በአለማችን ከሰይጣን ሀይል የተነሳ የሰው ክፋት እጅግም የበዛበት ሆኗል፤ ሰዎች በምድር ላይ አለን በሚሉት ነገር እርካታን፣ ሰላምን፣ ዋስትናን ማግኘት ያልቻሉበትም ወቅት ነው፡፡ በዚህ አስጨናቂ አለም ውስጥ በድል አድራጊነት በሰላምና በእፎይታ መኖር የሚቻለው በክርስቶስ ኢየሱስ ብቻ ነው፡፡ ነገር ግን ወደዚህ በረከት ለመግባት ክርስቶስን የተቀበልንበት መንገድ ወሳኝ ነው፡፡ ብዙ ሰዎች ክርስቶስን በሀይማኖት መልክ፣ በፍልስፍና መልክ፣ በምድር ስለሚያገኙት ብልጽግናና ተአምራት፣ በመልካም ስራና በመሳሰሉት ተቀብለውታል፣ ግን ሰላምና በእርሱ የሚገኝ የእርካታ ህይወት የላቸውም፡፡ ኢየሱስ በምድር በነበረበት ወቅት ደቀመዛሙርቱን ሰዎች እኔን ማን ይላሉ? ካለ በኋላ በመቀጠል እናንተስ ማን ትሉኛላችሁ? በማለት ጠይቋል፡፡ ጴጥሮስም አንተ ክርስቶስ የህያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ አለ፡፡ ይህ መገለጥ ነበር፡፡ ክርስቶስ መገለጥ ነው፣ ክርስቶስ ህይወት ነው፣ ክርስቶስ ብርሀን ነው፣ ክርስቶስ እርሱ እውነተኛ መንገድ ህይወትና እውነትም ነው፣ ክርስቶስ እውነተኛም ነብይ ነው፣ ክርስቶስ እርሱ ንጉስ ነው፡፡
ክርስቶስን ስንቀበል አስደናቂ በረከቶች ወደ እኛ መጥተዋል፣ የመንግስት ለውጥ አድርገናል፣ የእግዚአብሔር ልጆች ሆነናል፣ መንፈስ ቅዱስ በእኛ ውስጥ በማደር ይመራላል፣ ያስተምረናል፣ ይመክረናል፣ የዐሎት መልስ እናገኛለን፣ በቅዱሳን መልአክት ሁል ጊዜም ቢሆን የተጠበቅን ነን፣ የጨለማ ስልጣን ፈርሷል፣ ሰማያዊ ዜግነት አግኝተናል፣ ታላቁን ተልዕኮ የምንፈጽም አምባሳደሮች ነን፡፡ ከዚህ የተነሳ ሁልጊዜም ቢሆን በድል እንኖራለን፣ ክርስቶስን ለብሰናልና ለሰይጣን አስፈሪዎች ነን፡፡ ይህ ሁሉ የሚሆነው ግን የዘላለም ቃሉን በፍጹም ልብ በማመን ብቻ ነው፡፡
አፍሮ ቺልድረን ስኩል
Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from አፍሮ ቺልድረን ስኩል, Education, Addis abeba, Addis Ababa.
CHILDREN ARE GOD'S PREVIOUS GIFT TO US. IT IS OUR DESIRE TO PROVIDE SCOOL AND LOVING ENVIRONMENT FOR CHILDREN TO EXPERIENCE GOD AND THE JOY OF LEARNING MORE ABOUT HOW MUCH GOD LOVES THEM.
20/08/2019
በገላትያ ምዕራፍ 5 ከተገለጹት የመንፈስ ፍሬዎች መካከል አንዱ በጎነት ነው፡፡ በጎነት ለሰዎች ያለን መልካም አመለካከትና የምናደርገው ማንኛውም መልካም ሥራ ሁሉ ነው፡፡ በጎነት ማንኛውንም መልካምና ጥሩ፣ የበጀ የተወደደ፣ ሥራን ያካትታል።
በጎነት ማድረግ ከደስታም በላይ ነው
[email protected]
20/08/2019
አፍሮ ቺልድረን ስኩል ሀገር በቀል የወገን ህመም ህመሜ ብሎ የተመሰረተ ተቋም ነው። ተቋማችን እኛ እያለን አንድም ህፃን ከትምህርት ገበታ መቅረት የለበትም በሚል አላማ የሚንቀሳቀስ ተቋም ነው።
እግዚአብሔር አምላክ በሰጠን ዘመን፣ በሰጠን አቅምና ዕውቀት ከኛ ባለፈ ለትውልድ ልንሰራ ግድ ብሎናል።
ውድ ወገኖቻችን
አበው ሲተርቱ " ሃምሳ ሎሚ ለአንድ ሰው ሸክሙ ለሃምሳ ሰው ጌጡ ነው" ይላሉ። በሀገራችን ያሉ በርካታ ህፃናት የትምህርት ገበታ እየናፈቃቸው ዕድሉን ባለማግኘታቸው ከመንደር ካለማወቅ ጋር ይኖራሉ፣ ይህ ብቻ ሳይሆን በንፁህ ውሃ እጦት፣ በምግብ እጥረት እኚሁ ህፃናት ለችግር ተጋልጠው ይገኛሉ።
ለአብነት እኛ ተንቀሳቅሰን በሰራንባቸው አከባቢዎች
በአፋር፣በሶማሌ፣በምዕራብ አርሲ፣በባሌ በጅማ፣ በደቡብ ብሔር ብሔረሰብ እና ህዝቦች ክልላዊ መንግስት በሀላባ እንዲሁም በደቡብ ኦሞ በመንግስት የትምህርት ሽፋን ያልተዳረሰባቸው አከባቢዎች እኛ በመድረስ በርካታ ት/ቤቶችን ሰርተናል፣ የውሃ እጥረት ባለበት ንፁህ የመጠጥ ውሃ እንዲያገኙ አድርገናል።
እስካሁን ያለው ጉዟችን መልካም ቢሆንም ችግሩ ስፋት አንፃር እጅ ለእጅ ተያይዞ መስራቱ ለሀገር ውለታ እንደመዋል ነውና ሁላችን የአንድ ቀን የማኪያቶ ወጪያችንን እንኳ ብንቀንስ እና ለነዚህ ህፃናት ብናውል ትልቅ ለውጥ ማምጣት እንችላለን።
ለዚህም እንደ ሃምሳ ሎሚው ሃምሳው ለሁላችን ጌጥ የሆኑንን ትውልዶች እንድናፈራ እናበረታታችሇለን።
ለበለጠ መረጃ
በ 093009348
በ email _ [email protected]
ያግኙን
Click here to claim your Sponsored Listing.
Location
Category
Telephone
Website
Address
Addis Abeba
Addis Ababa