤምኔን ፕላስ ቻናልን ጨምሮ በትምህርት ቢሮና አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች እንደሚተላለፍ ጠቁመዋል።
በማርቆስ በላይ
የካቲት 25 ቀን 2017 ዓም
27/09/2025
With Kalebin ገጠር – I just got recognized as one of their top fans! 🎉
27/09/2025
16/09/2025
የቤተልሔም ዩዝ አካዳሚ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ቅርንጫፍ የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ሰኞ፣ መስከረም 05፣ 2018 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ ተጀምሯል።
የቤተልሔም ዩዝ አካዳሚ የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በአራቱም ቅርንጫፎች በዛሬው ዕለት ሰኞ፣መስከረም 05፣ 2018 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ ተጀምሯል።
15/09/2025
የቤተልሔም ዩዝ አካዳሚ የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በአራቱም ቅርንጫፎች በዛሬው ዕለት ሰኞ፣መስከረም 05፣ 2018 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ ተጀምሯል።
14/09/2025
ሰኞ፣ መስከረም 05፣ 2018 ዓ.ም ትምህርት ይጀመራል።
Click here to claim your Sponsored Listing.
Location
Category
Contact the school
Telephone
Website
Address
1. , Address Ethiopia, Addis Ketema Sub Sity, Merkato Around Amauel Church Behind Total Gas Station
Addis Ababa
122