06/07/2026
የታላቋን ሀገር #በጂኦግራፊእስርቤት መቆየት የማይፈቅደው
#የቀይባሕርትውልድ
---
ኢትዮጵያ በዓለም ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ከ130 ሚሊዮን በላይ የሚሆን እጅግ ሰፊ ሕዝብ ይዛ የባሕር በር አልባ ሆና እንድትቀጥል የተፈረደባት ብቸኛ ሀገር ናት።
ይህ ታሪካዊ ኢ-ፍትሐዊነት ትውልዱ ላይ ጥልቅ ቁጭት እና የሕልውና ጥያቄ የፈጠረ እና ምላሽ የሚሻ ነው።
ከቅድመ አክሱም ዘመን ጀምሮ እስከ 1985 ዓ.ም ድረስ ኢትዮጵያን እና ቀይ ባሕር ተነጣጥለው አያውቁም።
ከ1985 ዓ.ም እስከ 'መደመር ትውልድ' መነሣት ድረስ ያለው ትውልድ ግን በታሪክ "የሥነ-ልቦና ስብራት" ዘመን ተብሎ የሚታወቅበትን የባዶነት እና የቁጭት ጊዜ አሳልፏል።
በወቅቱ ሥልጣንን የተቆጣጠሩት ኃይሎች ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር ተመሳጥረው ታሪኩን የነጠቁት ያ ትውልድ፣ የባሕር በር ማጣትን እንደማይቀየር ቋሚ ዕጣ ፈንታ በመቁጠር ሲብሰለሰል ኖሯል።
ከ12 በመቶ በላይ የሚሆነው የዓለም የንግድ እንቅስቃሴ የሚተላለፍበትን እና በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኘውን ቀይ ባሕርን ዝም ብሎ ማየት ያንገፈገፈው "የመደመር ትውልድ" ዛሬ ተፈጥሯል።
የመደመር ትውልድ ከ60 በመቶ በላይ የሚሆነውን አምራች እና ወጣት ሕዝብ የሚወክለው የቀይ ባሕር ትውልድ ነው።
ይህ ትውልድ የባሕር በር አልባነትን እንደ ቋሚ ዕጣ ፈንታ ሳይሆን እንደ ታሪካዊ እና ሕጋዊ ስህተት ይመለከተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት እንደገለጹት፣ በ2050 ዓ.ም የሕዝብ ብዛቷ ወደ 150 ሚሊዮን ተብሎ የምትገመተዋ ታላቅ ሀገር መተንፈሻ አልባ ሆና መቀጠል አትችልም።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ደጋግመው እንደገለጹት ይህን ያህል ግዙፍ ሕዝብ ያላትን ሀገር በጂኦግራፊያዊ እስር ቤት ውስጥ አስገብቶ ለቀጣዩ ትውልድ ማውረስ የታሪክ ባለእዳነት ነው።
የቀይ ባሕር ትውልድ ታሪክን የማረም እና የታላቋን ኢትዮጵያን ትክክለኛ የጂኦግራፊ እና የኢኮኖሚ ስፍራ የመመለስ ታሪካዊ አደራ ወድቆበታል።
ይህ ትውልድ የባሕር በር ጥያቄ የፖለቲካ ቅንጦት ሳይሆን፣ የ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ሕልውና እና የዕድገት መሠረት መሆኑን በሚገባ የተገነዘበ ጠንካራ ሥነ-ልቦና አለው።
የቀይ ባሕር ትውልድ ታሪካዊ ስህተቶችን ለማረም የሚንቀሳቀሰው በጦርነት አዙሪት ሳይሆን፣ በጋራ ተጠቃሚነት፣ በኢኮኖሚያዊ ውህደት እና በብልህ የፓን-አፍሪካኒዝም ዲፕሎማሲ ነው።
ትውልዱ ኢትዮጵያ የምትገነባቸውን ግዙፍ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች ከቀይ ባሕር ጂኦ-ፖለቲካዊ ስትራቴጂ ጋር በማስተሳሰር፣ ቀጣናውን የጋራ ብልጽግና ማዕከል ለማድረግ ይተጋል።
#ቀይባሕር
05/24/2026
“It's not done...አላለቀም!”
ሻምፒዮኑ የዴክላን ራይስ ቃል
---
እዚሁ ያገኘሁት
---
ሕይወት እንዲህ ይቀጥላል!
ቃላት በሰው ልብ ውስጥ ሀያል ናቸው። ቃል ያፈርሳል፤ ደግሞ ሰውን ከወደቀበት አንስቶ የማይቻል የተባለውን እውን ያደርጋል። በአርሰናል ቤት የሆነውም ይህ ነው!
ባለፉት ሳምንታት አርሰናል በተለይም በቦርንመዝና በማንቸስተር ሲቲ ተረቶ፣ ተስፋ ቆርጦና አንገቱን ደፍቶ በነበረበት በዚያ በፈተና ወቅት... አይደክሜው የቡድኑ ሁለገብ ተጫዋች ዴክላን ራይስ የቡድን አጋሮቹን የልብ ስብራት ተመልክቶ በታላቅ ወኔ ጮኸ። “Hey... It's not done!” አላለቀም!” አለ💪
“..አላለቀም” ቀላል ትመስል ነበር። ነገር ግን በውስጧ ፅናት፣ ትዕግስት፣ ራስን ማመንና እስከመጨረሻው የመታገል አይበገሬነትን የያዘች የውስጥ እሳት ነበረች። የምትፋጅ🔥
“It's not done” የሚለው የራይስ መሪነትና ቃል በፈጠረው ተአምር አርሰናል ሽንፈቱን ጠግኖ፣ ጎል ሳይቆጠርበት ተከታታይ ድሎችን አስመዝግቦ ወደ ስኬት ማማው ተመለሰ።
መመለስ ብቻ አልነበረም ከ22 አመታት በኋላ የእንግሊዝ ሻምፒዮንም ሆነ 🏆
የራይስ ንግግር በታሪክ ውስጥ ስማቸው ከደመቀ ታላላቅ ሰዎች ሃሳብ ጋር ተሰልፏል፡፡👇
ከኔልሰን ማንዴላ፦
“It always seems impossible Until it's done - እስኪሳካ ድረስ ሁሉም ነገር የማይቻል ይመስላል” ፣
ከቤዝ ቦሉ ዮጊ ቤራ፦ “It ain’t over till it’s over! እስኪያልቅ ድረስ አያልቅም”
ከዊንስተን ቸርችል፦ Success is not final, failur is not fatal, It is the courage to continue that counts - ስኬት መጨረሻ አይደለም፤ ውድቀትም ጥፋት አይደለም፤ ዋናው ነገር ትግሉን የመቀጠል ድፍረቱ ነው” ከሚሉ ታሪካዊ ንግግሮች እንደ አንዱ ሆኗል፡፡
“It's not done ” ከእግር ኳስ በላይ... ለሕይወታችን!
ሰው በሚደክምበት ጊዜ ጡንቻው ብቻ ሳይሆን መንፈሱም ይደክማል። ዛሬ በዓለማችን ላይ ብዙ የተሰበሩ ልቦችና ተስፋ የቆረጡ ነፍሳት አሉ። እነዚህ ሁሉ የሚፈልጉት ገንዘብ ብቻ አይደለም።
የሚያነሳና የሚያበረታታ ትክክለኛ ቃል እንጂ!
“አልችልም” የሚል ሰው መንገዱን በራሱ ይዘጋል።
“እሞክራለሁ” የሚል ግን ለራሱ የስኬት በር ይከፍታል።
ያጋጠመህ ውድቀት እንጂ የሕይወትህ ጉዞ ገና አላለቀም! ሕልምህ አልሞተም፣ ተስፋህም አልደበዘዘም።
በአርሰናል ቤት “It's not done” ወደ “Done” ተቀይሮ ዋንጫው እንደተሳመ ሁሉ... አንተም በሕይወትህ ድል ታደርጋለህ!
05/04/2026
ከረባት መሳዩ የሸፍጥ መዝጊያ እና የኔትውልድ የቤትስራ
-----
የምቀኛ ሰፈር ልጅ እና የስልጣን ጥማት ያነወረው ብሔራዊ ክህደት ፤ድንበር ማካለል "ኧረ ውይይይይ" ያሰኛል።
💀
ለኢትዮጵያ የባህር በር ባለመኖሩ ምክንያት የምትከፍለው ዋጋ ከቀጥታ ክፍያ በላይ የኢኮኖሚዋ ማነቆ ብቻ ሆኖ ሳይሆን ዘላለማዊ ሃገር እና ትውልድን መግደል ነው።
1. የቀጥታ የወደብ አገልግሎት ወጪዎች (Direct Costs)
ኢትዮጵያ የጅቡቲን ወደብ ስትጠቀም በየቀኑ እና በየወሩ የምትከፍላቸው የተለያዩ ክፍያዎች አሉ።
እነዚህም፦
ሀ. የመርከብ ማቆሚያና የማራገፊያ ክፍያ ፤ (Stevedoring & Shore Handling) ዕቃዎች ከመረከብ ላይ ወርደው መሬት እስኪያርፉ የሚከፈል ከፍተኛ ዶላር።
ለ. የኮንቴይነር መቆያ (Demurrage):
ዕቃዎች በወቅቱ ከወደብ ካልወጡ በየቀኑ የሚታሰብ ቅጣት። ይህ ክፍያ ብቻውን በየዓመቱ በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር ይፈጃል።
ሐ. የወኪል አገልግሎቶች (Forwarding Fees):
በጅቡቲ በኩል ለሚሰሩ የጉምሩክና የትራንዚት ወኪሎች የሚከፈል ክፍያ።
2. የሎጂስቲክስና የትራንስፖርት ውስብስብነት (Logistics Burden) የባህር በር አለመኖር የንግድ ሰንሰለቱን ረጅም እና ውድ ያደርገዋል።
መ. የመንገድ ትራንስፖርት ጥገኝነት:-
ወደ 95% የሚሆነው የሀገሪቱ ንግድ በጅቡቲ ኮሪደር ላይ የተንጠለጠለ ነው። ይህም ለመንገድ ጥገና፣ ለነዳጅ እና ለከባድ መኪናዎች መለዋወጫ የሚወጣውን የውጭ ምንዛሬ ያንረዋል።
ሠ. የጊዜ መባከን:-
ዕቃዎች ከወደብ ተነስተው አዲስ አበባ እስኪገቡ ያለው ረጅም ጊዜ የንግድ እንቅስቃሴውን (Inventory turnover) ያቀዘቅዘዋል። ይህም ነጋዴዎች ባላቸው ካፒታል ብዙ ጊዜ ደጋግመው እንዳይነግዱ ያደርጋቸዋል።
3. በኢንዱስትሪና ግብርና ላይ የሚኖረው ተጽዕኖ
ረ. የግብርና ግብዓቶች ዋጋ መጨመር:-
ማዳበሪያና ኬሚካሎች በወቅቱና በዝቅተኛ ዋጋ አለመግባት በምርታማነት ላይ ተጽዕኖ ያሳድራል።
ሰ. የወጪ ንግድ ተወዳዳሪነት:-
ለምሳሌ አንድ የኢትዮጵያ ምርት (እንደ ቡና ወይም ጨርቃጨርቅ) የአውሮፓ ገበያ ላይ ሲደርስ፣ ከባህር በር ክፍያና ከትራንስፖርት ውድነት የተነሳ ዋጋው ይጨምራል። ይህም የባህር በር ካላቸው ሀገራት ጋር ለመወዳደር አስቸጋሪ ያደርገዋል።
4. ስልታዊና ጂኦፖለቲካዊ ተጽዕኖ (Strategic Risks)
ሸ. የአንድ አማራጭ ስጋት፦
ሀገሪቱ በአንድ ወደብ ላይ ብቻ ጥገኛ መሆኗ ለብሔራዊ ደህንነትና ለኢኮኖሚው ስጋት ነው። በወደቡ ላይ የሚፈጠር ማንኛውም መስተጓጎል (የሰራተኞች አድማ፣ የቴክኒክ ብልሽት ወይም ፖለቲካዊ አለመረጋጋት) የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ሙሉ በሙሉ ሊያቆመው ይችላል።
ቀ. የውጭ ምንዛሬ እጥረት፦
በየዓመቱ የሚከፈለው ከ3 እስከ 4 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ በቀጥታ ከሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ላይ የሚቀነስ በመሆኑ፣ ለሌሎች የልማት ስራዎች (ለፋብሪካዎች ጥሬ ዕቃና ለመድኃኒት ግዢ) የሚውለውን የገንዘብ መጠን ያጥባል።
5. "Landlocked" የመሆን የስነ-ልቦና እና የኢንቨስትመንት ተጽዕኖ
ብዙ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ኢንቨስት ሲያደርጉ "የባህር በር የላትም" የሚለውን እንደ ትልቅ አደጋ (Risk) ይቆጥሩታል። ይህም ቀጥተኛ የውጭ ኢንቨስትመንት (FDI) በከፍተኛ ሁኔታ እንዳያድግ እና እንዳይስፋፋ እንቅፋት ይሆናል።
በአጠቃላይ በእነዚህ እና ሌሎች ተጨማሪ ምክንያቶች የባህር በር አለመኖር ለኢትዮጵያ "የድህነት ግብር" (Tax on development) እንደመክፈል ይቆጠራል።
ይህ የተቀነባበረ ችግር ካልተቀረፈ የሀገሪቱ ለእድገት ለምታደርገው ጉዞ ሁሌም ፈታኝ ሆኖ ይቀጥላል።
---
ቀይባሕር ለኢትዮጵያ -ኢትዮጵያ የቀይባሕር ‼️
#አሰብ
#ቀይባሕር
#ቀይባሕርለኢትዮጵያ
#ኢትዮጵያየቀይባሕር
04/22/2026
ሕልመኛው ታዳጊ
ገና በልጅነቱ በሰማይ የሚበሩ አውሮኘላኖችን ሲመለከት ትኩረቱን ይስቡት ነበር። ወላጆቹን ስለ አውሮኘላኖች አዘውትሮ ይጠይቅም እንደነበር ይናገራል። ከጥያቄ አልፎ ግን ያለውን ተሰጥኦ ከሰፈር የሚያገኛቸውን የወዳደቁ ዕቃዎችን በመጠቀም የፈጠራ ክህሎቱን "ሀ" ብሎ ጀመረ፤ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኤሮ ስፔስ ኢንጅነሪንግ የሁለተኛ ዓመት ተማሪው አማኑኤል መኳንንት።
በየቀኑ እየጠየቀ የሚያገኘውን ምላሽ ወደ ተግባር በመለወጥ በካርቶን አውሮፕላን አስመስሎ በመሥራት ሕልሙን ዕውን የማድረግ ሥራውን ጀምሯል። ከዚያም የባትሪ ድንጋይ በመጠቀም የሚንቀሳቀስ መኪና የሚመስል ትንሽ ሞዴል ፈጠራ መሥራቱን ነግሮናል።
እያደገ ሲመጣ ከትምህርቱ ጎን ለጎን መረጃዎችን ከዩቲዩብ በመሠብሠብ ክህሎቱን ማሳደጉን ገልጾልናል። ፈጠራውንም አስቀጥሏል።
በወቅቱ ግን የፈጠራ ሥራውን መስሪያ ቁሳቁስ ለመግዛት ገንዘብ እንዳልነበረው አውስቷል። ከዚያም በትርፍ ሰዓቱ የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ ጥገና ሥራዎችን በመሥራት ገንዘብ ማግኘቱን የሚናገረው ተማሪ አማኑኤል ባገኘው ገንዘብ መስሪያ ቁሳቁስ በመግዛት በሪሞት የሚንቀሳቀስ አውሮፕላን የፈጠራ ውጤትን ዕውን አድርጓል።
ከብዙ ጥረት በኋላ አኹን ላይ የልጅነት ሕልሙ እያደገ በሪሞት የሚንቀሳቀሱ ሰው አልባ አውሮኘላኖችን እየሠራ የፈጠራ ሥራውን እያሳደገ ይገኛል።
በፈጠራ ሥራውም ከተለያዩ ተቋማት ዕውቅና ማግኘቱን ገልጿል። ባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ በሚያደርግለት እገዛም የተሻሉ የፈጠራ ሥራዎች እየሠራ መኾኑን ተናግሯል። የወላጆቹ ድጋፍ ከፍተኛ መኾኑን የሚገልጸው ተማሪ አማኑኤል "አኹንም የማሳካው ሕልም አለኝ" ይላል።
ለወደፊትም የፈጠራ ተሰጥኦ ያላቸውን ልጆች ለማበረታታት፤ በግብርናው ዘርፍ ለኬሚካል ርጭት የሚያገለግሉ በሪሞት የሚንቀሳቀሱ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን በመሥራት ወደ ገበያ ለማቅረብ አልሟል። ይህ ደግሞ የአርሶ አደሮች ጊዜ፣ ገንዘብ፣ ጉልበትን ለመቆጠብ እና ጤንነቱን ለመጠበቅ ድርሻው የጎላ እንደሚኾን ነው የተናገረው።
ለአብነት ተማሪ አማኑኤልን አነሳን እንጂ በተለያዪ ዘርፎች በርካታ ሕልም ያላቸው ታዳጊዎች አሉ። እነዚህ ታዳጊዎች የሀገሪቱን ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ዕውን ለማድረግ ተስፋ ተጥሎባቸዋል። እንደነዚህ አይነት የፈጠራ ሥራዎች ወደ ተግባር እንዲለወጡ ማድረግ እንደሚገባም ተማሪ አማኑኤል ተናግሯል።
የፈጠራ ሥራዎች የማኅበረሰቡን ችግር ቀላል እንዲያደርጉ የሚመለከተው አካል የሚያደርገውን ክትትል እና ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቋል።
አሚኮ
04/21/2026
ለሰላም የሚዘረጋ እጅ የጥንካሬ፣ የጥበብ እና የብልህነት ምልክት ነው።
ለሰላም እጅን መዘርጋት ብልህነት ብቻ ሳይሆን የሞራል ልዕልና እና ጥንካሬም ጭምር መሆኑን ታሪክ ደጋግሞ ያወሳል።
ሰላም የጥበበኞች የእውነት እና የጋራ አሸናፊነት መሣሪያም ነው፡፡እውነተኛ አሸናፊነትም የሚመጣው በሰላም ብቻ ነው።
በሰላማዊ መንገድ የተገኘ ድል ደግሞ ዘላቂነት ይኖረዋል፡፡ በመሆኑም “ምክንያታዊ” ሆነን ሰላምንና የሰላምን መንገድ መውሰድ አማራጭ የሌለው መሆኑን ያሳየናል።
Sibuh Gebeyaw Tareke
04/21/2026
ዓለምን በሚበይነው የዲጂታል ዘርፍ ሪፎርም የተገኙ ቁልፍ ውጤቶች:-
• መሰረተ-ልማት-
የ5G እና የ4G ሽፋን መስፋፋት።
• የዲጂታል መሳሪያዎች-
ስማርት ስልኮችን በሀገር ውስጥ መገጣጠም።
• ዲጂታል መንግስት-
በመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት 2260 አገልግሎቶች በአንድ ቋት መደራጀት፣ ዲጂታል ክፍያዎች፣ የፍትህ ተደራሽ ስማርት ችሎት እና ዲጂታል ፖሊስ።
• ዲጂታል ክህሎት-
5 ሚሊዮን ኮደሮች ስልጠና፣ ትምህርት ቤቶችን በኢንተርኔት (SchoolNet)፣ በሶስተኛ ዲግሪ (PhD) ደረጃ የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ምርምር እና ስታርት አፖችን በእውቀትና በፈጠራ ማብቃት።
• የተቋማት ግንባታ-
ዲጂታል ስታቲስቲክስ እና ልማት አስተዳደር፣ AI ኢንስቲትዩት፣ AI ዩኒቨርሲቲ እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር።
• የህግ ማዕቀፍ ተዓማኒነት-
በፋይዳ መታወቂያ ከ40.9 ሚሊዮን በላይ ዜጋ ተካቷል፣ የግል መረጃ ጥበቃ አዋጅ፣ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ እና የኤሌክትሮኒክ ፊርማ ተግባራዊነት።
Key Achievements in the World-Defining Digital Sector Reform
• Connectivity
Infrastructure: Expansion of 5G and 4G network coverage.
Digital Devices: Domestic assembly of smartphones.
• Digital Government
2,260 services integrated into a single platform via 'Mesob', digital payments, accessible justice through smart courts, and digital policing.
• Digital Skills
The "5 Million Ethiopian Coders" initiative, connecting schools to the internet (SchoolNet), PhD-level Artificial Intelligence (AI) research, and creating a conducive environment for startups.
• Institution Building
Establishment of the Digital Statistics and Development Administration, Artificial Intelligence (AI) Institute, AI University, and the Information Network Security Administration (INSA).
• Legal Framework & Reliability
Fayda (National Digital ID) reaching 40.9 million+ citizens, Personal Data Protection Proclamation, the Digital Ethiopia 2030 Strategy, and the implementation of Electronic Signatures.
04/21/2026
ዛሬ የመሬት ቀን ነው!ስሙትማ👇
"ከመሬትስ ጋራ ታረቀነ በመላ
ፊት እኛ በልተነው ኋላ እሱ ሊበላ"
አዝማሪ አበበ መብሬ 'መሬትን' በአግባቡ የገለጸ ሰው ‼️
https://www.tiktok.com//video/7631161337434901768
https://www.tiktok.com//video/7631161337434901768
TikTok · Gulilat Geletaw
Check out Gulilat Geletaw’s video.
04/19/2026
መቼም ቢሆን ✅ መድፈኛው🔍
መሸፈኛው እንጂ መድፈኛው አይበገርም‼️
---
Gunners Never Giveup 💪
---
አለመበሳጨትህን -ባለመበሳጨትህ ውስጥ ጥራው😢
Always Gunners .