New Line College

New Line College Maytsebri New Line College

31/07/2026
1. የብቃት ምዘና (CoC) ማለት ምን ማለት ነው?የብቃት ሰርቲፊኬት/ምዘና (Certificate of Competence - CoC) አንድ ግለሰብ በአንድ የተወሰነ መስክ ውስጥ አስፈላጊውን እው...
29/07/2026

1. የብቃት ምዘና (CoC) ማለት ምን ማለት ነው?

የብቃት ሰርቲፊኬት/ምዘና (Certificate of Competence - CoC) አንድ ግለሰብ በአንድ የተወሰነ መስክ ውስጥ አስፈላጊውን እውቀት፣ ክህሎት እና ብቃት እንዳለው የሚያረጋግጥ ይፋዊ ሰነድ ነው።

2. የብቃት ሰርተፍኬት (CoC) ጥቅሞች

1. ሙያዊ ብቃትን ያረጋግጣል፦ አንድ ሰው በስራው ውስጥ አስፈላጊውን ክህሎት እንዳለው ይፋዊ ማረጋገጫ ይሰጣል።

2. የስራ እድሎችን ያሳድጋል፦ በገበያ ውስጥ ተወዳዳሪነትን ያሳድጋል።

3. ለከፍተኛ ኃላፊነት ያበቃል፦ ከፍተኛ ስራዎችን ለመስራት መንገድ ይከፍታል።

4. የተሻለ ደሞዝ ያስገኛል፦ የተረጋገጡ ባለሙያዎች ከፍተኛ ክፍያ ያገኛሉ።

5. የአለም አቀፍ ደረጃን ያሟላል፦ እንደ STCW ባሉ አለም አቀፍ ስምምነቶች መሰረት የሚወጣ ነው።

6. የህግ መስፈርት ሊሆን ይችላል፦ በአንዳንድ ሙያዎች ለመስራት ህጋዊ ፍቃድ ነው።

7. የደህንነት ደረጃን ያሻሽላል፦ ሰራተኞች ስራቸውን በደህና እንዲሰሩ ያረጋግጣል።

8. የባለሙያነት ማረጋገጫ ነው፦ እውቀትን እና ልምድን በይፋ ያረጋግጣል።

9. ለሙያ እድገት መሰረት ነው፦ ወደ ከፍተኛ የስልጠና እና የሙያ ደረጃዎች ያመራል።

10. አሠሪዎች የሚያምኑት ማስረጃ ነው፦ በተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ውስጥ እምነት የሚጣልበት ማረጋገጫ ነው።

11. የበላይ ተቆጣጣሪዎች ይፈልጉታል፦ ለቁጥጥር እና ፍተሻ አስፈላጊ ነው።

12. የስራ እርግጠኝነትን ያሳድጋል፦ ለረጅም ጊዜ የስራ መቆያ እድልን ይጨምራል።

13. በፍጥነት ወደ ስራ ለመግባት ያስችላል፦ አጭር ጊዜ በሚፈልጉ የሙያ መስኮች ፈጣን መፍትሄ ነው።

14. የስራ መደብ መለያ ያደርጋል፦ አንድ ሰው ምን ኃላፊነት መያዝ እንደሚችል ይገልጻል።

15. የተማሪዎችን ምዘና ያመቻቻል፦ በስልጠና ላይ ያሉ ሰዎች ብቃታቸውን ለማረጋገጥ ይጠቀማሉ።

16. የሙያ ዕውቅና ይሰጣል፦ በአንድ ዘርፍ ውስጥ ባለሙያነትን ያሳያል።

17. ለተለያዩ የስራ መደቦች ያበቃል፦ ለመርከብ መኮንን፣ መሐንዲስ፣ ወዘተ የተለያዩ ዓይነቶች አሉ።

18. የስራ መስክ ደረጃን ይጠብቃል፦ ኢንዱስትሪዎች ደረጃቸውን እንዲጠብቁ ይረዳል።

19. ለተማሪዎች እና ሰልጣኞች ጥቅም አለው፦ ሙያቸውን ለሚጀምሩ ጠቃሚ ነው።

20. በተለያዩ አገሮች ውስጥ ይታወቃል፦ በአለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና ሊኖረው ይችላል።

ራስ ገዚ ዩኒቨርስቲዎች በአድስ አመራር እየተተኩ ነው። ትምህርት ሚንስቴር በቀን 10/112018 በፃፈው ደብዳቤ በራስ ገዝነት ዝግጁነት ላይ ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ፣ የራስ ገዝነት ሂደት እንዲ...
29/07/2026

ራስ ገዚ ዩኒቨርስቲዎች በአድስ አመራር እየተተኩ ነው።

ትምህርት ሚንስቴር በቀን 10/112018 በፃፈው ደብዳቤ በራስ ገዝነት ዝግጁነት ላይ ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ፣ የራስ ገዝነት ሂደት እንዲጀምሩ የተፈቀደላቸው ዘጠኙ ዩኒቨርሲቲዎች፣ በሚመደበው_አመራር_በአዲስ እይታ የሪፎርም ዕቅድ አቅርበው ወደ ሥራ የሚገቡ ስለሆነ፣ ማንኛውንም ከመደበኛ ሥራዎች ውጭ የሆነ ተግባር በትምህርት ሚኒስቴር ካልተፈቀደ በስተቀር እንዳያከናውኑ አሳስቦ ነበር።

በዚህ መሠረት የሁለቱ ዩኒቨርሲቲዎች አመራሮች ተቀይረው በአዳድስ አመራሮች የተተኩ ስሆን ሌሎችም በቀጣይ የሚፈፀሙ ይሆናል።

27/07/2026

‎📌 ለመውጫ ፈተና ያልተሳካላቸው ተማሪዎች "Special Diploma" ይሰጣል!
‎ከሐምሌ 2015 ዓ.ም ጀምሮ መውጫ ፈተናውን ወስደው ያላለፉ ዕጩ ተመራቂዎች ልዩ ዲፕሎማ (Special Diploma) ሰርተፊኬት እንደሚሰጣቸው የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት አስታውቋል።

‎ህብረቱ ከትምህርት ሚኒስቴር አመራሮች ጋር ባደረገው ተከታታይ ውይይት መሰረት ውሳኔው ላይ መድረሱን ለቲክቫህ ገልጿል።

‎ዋና ዋና ነጥቦች፦
‎✅ ልዩ ዲፕሎማው በቅርቡ መሰጠት እንደሚጀምር ተረጋግጧል
‎✅ ተማሪዎቹ ሥራ እየሠሩ በማንኛውም ጊዜ ፈተናውን በድጋሜ መውሰድ ይችላሉ
‎✅ ፈተናውን ያላለፉት ልዩ ዲፕሎማ፣ ያለፉት ደግሞ ዲግሪ ይሰጣቸዋል
‎✅ ለልዩ ዲፕሎማው የደመወዝ ስኬል እንዲወጣ ህብረቱ ከሚኒስቴር ጋር እየተወያየ ይገኛል


‎English:
‎Follow | Like | Share | Comment ያድርጉ!

ማስታወቂያ!​በመቐለ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁለ2018 ዓ.ም. የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ ፈተና (ESSLCE) የወረቀት ተፈታኞች በሙሉ​በ2018 ዓ.ም. በወረቀት ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ ፈተ...
22/07/2026

ማስታወቂያ!
​በመቐለ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ
ለ2018 ዓ.ም. የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ ፈተና (ESSLCE) የወረቀት ተፈታኞች በሙሉ
​በ2018 ዓ.ም. በወረቀት ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ ፈተና (ESSLCE) በመቐለ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ ተፈታኞች በሙሉ የፈተናው መርሃ-ግብር እንደሚከተለው መሆኑን እናስታውቃለን።
​ሐምሌ 20 ቀን 2018 ዓ.ም.፦ በየግቢው በመገኘት አቀባበል፣ ምዝገባ እና የመኝታ ክፍል ምደባ
​ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም.፦ ጠዋት ስለ ፈተናው ሂደት፣ ደንቦች፣ መብቶችና ግዴታዎች ዝርዝር ገለጻና ግንዛቤ መስጠት (Orientation day)
​ሐምሌ 22 – 24 ቀን 2018 ዓ.ም.፦ ዋናው ሀገራዊ ፈተና የሚሰጥበት ጊዜ
​መቐለ ዩኒቨርሲቲ ፈተናው የተሳካ እንዲሆን ሁሉንም አስፈላጊ ዝግጅቶች አጠናቆ እየተጠባበቀ ይገኛል። ስለዚህ በመቐለ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ ተፈታኞች በሙሉ ሐምሌ 20 ቀን 2018 ዓ.ም. ከጠዋቱ ጀምሮ አቀባበል ለማድረግ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን እየገለጽን፣ በተመደባችሁበት ግቢ በጊዜው እንድትደርሱ እናሳስባለን።
​ተፈታኞች ይዘው መምጣት የሚገባቸው አስፈላጊ ቁሳቁሶች፦
​የግል ልብሶች፦ ብርድ ልብስ፣ አንሶላ እና የትራስ መሸፈኛ፤
​የግል ንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች፦ ሳሙና፣ የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች ወዘተ.፤
​ለፈተና የተፈቀዱ የመፃፊያ ቁሳቁሶች፦ እርሳስ፣ ላጲስ፣ የእርሳስ መሳያ (መቅረጫ)፤
​የግል መታወቂያ እና የሀገራዊ ፈተና መለያ ካርድ (ESSLCE Identification Card)።
​ማሳሰቢያ፦
ተንቀሳቃሽ ስልክ (Mobile phone)፣ ሰዓት፣ ጌጣጌጦች (ቀለበት፣ ሐብል ወዘተ.)፣ ስለታም ያላቸው እና ሹል ነገሮችን ይዞ ወደ ግቢ መግባት የተከለከለ ነው። ይህንኑ ተገንዝባችሁ በተጠቀሰው ቀን በተመደባችሁበት ግቢ ለመገኘት ከወዲሁ እንድትዘጋጁ በአክብሮት እናሳስባለን።

​መቐለ ዩኒቨርሲቲ
ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም

21/07/2026

የጥሪ ማስታወቂያ
_____//____

ለአክሱም ዩኒቨርሲቲ ነባር የክረምት (Summer) እና ኢ-መደበኛ (Extension) ተማሪዎች፤
________________//_____________

በአክሱም ዩኒቨርሲቲ በመንግስት ስፖንሰርሺፕ እና በግል በክረምት እና ኤክስቴንሽን መርሃግብር ስትማሩ የነበራችሁ ነባር የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎች፤ እንዲሁም የPGD ተማሪዎች፤ የ2018 ዓ/ም የክረምት ሴሚስተር ትምህርት ምዝገባ የሚከናወነው፡
1. ለኤክስቴንሽን ተማሪዎች ከሐምሌ 25-26/2018 ዓ/ም፤
2. ለክረምት ተማሪዎች ከሐምሌ 27-28/2018 ዓ/ም
በዋናው ግቢ የሚከናወን መሆኑን እየገለጽን፤ ከተጠቀሱት ቀናት ቀድሞ ይሁን ዘግይቶ የሚመጣ ተማሪ የማናስተናግድ መሆናችንን ለማሳወቅ እንወዳለን።
ማሳሰቢያ፦
ኦፊሻል ትራንስክሪፕት ያላስላካችሁ የድህረ-ምረቃ ተማሪዎች፤ የመጀመሪያ ዲግሪ ኦፊሻል ትራንስክሪፕት ከተማራችሁበት ዩኒቨርሲቲ ማስላክ እንደሚጠበቅባችሁ፤
በመንግስት ስፖንሰርሺፕ ስትማሩ የነበራችሁ የክረምት ተማሪዎች የመገጣጣሚያ ደብዳቤ በአሁኑ ሰዓት ከምትሠሩበት ወረዳ ይዛችሁ እንድትመጡ ለማሳሰብ እንወዳለን።
የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ዋናው ሬጅስትራር ፅ/ቤት!

18/07/2026
17/07/2026
16/07/2026

Address

Maytsebri
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when New Line College posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category