Bekafa Seventh Day adventist church

Bekafa Seventh Day adventist church

Share

“ወደ ሕይወት ዛፍ ለመድረስ ሥልጣን እንዲኖራቸው በደጆችዋም

12/06/2023
30/12/2022

የአይሁድ ሕዝብ ከአንድ ሺህ ዓመታት በላይ የመድህንን መምጣት ሲጠባበቁ ቆዩ። ያ ወቅት የተስፋቸው መደምደሚያ ነበር። በመዝሙር፣ በትንቢት፣ በቤተ መቅደስ ሥርዓተ ማሕሌትና በቤተሰብ ጸሎትም ስሙ ተከብሮ ነበር። ነገር ግን በመጣ ጊዜ አላወ ቁትም። የሰማዩ ተፈቃሪ በእነርሱ ዘንድ «እንደ ቡቃያ ከደረቅ መሬት እንደ ሥር አድጐአል። መልክና ውበት የለውም። ባየነውም ጊዜ እንወደው ዘንድ ደም ግባት የለውም።» «ወደ ወገኖቹ መጣ፤ ወገኖቹም አልተቀበሉትም»። ኢሳ53:2፣ ዮሐ1:11።
አይሁድ ስለ መሲህ መምጣት ቢመኙም ስለ ሥራው ግን በቂ ግንዛቤ አልነበራቸውም። ከሮማዉያን አገዛዝ ነጻ ለመውጣት እንጂ ከኃጢአት ለመዳን አልፈለጉም።
አይሁዶች ከሥርዓተ አገልግሎታቸው መንፈሳዊ ሕይወትን አላገኙምህ ይዘት የሌለው ቅርጻዊ አገልግሎትን የሙጥኝ አሉ። ሥርዓተ አገልግሎቱ በሚያመለክተው ላይ ከማተኮር ፋንታ በአገልግሎቱ ሥርዓት ላይ አተኮሩ። ካህናትና ጸሐፊዎች ያጡትን ደረጃ ለመተካት ሲሉ የራሳቸውን ብዙ መመሪያዎች አወጡ፤ አቋማቸውን እያከረሩ እንደ ሔዱ መጠን የእግዚአብሔር ፍቅር መግለጫ እየቀነሰ መጣ። የቅድስናቸው መለኪያ የአገልግሎታቸው ብዛት ሆነ፤ ልባቸውም በትእቢትና በግብዝነት ተወጠረ።

21/09/2022

በካፋ 7ተኛ ቀን አድቨንቲስት ቤተ-ክርስቲያን
ጃንተስ መዘምራን : ዘላለም ህያዉ ነህ!

https://fb.watch/fGKB4VXDZF/

21/09/2022

ልዩ ፕሮግራም በበካፋ 7ተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተ-ክርስትያን!

15/04/2022

መልካም ሰንበት ዝግጅት ::

“ኢየሱስም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ፦ ተፈጸመ አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ።”
— ዮሐንስ 19፥30
ተፈጸመ አለና አንገቱን ደፍቶ መንፈሱን ሰጠ።

ደቀ መዛሙርቱ ኢየሱስ “ተፈጸመ” ብሎ ሲጮኽ ተመለከቱ። ነገር ግን የተጠናቀቀው የኢየሱስ ሕይወት አልነበረም—ከእግዚአብሔር ፍቅር የሚለየን ሁሉም ነገር ነበር።

እኛን ለማዳን ነፍሱን አሳልፎ በመስጠት “እግዚአብሔር ከእኛ ጋር” ሆነ።

ኢየሱስ መከራን የተቀበለው በእኛ መከራ የሚሠቃይ ዓለማችን እግዚአብሔርን በግል እንዲያውቅ ነው።

በመስቀል ላይ የተሰቀለው እና እኛን ለማዳን ሁሉንም ነገር የሰጠ ፍቅር ነው። "ተፈፅሞል " የድል ጩኸት ነበር, ምክንያቱም እኛን በምርኮ ያቆዩንን ሁሉ አሸንፈናል ::

18/12/2021

መዝሙር 147
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ሃሌ ሉያ። አምላካችንን በመዝሙር ማወደስ እንዴት መልካም ነው፤ እርሱን ማመስገን ደስ ያሰኛል፤ ይህ ተገቢም ነው።
² እግዚአብሔር ኢየሩሳሌምን መልሶ ይሠራታል፤ ከእስራኤል የተበተኑትን ይሰበስባል።
³ ልባቸው የተሰበረውን ይፈውሳል፤ ቍስላቸውንም ይጠግናል።
⁴ የከዋክብትን ብዛት ያውቃል፤ እያንዳንዱንም በስሙ ይጠራዋል።
⁵ ጌታችን ታላቅ ነው፤ እጅግ ኀያልም ነው፤ ለጥበቡም ወሰን የለውም።

10/12/2021

መልካም ሰንበት ይሁንላችሁ 🙏

ተስፋ ቆርጣችሁኃል?

አንተን ተስፋ የሚያደርጉ፣ ከቶ አያፍሩምመዝ 25፡3
እርሱን ተስፋ ለሚያደርጉት፣ ለሚፈልገውም ሰው እግዚአብሔር መልካም ነው፡፡ ሰው የእግዚአብሔርን ማዳን ዝም ብሎ ተስፋ ቢያደርግ መልካም ነው፡፡ለቆ ኤር 3፡25-26
ነፍስን ተስፋ ማስቆረጥ የሰይጣን ስራ ነው ፤ በተስፋና በእምነት መሙላት ደግሞ የክርስቶስ ተግባር ነው፡፡
ሰይጣን ከእግዚአብሔር የተቀበልነውን የተባረከ ዋስትና ሊዘርፈን ሁልጊዜ ዝግጁ ነው፡፡ ማንኛውንም የተስፋ ጭላንጭል ሊያጠፋ ይሻል፤ ነገር ግን ይህንን እንዲያደርግ ልትፈቅዱላት አይገባም፡፡ እምነትን ተለማመዱ ፤ የእምነትንም መልካሙን ገድል ተጋደሉ፤ ከእነዚህ ጥርጣሬዎች ጋር ተፋለሙ ፤ ከጌታ የተስፋ ቃሎች ጋር ራሳችሁን አስተዋውቁ፡፡
አንተ ባዘጋጀህልን በጠባቡ መንገድ መሄድ እንድንችል እርዳን :: አሜን!

25/08/2021

የሺኖ ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተ-ክርስቲያን ናታኒም መዘምራን መዝሙር ነሐሴ 29 /2013 ይመረቃል : :

11/12/2020

ምሳሌ8
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁴ የሚሰማኝ ሰው ምስጉን ነው ዕለት ዕለት በቤቴ መግቢያ የሚተጋ፥ የደጄንም መድረክ የሚጠብቅ።
³⁵ እኔን ያገኘ ሕይወትን ያገኛልና፥ ከእግዚአብሔርም ሞገስን ያገኛልና።
³⁶ እኔን ያጣ ግን ራሱን ይጐዳል፤ የሚጠሉኝ ሁሉ ሞትን ይወድዳሉ።
መልካም ሰንበት

05/06/2020

📖 አጥሩ ላይ ነኝ 📖

በርካታ ቁጥር ያላቸው ሰዎች ተሰብስበው ነበር። በአንድ ቡድን በኩል አንድ ሰው ቆሟል ፤ ክርስቶስ ፣ በሌላኛው በኩል ደግሞ ሌላ ፤ሰይጣን። ሁለቱን ቡድኖች የሚለይ ደግሞ አጥር ተዘርግቷል። ይህ ተሰናድቶ እያለ ክርስቶስም ሰይጣንም ወደየቡድናቸው ሰዎችን መጥራት ጀመሩ። አንድ በአንድ ሁሉም በራሱ ውሳኔ ወይ ወደ ክርስቶስ ፤ ወይ ወደ ሰይጣን መሄድ ጀመረ። ይህ ለተወሰነ ጊዜ ከቀጠለ ብኋላ በበቂ ጊዜ ውስጥ በዛ ካለው ህዝብ ውስጥ ክርስቶስ በራሱ ዙሪያ ሰዎችን ሰበሰበ፤ ሰይጣንም እንዲሁ።

አንድ ሰው ግን ከሁለቱም አልተቀላቀለም። በሁለቱ መሃል በተሰራው አጥር ላይ ተንጠላጥሎ ቁጭ አለ። ክርስቶስና የእርሱ ቡድን ሰዎች ሄዱ ከቦታውም አልተገኙም፤ ሰይጣንም እንዲሁ ከነህዝቡ ሄደ። በአጥሩ ላይ ያለው ሰው ግን ብቻውን ተቀመጠ። ይህ ሰው ብቻውን ተቀምጦ እያለ ሰይጣን የረሳውን ነገር እንደሚፈልግ አይነት ሆኖ ተመልሶ መጣ ፤

ሰውየውም “የረሳኸው ነገር አለ?” ሲል ሰይጣንን ጠየቀው፣…

ሰይጣን ፊትለፊት እሱን እያየ “አይ፤ ይኸው አገኘሁት ና ከእኔ ጋር” አለው።

ሰውየው ግራ በመጋባት “ግን እኔ እኮ አጥር ላይ ነው የተቀመጥኩት እንጂ ከሁለት አንዳችሁንም አልመረጥኩም” ሲል መለሰ፤

ሰይጣንም መልሶ “ግድ የለም ና፤ አጥሩም የእኔ ነው”።

“ከእኔ ጋር ያልሆነ ይቃወመኛል፥ …” ማቴ 12:30
ቡድንህን ዛሬ ምረጥ

31/05/2019

Happy preparation day SDA family

Want your school to be the top-listed School/college in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Website

Address

Addis Ababa

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00
Saturday 09:00 - 17:00
Sunday 09:00 - 17:00