06/11/2025
ወርቁ አበበ
በዘመናት ቃንቄ በህይወት ነበልባል
ነጥሮ እየወጣ ታሪኩ ያብባል
መርሣት ያልጋረደው ዳናው ያልተፋቀ
በልጆቹ ልብ ውስጥ ዕውቀቱ የዘለቀ
ምክሩ ከህሊና ተግሣፁ ከአይምሮ
የአባትነት ፍቅሩ ትውልድ አጠንክሮ
ነጥሮ እየወጣ በዘመኑ የስራው
የዘራው መልካም ዘር በክብር እያስጠራው
በዕውቀት ልጆቹ ሰርክ እየታወሰ
መርሣት ሳይጎበኘው እዚህ የደረሰ
እሱ ነው .....ሰውዬው
ወርቁ አበበ ሲባል..ነጥሮ ደምቆ የታየው .!!!
ጋሼ .......መምህሩ
ውለታህ አይረሣም.....!!!!
23/09/2025
የቅዱስ ዮሴፍ ካቶሊክ ት/ቤት--አዳማ የ2011ዓ.ም ባች የቀድሞ ተማሪ ነው ። በተለያየ የሙያ ዘርፍ ተሰማርተው በቀሰሙት ዕውቀት ህዝብንና ሀገራቸውን እያገለገሉ እንደሚገኙ የቀድሞ የሴንጆ ተማሪዎች ሁሉ ኤርሚያስ ለገሠም የሀገር ኩራትና መመኪያ የሆነውን ትልቁን ተቋም መከላከያን በመቀላቀል በሁሩሶ ማስልጠኛ ተገቢውን ስልጠና በመውሰድ በመኮንንነት ተመርቋል። በተጠናቀቀው የህዳሴ ግድባችን ምርቃ ማግስት ለምርቃት የበቁት መኮንኖቹ "የአባይ ዘመን መኮንኖች" የሚል ታሪካዊ ስያሜ በመያዛቸው ም/መ/ አ ኤርሚያስ ለገሠ የዚህ ታሪካዊ አካል ብቻ ሣይሆን የታላቁ ተቋም አባል በመሆንህም ፣ ለዚህ ምረቃ በመብቃትህም እንኳን ደስ አለህ እያልን በታሪካዊው ውጤት እጅግ ኮርተንብሀል ። በቀጣይም በተመደብክበት ሁሉ ሀላፊነትህን በትጋትና በታማኝነት እንደምትወጣ እምነታችን የፀና ነው ።
መልካም የሥራ ዘመን ይሁንልህ !!
02/09/2025
ከሁለት አሥርት አመታት በላይ በመምህርነት ቆይቷል በቅዱስ ዮሴፍ ካቶሊክ ት/ቤት አዳማ-ናዝሬት..ሴንጆ ለዓመታት የአስተማራቸውን የዕውቀት ልጆቹን ሲያስመርቅ ቆይቷል ...ዘንድሮ ነሀሴ28/2017 ዓ.ም ደግሞ የአብራኩ ክፋይ ልጁን እፁብ በድሉን በሀይሌ ሪዞርት አዳማ በተደረገው የሴንጆ ተማሪዎች የምርቃ ፕሮግራም ላይ አስመርቋል ። መምህር እንኳን ደስ አለህ...እፁብ CONVRATULATION..!!!
የቀድሞ የቅዱስ ዮሴፍ ተማሪዎች ማህበርም ለመምህር በድሉ ንጉሴና ..ለእፁብ በድሉ እንዲሁም ለዘንድሮ ተመራቂዎችና ወላጆቻቸው በሙሉ መልካም ምኞቱን ይገልፃል ።
11/06/2025
እንኳን ደሰ አለሽ !!
መልካም ነገር ሁሉ ሲያዩት ደስ ይላል ። የሰው ልጅ በህይወት ዘመኑ ትልቅ ዋጋና ቦታ ከሚሰጠው ዋነኛው ትዳር ነው ። ሮኆቦት ማስረሻ በቅዱስ ዮሴፍ ካቶሊክ ት/ቤት አዳማ--ናዝሬት ከተማሩ በመልካምነት ከሚጠቀሱ ለጥሩ ወጤት ከበቁ አንዷ የ2012 ዓ.ም ባች ናት። የቀድሞ የሴንጆ ተማሪዎች በሚያከናውነው የበጎ ተግባር ሥራ ላይ በትጋት ትሳተፍ የነበረችና ለጋስና ትሁት ልብ የታደላት ሮኆቦት ማስረሻ የከፍተኛ ትምህርቷን ተከታትላ በጥሩ ሁኔታ
ካጠናቀቀች በኋላ እግዜአብሔር በሚወደው ወዳጅ ዘመድ በመኮራበት የቀድሞ መምህራኖቿ በተደሰቱበት መልኩ የጋብቻ ሥነ ስርዓቷን ፈፅማለች። የቀድሞ የናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍ ተማሪዎች ማህበርም በአብሮነት ለነበረን የበጎ አድራጎት ሥራ እያመሠገንን ለዚህ ታላቅ ክብርና የህይወትሽ የደስታ ቀን ፈጣሪ በክብር ስላበቃሽ እንኳን ደስ ያለሽ ማለት እንወዳለን!! ለመላው ቤተሰብ እንኳን ደስ አላችሁ !
ለአንቺም ለትዳር አጋር ባለቤትሽ መልካም ጋብቻ የሠላምና የደስታ የትዳር ዘመን ይንላችሁ !!በማለት መልካም ምኞቱን ይገልፃል ።
እንኳን ደስ አላችሁ !!
30/05/2025
ከቀድሞ የናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍ ተማሪዎች መካከል አንዷ ናት ...የ1982 ዓ.ም ባችዋ ..ክትነሽ አየለ ። የህይወት አጋጣሚ ሆኖ ኑሮዋን በባህር ማዶ በሀገረ አሜሪካ በአትላንታ ከተማ ካደረገች አመታት ተቆጥሯል ታዲያ ይህ የህይወት ጉዞዋ በገጠማት የጤና እክል በህክምና ስትነዳ ብትቆይም May 26/2025 ከዚህ ዓለም ድካም በማረፍ ተጠናቋል። የቀብር ስነ ስርዓቷም ትኖርበት በነበረው አትላንታ ተፈፅሟል። የቀድሞ የናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍ ተማሪዎች ማህበርም በእህታችን ክትነሽ አየለ ህልፈት የተሰማውን ሀዘን እየገለፀ ለመላ ቤተሰቦቿ ለልጇ ፣ አብረዋት ለተማሩ የቀድሞ ተማሪ ጓደኞቿ ለመምህራኖቿና በተለያየ የህይወት አጋጣሚ ለሚያውቋት ወዳጆቿ መፅናናትን እንመኛለን ።
መልካም ዕረፍት !!!
11/05/2025
እንደእናት በፍቅር መክራችሁ፣በግብረገብ አንፃችሁ፣ በሥነምግባር ቀርፃችሁ ለዛሬ መልካም ህይወታችን መሠረት በመጣል በማንነታችን ውስጥ ትልቁን ድርሻና ደማቅ የዕውቀት አሻራችሁን ያሣረፋችሁ የቀድሞ እንስት መምህርቶቻችን እንኳን ለእናቶች ቀን አደረሣችሁ !!!
መልካም የእናቶች ቀን !!
HAPPY MOTHERS DAY !!!
11/05/2025
ክቡር ለሆነውና ለታለቁ የእናትነት ፀጋ ለበቃችሁ ለቀድሞ የናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍ እንስት ተማሪዎች ለዛሬዎቹ እናቶች እንኳን ለእናቶች ቀን አደረሣችሁ !!!
HAAPY MOTHERS DAY !!
20/04/2025
እንኳን አደረሰን ...እንኳን አደረሳችሁ
መልካም የትንሣኤ....የፋሲካ በዓል ይሁንላችሁ !!!
19/03/2025
ለዚህ በጎ ተግባር ቅን ልባቸውን ከከፈቱ ቀኛቸውን ከስጡ የቀድሞ የናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍ ተማሪዎች መካከል ኑሮዋን በሀገረ አሜሪካ ቨርጂኒያ ያደረገችው ኤልሣ ከበደ አንዷ ናት። ጉዳዩን እንደሰማሁ አዝኛለሁ በፀሎት ብቻ ሣይሆን እንደአቅሜ ከወንድማችን ዘዉዱ ታደሠ ጎን መሆን እፈልጋለሁ በማለት ድጋፍ አድርጋለች ። እናመሠግናለን !!!
የሚሰጡ እጆች የተባረኩ ናቸው !!
ONE FOR ALL ALL FOR ONE
09/03/2025
ከበርካታ የናዝሬት ሴንጆ የቀድሞ ተማሪዎች መካከል አንዷ ናት በአሁን ሰዓት ኑሮዋን አውስትራሊያ ሜልቦርን ያደረገችው ሊሻን ከበደ ። ዘዉዱ በገጠመው የጤና እክል ከልብ ማዘኗንና እግዜአብሔር አምላክ እንዲፈውሰው እንደምትፀልይ በመግለፅ አጋርነቷን ድጋፍ በማድረግ ጭምር አሣይታለች።
እናመሠግናለን !!!!
የሚሰጡ እጆች የተባረኩ ናቸው !!
ONE FOR ALL ALL FOR ONE