07/08/2023
የአዳማ ከተማ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት በ2015 ዓ.ም በሥርዓተ ትምህርቱ መሠረት ሲማሩ ለነበሩ የሰንበት ት/ቤት ተማሪዎች በ30/11/2015 ዓ.ም የማጠቃለያ ፈተና ፈተነ።
ይህ ገፅ በአዳማ ከተማ የሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ነው
07/08/2023
የአዳማ ከተማ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት በ2015 ዓ.ም በሥርዓተ ትምህርቱ መሠረት ሲማሩ ለነበሩ የሰንበት ት/ቤት ተማሪዎች በ30/11/2015 ዓ.ም የማጠቃለያ ፈተና ፈተነ።
06/08/2023
+++ ጾመ ማርያም +++
❖
አምላክን በድንግልና የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ባረፈች ጊዜ ሐዋርያት ስጋዋን ለመቅበር ወደ ጌቴ ሴማኒ ይዘው ሲሄዱ ለቅናት የማያርፉት አይሁድ ተነሱባቸው ከዚህ ቀደም ልጇን ሞተ ተነሳ ዐረገ እያለ ሲረብሹ እንደነበር አሁን ደግሞ እሷን ሞተች ተነሳች ዐረገች እያሉ ሊረብሹን አይደለምን ብለው ከተማከሩ በኋላ ሥጋዋን ቀምተው ሊያቃጥሉት ወሰኑ ፡፡
ከዚያም ሥጋዋን ከሐዋርያት ለመቀማት ሲነሱ ታውፋንያ የተባለው የጎበዝ አለቃ ቀድሞ በመድረስ የአልጋውን ሸንኮር በመያዝ ሊጥላት ሲሞክር መልአከ እግዚአብሔር ሁለት እጆቹን ቆረጣቸው ሥጋዋንም ነጥቆ ከሐዋርያው ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር ወደ ገነት ዐረገ ከዚያ በኋላ ሐዋርያት ሥጋዋን አግኝተው ይቀብሩት ዘንድ ባረፈች በስምንተኛው ወር ከነሐሴ 1 ቀን ጀምሮ እስከ 14 ቀን ሁለት ሱባኤ ይዘው በ14ተኛው ቀን ሥጋዋን እንደገና ከጌታ ተቀብለው በጸሎትና በደስታ በጌቴ ሴማኒ አሳረፉት በሦስተኛው ቀን ተነስታ ስታርግ ጥሪው ከሰዱቃውያን ወገን የሆነ ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ አያት ከሌላ ቦታ ሲያስተምር ነበርና በቀብሯ ጊዜ አልተገኘም ነበር፡፡ እርሱም ትንሣኤዋን ከእርሱ የደበቀች መስሎት በፊት የልጅሽን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁ አሁን ደግሞ ያንችን ትንሣኤ ሳላይ ብሎ ከደመና ሊወድቅ ሲል እመቤታችን ከእርሱ በፊት ትንሣኤዋን ያየ ሌላ ሰው እንደሌሌለ ነገረችው ለሐዋርያት ነግሮም ለማስረጃነት እንዲያሳያቸው ሰበኗን ሰጥታው ዐረገች፡፡
ቅዱስ ቶማስም ሐዋርያትን አግኝቶ የእመቤታች ነገር እንዴት ሆነ አላቸው እነሱም አግኝተናት ቀብረናታል አሉት፡፡ ሞት በጥር በነሐሴ መቃብር እንዴት ይሆናል አላቸው እነሱም እንዲያምንላቸው ወደ መቃብሯ ወስደው ሊያሳዩት መቃብሩን ቢከፍቱ አጧት ከዚያም በኋላ ቶማስ እኔስ አታምኑኝም ብየ ነው እንጂ እመቤታችንስ ዐርጋለች ብሎ ሰበኗን ሰጣቸው፡፡ እነርሱም ተከፋፍለው እራሳቸው ላይ አሠሩት በዓመቱ ሐዋርያት ተሰብስበው ቶማስ ትንሣኤሽን አይቶ እኛ እንዴት ይቀርብናል በማለት ሱባኤ ገቡ ከዚያም ልመናቸውን ሰምቶ ሐዋርያትን ወደ ገነት አውጥቶ ከዕፀ ሕይወት መቃብር ሥር እመቤታችንን አስነስቶ አሳይቷቸዋል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንም ይህንን አብነት በማድረግ ጾሙን ከአዋጅ አጽዋማት ውስጥ አስገብታዋለች፡፡ እኛም የእመቤታችንን ምልጃና ጸሎት የሐዋርያት በረከት ይደርሰን ዘንድ ከነሐሴ አንድ ጀምሮ እስከ ዕርገቷ ድረስ እንጾማለን ጾሙን ለመጀመሪያ ጊዜ የጾሙት ቅዱሳን ሐዋርያት ሲሆን የጾሙ መጀመሪያ ነሐሴ 1 ቀን ጀምሮ እስከ ነሐሴ 15 ቀን ነው ፡፡
ከነሐሴ 1 - ነሐሴ 14 የሌሊት ሰዓታት ይቆማል የጠዋት ስብሐተ ነግህ ይደረሳል የውዳሴ ማርያምና የቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ ይተረጎማል ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ቅዳሴ ከሳምንት እስከ ሳምንት አይታጎልም ምናልባት ሊቃውንት የሌሉበት ቤተክርስቲያን ከሆነ ስብሐተ ነግህ ላይቆም ይችል ይሆናል፡፡ የጾመ ፍልሰታ የጾሙ ሰዓት እስከ ዘጠኝ ሰዓት ሰዓት ነው በጾመ ፍልሰታ በተቀደሰው በአባቶቻችን ዘመን የሚያገድፍ ነገር እንኳል ሊበላ ሊጠጣ ቀርቶ ስሙ አይጠራም ነበር፡፡ ለምሳሌ እርጎ ቅቤ ወተትና ሥጋ ብሎ መጥራት የተለያየ ቅጣት ነበረው፡፡ ቅጣቱም እንደ አካባቢው ባሕል ይከናወን ነበር፡፡ አሁንም በአንዳንድ የገጠሪቱ ኢትዮጵያ አካባቢዎች ይህ ትውፊት ይታያል፡፡ የውዳሴ ማርያምና የቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ ከነሀሴ 1 - 14 ይተረጎምና በ15 ኛው ቀን የእመቤታችን ዜና ጽንሰቷ ፡ ዜና እረፍቷና ጸሎተ ሃይማኖት ይተረጎማል፡፡
03/08/2023
በሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አዘጋጅነት ሲሰጥ የነበረው ሥልጠና ተጠናቀቀ።
ሐምሌ 27 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
በሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አዘጋጅነት ሲሰጥ የነበረው የመምህራን አሰልጣኞች ሥልጠና ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ተጠናቋል።
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ባዘጋጀው የአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የአሠልጣኝ መምህራን ሥልጠና ማጠናቀቂያ መርሐ ግብር ላይ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እንዲሁም የተለያዩ መምሪያ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን በቆይታውም የተመራቂ ተማሪዎች የቆይታ ሪፖርት ቀርቦ መምህራኑ ከብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትና ከመምሪያው ኃላፊዎች የምስክር ወረቀታቸውን ተቀብለዋል።
ሠልጣኝ መምህራኑ ከዚህ በኋላ ለሚኖራቸው ሐዋርያዊ አገልገሎት ቤተ ክርስቲያንን በሚፈለገው መጠንና ዘመኑን በዋጀ መልኩ አገልግሎታቸውን እንዲያከናውኑ የማሳሳቢያ መልዕክት ከመምሪያው ኃላፊዎች ተቀበልዋል፤ የማደራጃ መምሪያው ምክትል ሰብሳቢ መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሣኤ እንደተናገሩት "ዛሬ የተሰጣችሁ ከተዘጋጀው ትምህርት በጣም ጥቂት ቢሆንም እናንተ ሥርዓተ ትምህርቱን ጠንክራችሁ ለፍሬ እንዲበቃ ማድረግ አለባችሁ" በማለት አሳስበዋል።
በመጨረሻም የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ ለተመራቂ መምህራኑ በሰጡት የአደራ መልእክት "እናንተ ቤተክርስቲያንን የመጠበቅ ኃላፊነት አለባችሁ አሁን በተማራችሁት ትምህርት ነገ ሌሎች እንዲፈሩ ማድረግ አስፈላጊ ነው፤ እንደነ ቅዱስ ጳውሎስ ለተመረጣችሁበትና ለተሾማችሁበት ወንጌል በመታመን ማገልገል አለባችሁ" ብለዋል።
02/08/2023
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ሐምሌ ሃያ ስድስት በዚች ቀን የእመቤታችን ድንግል ማርያም እጮኛዋ ለጌታችንም አሳዳጊው ለመሆን የተገባው አረፈ፣ ለኢትዮጵያ ሀገር ብርሃንን የገለጠ ቅዱስ አባት አረፈ።
27/07/2023
እንድትገኙ ተጋብዛችኋል ።
27/07/2023
የና/ደ/ሰ/ፈ/ሰ/ዘመላእክት ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል ሰ/ት/ቤት የሐምሌ 19 ዓመታዊ በዓል አከባባር ።
25/07/2023
ወደ ጋኑ ውስጥ በገቡ ጊዜ ቅዱስ ገብርኤል የውኃውን ፍላት እንደ ንጋት ውርጭ አቀዘቀዘው፤ ይህም በሐምሌ ፲፱ ቀን ነበር፡፡
*****************************************************************************************************
ሕፃኑ ቂርቆስ ገና የሦስት ዓመት ብላቴና ሳለ እናቱ ኢየሉጣ ከሮሜ አገር የኪልቂያ አውራጃ ከሆነች ጠርሴስ ወደ ምትባል አገር ይዛው ሸሸች። በዚያም የሸሸችውን መኮንን እለእስክንድሮስን አገኘችው። መኮንኑም ኢየሉጣን አጥብቆ መረመራት። “ስምሽ ማን ነው? አገርሽ ከወዴት ነው?” አላት። እርሷም “ስሜ ክርስቲያን ነው” በማለት መለሰችለት።
መኮንኑም ቅዱስ ቂርቆስ መልኩ የሚያምርና ደም ግባት ያለው ለሕፃን እንደሆነ ባየ ጊዜ “ደስ የምትል ደስተኛ ሕፃን ሰላምታ ይገባሃል” አለው። ሕፃኑ ቂርቆስም “እኔን ደስተኛ ማለትህ እውነት ተናገርክ፤ ለአንተ ግን ደስታ የለህም” አለው። “መኮንኑም “ስምህ ማን ነው?” የሚል ጥያቄ ሲጠይቀው እንዲህ አለ፤ “እኔ ክርስቲያን ነኝ” አለ፡፡
ከዚህ በኋላ መኮንኑ አፈረና ጽኑ ሥቃይ ሊያሠቃያቸው ወድዶ እንደ ክረምት ነጎድጓድ ድምፅ ወደ ሚያስተጋባው የፈላ ውኃ እንዲጥሏቸው አዘዘ፤ ያን ጊዜ እናቱ ፈራች፤ ሕፃኑ ግን ለእናቱ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፤ እንዲህም አላት፤ “እናቴ ሆይ አትፍሪ! ጨክኝ፤ አናንያ አዛርያ ሚሳኤልን ያዳነ አምላክ እኛንም ያድነናል” አላት። እናቱ ቀና ብላ ብትመለከት ለቅዱሳን ሰማዕታት የተዘጋጁትን የብርሃን ማደርያቸውን ተመለከተች፤ ደስም ተሰኝታ እንዲህ አለች፤ “ልጄ ሆይ ከእንግዲህ አባቴ ነህ፤ እኔም ልጅህ ነኝ፤ አንተን የወለድኩባት ቀን የተባረከች ናት፡፡
ሕፃኑ ከእናቱ ጋር ወደ ፈላው እሳት ተጣለ። ያን ጊዜ የአካላዊ ቃልን ሰው የመሆን የምሥራች የተናገረ፣ የይቅርታና የቸርነት አማላጅ፣ ነቢያት በትንቢታቸው “ይወርዳል ይወለዳል” የተናገሩት፣ ትንቢታቸው መፈጸሙንም የምሥራች ቃል በመናገር ለዓለሙ ሁሉ ደስታ የሆነ፣ የጨለማ አበጋዝ በሚሆን በሰይጣን ተንኮል ከእፉኝት መርዝ የሚከፋ በሰው ልቡና ውስጥ አድሮ የነበረውን የኀዘን ስሜት ያጠፋ፣ በሰይጣን የተንኮል ቃል በዓለም ላይ የተዘረጋው የጨለማ መጋረጃ በምሥራች ቃል በዓለሙ ሁሉ የሕይወት ብርሃን ያበራ ቅዱስ ገብርኤል ወደ ጋኑ ውስጥ በገቡ ጊዜ የውኃውን ፍላት እንደ ንጋት ውርጭ አቀዘቀዘው፤ ይህም በከበረች በሐምሌ ፲፱ ቀን ነበር፡፡
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ የቅዱስ ገብርኤል አማላጅነትና ተረዳኢነት አይለየን፤ በቅዱስ ቂርቆስና በቅድስት ኢየሉጣ ጸሎት ይማረን፤ በረከታቸው ይድረሰን፤ ለዘለዓለሙ አሜን!!!
ስንክሳር ዘወርኀ ሐምሌ እና ድርሳነ ገብርኤል፡፡
24/07/2023
በትግራይ በተከናወነው የሕገ ወጥ ኤጲስ ቆጶሳት ሹመት አስመልክቶ ቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ለሐምሌ 25/2015 ዓ.ም ምልዐተ ጉባኤ ጠራ።
22/07/2023
22/07/2023
ከአዳማ ከተማ የመንበረ ጵጵስና ሰ/ት/ቤቶች አንድነት የተውጣጡ :በማኅበረ ቅዱሳን የአዳማ ማዕከል አስተባባሪነት ለሚሰጠው የኦሮምኛ (Afaan Oromo) የደረጃ 1-ተተኪ መምህራን ስልጠና የሚሳተፉ 20 ወንድሞች :በዛሬው ዕለት ወደ ስልጠና የገቡ ሲሆን በአንድነቱ እና በማዕከሉ ተወካዮች አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
15/11/2015 ዓ.ም
አዳማ ኢትዮጵያ ።
19/07/2023
" ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ።" ዳን ፲፥፲፫
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
እንኳን ለቅዱስ ሚካኤል ወርሃዊ በዓል አደረሰን አደረሳችሁ። የቅዱስ ሚካኤል ተራዳይነት አይለየን።