18/04/2026
New Line College
Maytsebri New Line College
18/04/2026
13/04/2026
#በሃሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ተቀጥረው ሲያስተምሩ የነበሩ የመምህራን ቅጥር ተቋረጠ።
ደባርቅ:- ሚያዝያ 05/2018 ዓ/ም (ሰሜን ጎንደር ኮሙዩኒኬሽን )
በሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ በሃሰተኛ የትምህርት ማስረጃ በመምህርነት ተቀጥረው ሲያስተምሩ የነበሩ የ19 መምህራን ቅጥር ማቋረጡን የጠለምት ወረዳ ትምህርት ፅህፈት ቤት አስታወቀ።
የጠለምት ወረዳ ትምህርት ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቸርነት መኳንንት እንዳስታወቁት በተለያዩ ወቅቶች የተቀጠሩ መምህራን መረጃ ከተማሩበት ኮሌጅ ድረስ በመላክ የ19 መምህራን መረጃ ሃሰተኛ መሆኑ ስለተረጋገጠ ቅጥራቸው ተሰርዟል ብለዋል።
አቶ ቸርነት አያይዘውም ሃሰተኛ ዲግሪ በማያያዝ ከመምህር ወደ ርእሰ መምህር ያደጉ የ3 ርእሳነ መምህራን መረጃ ሃሰተኛ መሆኑን በማረጋገጥ ከርእሰ መምህርነት ታግደዋል ብለዋል።
ጠለምት ወረዳ ኮሙዩኒኬሽን
12/04/2026
የትንሳኤ በዓል ታሪክ መሠረቱ ተስፋ፣ ጽናት እና አዲስ ጅማሬ ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ካሳለፈው መከራ በኋላ በድል በመነሣት ለሰው ልጆች ድኅነትና አዲስ ሕይወት አምጥቷል።
❤️❤️❤️
በሥራችንም ሆነ በግል ሕይወታችን የሚያጋጥሙን ተግዳሮቶች ሁሉ ወደ ላቀ ስኬት መሸጋገሪያ መንገዶች መሆናቸውን ይህ ታላቅ በዓል ያሳስበናል።
❤️❤️❤️
በዓሉ ለእያንዳንዳችን አዲስ ነገር፣ አዲስ ሰላም እና አዲስ ስኬት ይዞ እንዲመጣ መልካም ምኞታችን ነው።
ኒው ላይን ኮሌጅ ማይፀብሪ ዋና ካምፖስ ማስተባበርያ ቢሮ
መልካም ፋሲካ!
10/04/2026
☦️ መልካም የስቅለት በዓል! ☦️
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ በሙሉ፦
"እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!"
ይህ በዓል፦
የሰላም🕊️
የፍቅር ❤️ እና
የበረከት ✨
እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን!
09/04/2026
ቢሮው በአዲስ እሳቤዎች እና ተግባራዊ አፈፃፀማቸው ዙሪያ ለጠቅላላ ሰራተኞች ስልጠና መሰጠቱን ገለፀ።
የአብክመ ሥራ እና ክህሎት ቢሮ በዘርፍ አዲስ እሳቤዎች እና ተግባራዊ አፈፃፀማቸው ዙሪያ ለጠቅላላ ሰራተኞቹ ልዩ ስልጠና በተቋማት አቅም ግንባታ: አግባብነት እና ጥራት ማረጋገጫ ዳሬክቶሬት ዳሬክተር በአቶ ሙላው ልመንህ መሰጠቱን አሳወቀ። አቶ ሙላው “ የተቋሙ አዲስ እሳቤዎችና የሪፎርም አምዶች ” በሚል ርዕስ ዙሪያ ስልጠናውን በጥልቀት ያቀረቡ ሲሆን ስልጠናው የቢሮው እሳቤዎች እና አፈፃፀማቸውን ከጠቅላላ ሰራተኞች ጋር የጋራ ተደርጓል። ከዚሁ ጋር በማያያዝ አቶ ሙላው ለዘርፍ እሳቤዎች ስኬታማነት ሠራተኛው እራሱን በፈጠራ፣ በዲጂታል ቴክኖሎጂ እና በዘመናዊ የአገልግሎት አሰጣጥ ዘዴዎች አቅማቸውን ማሳደግ ይኖርብናል ብለዋል። እንደ አቶ ሙላው ልመንህ ገለፃ ዛሬ የሥራ ቦታዎች በፈጣን ለውጥ ላይ ናቸው። በመሆኑም አሉ እሳቸው የዘርፍ አዲስ እሳቤዎችን በፍጠነት በመቀበላችን እና በመተግበራችን ዛሬ ላይ ተቋማት አጠቃላይ አቅም በማሳደግ ተመራጭ መሆን ጀምረዋል። አቶ ሙላው ለዚህ ስኬት የእያንዳንዱ ሰራተኛ ድርሻ የጎላ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል። በተለይ ዲጂታል መሳሪያዎችን በመጠቀም የአገልግሎት ፍጥነትን እንዴት ማሳደግ እንደምንችል ተምረናል ብለዋል።
በመጨረሻም የቢሮው ሃላፊ ዶ/ር ስቡህ ገቢያው ይህ ዓይነቱ ስልጠና በቀጣይም በተደጋጋሚ ይካሄዳል ብለው ገልጸዋል። ይህም ከጀመርነው የሪፎርም ስራ አንፃር የቢሮው ሰራተኞችን ብቃት ለማጎልበትና የአገልግሎት ጥራትን ለማሻሻል ያግዛል ብለዋል።
የቢሮው የህዝብ ግንኙነት ክፍል
በከፍተኛ ትምህርት እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ፈቃድ እና ፈቃድ እድሳት አሰጣጥ መመሪያ ቁጥር 988/ 2016 መሠረት የከፍተኛ ትምህርት አሰጣጥ ዘዴዎች፡-
--------------------------------------------------------------------------
** በቀን ክፍለ ጊዜ የሚሰጥ ትምህርት ነው።
** (Online learning) ማለት ሙሉ በሙሉ የመረጃና መገናኛ ቴክኖሎጂ መሣሪያዎችን በመጠቀም በበይነ መረብ አማካኝነት ተማሪ በአካል መገኘት ሳያስፈልገው ባለበት ቦታ ሆኖ ትምህርቱን እንዲከታተል በማድረግ የሚሰጥ የከፍተኛ ትምህርት አሰጣጥ ዘዴ
ነው።
** ፈቃድ በተሰጠበት ከተማና አካባቢ እስከ 50 ኪ.ሜ ራዲየስ የሚሸፍን በቦታ የተገደበ ሆኖ ቢያንስ በአንድ ተርም ሁለት(2) ጊዜ ተማሪዎች በአካል እየተገኙ የገጽ ለገጽ ትምህርት የሚሰጥበት የከፍተኛ ትምህርት አሰጣጥ ዘዴ ነው።
** በማታ፡ በቅዳሜና እሁድ ወይም በክረምት ትምህርት የሚሰጥበት የመርሃ ግብር ነው።
** በማታ ክፍለ ጊዜ ትምህርት የሚሰጥበት ዘዴ ሆኖ በዓመት እኩል የተከፋፈሉ ሶስት ሴሚስተሮች ክረምትን ጨምሮ የሚሰጥበት ዘዴ ነው።
** በሳምንቱ መጨረሻ ቅዳሜና እሁድ ክፍለ ጊዜ የሚሰጥ ሆኖ በዓመት እኩል የተከፋፈለ ሶስት ሴሚስተሮች ክረምትን ጨምሮ የሚሰጥበት ዘዴ ነው።
** በክረምት ወራት የሚሰጥ የከፍተኛ ትምህርት አሰጣጥ ዘዴ ነው።
** ውጭ ሀገር እውቅና ያለው ተቋም ሀገር ውስጥ ከሚገኝ ፈቃድ ወይም እውቅና ካለው ተቋም ጋር በመተባበር ወይም እውቅና ያለው የውጭ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ሀገር ውስጥ ፈቃድ በማውጣት የሁለተኛ ዲግሪ እና ሶስተኛ ዲግሪ መርሃ ግብር በጋራ ወይም በተናጠል የሚሰጥበት የትምህርት አሰጣጥ ዘዴ ነው።
የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
FDRE Education and Training Authority-ETA
Encourage and assist the growth of organizational culture in education and training institutions.
08/04/2026
Call for Papers: 2nd Annual National Research Conference 📢
Debark University invites researchers and academics to submit papers for our upcoming national conference on
May 17–18, 2026.
📍 Thematic Areas:**
*Sustainable Agriculture & Environmental Management
* Tourism Development & Heritage Management
* Indigenous Knowledge
📅 Key Dates:
Abstract Deadline:April 14
Full Paper Submission: April 24–28
Acceptance Notification: May 4
📝 Submission Highlights:
Abstracts: Max 250 words
Papers: Max 10 pages (MS Word)
Publication Opportunity: *Ras Dejen Journal of Science*
📧 Contact/Submit: [email protected]
[email protected]
05/04/2026
05/04/2026
🌍✨ ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ!
በሥራና ክህሎት ሚኒስትር በለማው የኢትዮጵያ ሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት /E-LMIS/ ሥራ ፈላጊ ለሆኑ ዜጐች ከስራ ቀጣሪ ተቋማት ጋር በጋራ በተለያዩ የስራ ዘርፍ በE-LMIS በኩል ሰራተኞችን መመልመል ይፈልጋል።
የስራ መደቦች
📌 CIVIL FOREMAN (ሲቪል ፎርማን (የግንባታ ተቆጣጣሪ)- ብዛት 100
📌 CIVIL CHARGEHANDS ( ሲቪል ቻርጅሃንድ (ረዳት ተቆጣጣሪ)- ብዛት 200
📌 MASONS (ግንበኞች)- ብዛት 100
📌 SHUTTERING CAPENTERS (ቅርጽ አውጪዎች)- ብዛት 100
📌 STEEL FIXERS ( ብረት አሳሪዎች) - ብዛት 100
📌 CONSTRUCTION HELPERS (የግንባታ ረዳት ሰራተኞች (ቀን ሰራተኞች)- ብዛት 500
🏫 ስለሆነም ይሆንን እድል ለትጠቀሙ የምትፈልጉ በመጀመሪያ lmis.gov.et ብላችሁ በመመዝገብ አቅራቢያችሁ ባለ የአገልግሎት መስጫ ማዕከል (ወረዳ ወይም ቀበሌ) በመሄድ የባዮሜትሪክስ መረጃ በመስጠት የሰራተኛነት መለያ ቁጥር /Labor ID/ ከያዛችሁ በዚህ https://forms.lmis.gov.et/uae-new-2/ በመግባት ትክክለኛ መረጃዎችን ሞልተው ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
☎️አስተያየት እና ጥቆማዎን በ9138 ነፃ የሥልክ መስመር በመደወል እንዲያደርሱን እናሳስባለን።
04/04/2026
02/04/2026
📝ማስታወቂያ🔔
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚዘጋጅባቸውን የትምህርት ዓይነቶችና የክፍል ደረጃዎች ይፋ አድርጓል።
በዚሁ መሠረት፡-
1) ፈተና የሚሰጥባቸው የትምህርት ዓይነቶች በተፈጥሮ ሳይንስ እንግሊዘኛ፣ ሒሳብ፣ ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ ባዮሎጂ፣ ኬሚስትሪና ፊዝክስ ሲሆኑ በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ እንግሊዘኛ፣ ሒሳብ፣ ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ ታሪክ፣ ጂኦግራፊና ኢኮኖሚክስ ናቸው።
2) ፈተናው በየትምህርት ዓይነቱ ከ9ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል ያሉትን ሁሉንም ምዕራፎች የሚሸፍን ይሆናል። የዝግጅት አግባቡም 9ኛ ክፍል ላይ የቀድሞውና የአዲሱ ስርዓተ ትምህርቶች የጋራ ይዘት (Common Contents) ላይ ያተኩራል። ከ10ኛ እስከ 12ኛ ከፍል ያለው በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ላይ የተመሠረተ ይሆናል። የኢኮኖሚክስ የትምህርት ዓይነት ግን በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሠረት ሆኖ ከ10ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያለውን የሚሸፍን ይሆናል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
02/04/2026
Click here to claim your Sponsored Listing.
Location
Category
Contact the school
Telephone
Website
Address
Addis Ababa