የደሙ ሀይል

የደሙ ሀይል Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የደሙ ሀይል, Hagere Mariam.

አና ሃሰልታይን ጃድሰን፡ በበርማ ቀዳሚዋ ሚስዮናዊየትውልድ ዘመን፡ እ.አ.አ1789 ዓ.ም - 1826 ዓ.ም  “ለክርስቶስ ዓላማ ተብሎ የሚከፈል ትንሽ መስዋዕትነት ሊጠቀስ የሚገባው አይደለም፤ ...
19/06/2026

አና ሃሰልታይን ጃድሰን፡ በበርማ ቀዳሚዋ ሚስዮናዊ
የትውልድ ዘመን፡ እ.አ.አ1789 ዓ.ም - 1826 ዓ.ም

“ለክርስቶስ ዓላማ ተብሎ የሚከፈል ትንሽ መስዋዕትነት ሊጠቀስ የሚገባው አይደለም፤ ለኃጢአተኞች ሲል ሕይወቱን አሳልፎ ለሰጠው አምላክ ያለኝን ሁሉ መስጠት መቻል ትልቅ ክብር እንደሆነ ይሰማኛል።”

አን ሃሰልታይን ታኅሣሥ 22 ቀን 1789 ዓ.ም. በማሳቹሴትስ ግዛት ብራድፎርድ ከተማ ተወለደች። በዚያ ፍቅርና ደስታ በሞላበት ቤተሰብ ውስጥ ካደጉት አምስት ልጆች መካከል እርሷ የመጨረሻዋ ነበረች። በታዳጊነት ዕድሜዋ "ናንሲ" በሚለው የቁልምጫ ስሟ የምትታወቀው አና፤ በሰዎች ዘንድ ተወዳጅ፣ ብልህ እና በተለይ በተጫዋችነቷና በደስተኛነቷ የምትታወቅ ነበረች።

የሚስዮናዊነት ጥሪ
የአና መንፈሳዊ ጉዞ የጀመረው ድራማዊ በሚመስል አጋጣም ሕይወቷን በለወጠ (የንስሐ) ልምምድ፣ ገና በስድስት ዓመቷ ነበር። በወቅቱ በነበረው መንፈሳዊ መነቃቃት ወቅት በብራድፎርድ አካዳሚ ትምህርቷን እየተከታተለች ሳለ፣ “ስትሪክቸርስ ኦን ዘ ሞደርን ሲስተም ኦፍ ፊሜል ኤጁኬሽን” (Strictures on the Modern System of Female Education) የተሰኘውን የሃና ሞርን መጽሐፍ ለማንበብ በቃች። ይህ መጽሐፍ “ለሌሎች የምትጠቅምበትን የሕይወት ጎዳና እንድትፈልግ” ውስጣዊ ግፊት ፈጠረባት። ይህ ጠንካራ እምነት በጓደኞቿ ዘንድ ተወዳጅ የነበረችውን ወጣት፤ የራሷን ምቾት ትታ ለላቀ ዓላማ እንድትኖር አደረጋት። ገና በ13 ዓመቷ የእምነት ጉዞዋን የምታሰፍርበት መንፈሳዊ ማስታወሻ መጻፍ ጀመረች።

የሕይወቷ ትልቁ አጋጣሚ የተከሰተው በ1810 ዓ.ም. ክረምት ላይ ነበር። በወቅቱ የሃሰልታይን ቤተሰቦች ለአገር ጎብኚ ሚስዮናውያን የእንግዳ መቀበያ ፕሮግራም አዘጋጅተው የነበረ ሲሆን፣ ከእንግዶቹ መካከል አዶኒራም ጃድሰን የተባለ ወጣት ይገኝበታል። አዶኒራም ገና እንዳያት በአና ማንነትና ብልህነት ልቡ ተማረከ። ግንኙነታቸው እያደገ ሲሄድ አና በሕይወቷ ውስጥ እጅግ ከባድና ወሳኝ ውሳኔ ከፊቷ ተደቀነ፤ አዶኒራም የውጭ አገር ሚስዮናዊ ለመሆን ቆርጦ የተነሳ ሰው ነበር፤ ይህም በወቅቱ ለአሜሪካውያን ሴቶች ፈጽሞ የማይታሰብና ያልተለመደ የሕይወት መስመር ነበር። እሱን ማግባት ማለት ባል ማግኘት ብቻ ሳይሆን፣ የተለመደውንና የለመደችውን ነገር ሁሉ ትታ ለመሄድ የሚያስገድዳትን ያንን መለኮታዊ ጥሪ በጸጋ መቀበል ማለት ጭምር ነበር።

የካቲት 5 ቀን 1812 ዓ.ም አና እና አዶኒራም ጋብቻቸውን ፈጸሙ። ከዚያም ብዙ ሳይቆዩ በአባቷ ምርቃትና ቡራኬ ወደ ሚስዮናዊነት አገልግሎት ስፍራቸው በመርከብ ተጓዙ። በዚህም በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ውጭ አገር ከተላኩት አሜሪካውያን ሚስዮናውያን ቡድን አባል ሆኑ። አን ከጊዜ በኋላ ለክርስቶስ ዓላማ ስለከፈለችው መስዋዕትነት ስታስታውስ፣ ያላት ጠንካራ እምነትና ቁርጠኝነት በሚያንጸባርቅ መልኩ እንዲህ ስትል ጽፋ ነበር፤ “ለክርስቶስ ዓላማ ተብሎ የሚከፈል ትንሽ መስዋዕትነት ሊጠቀስ የሚገባው አይደለም፤ ለኃጢአተኞች ሲል ሕይወቱን አሳልፎ ለሰጠው አምላክ ያለኝን ሁሉ መስጠት መቻል ትልቅ ክብር እንደሆነ ይሰማኛል።”

ወደ በርማ የተደረገው ጉዞ
ወደ ካልካታ (ሕንድ) ያደረጉት አስቸጋሪ የባሕር ላይ ጉዞ ከተጠናቀቀ በኋላ፣ የብሪታንያ የምሥራቅ ሕንድ ኩባንያ (British East India Company) የውጭ አገር ሚስዮናውያንን አጥብቆ እንደሚቃወም ተረዱ። ይህም ሌላ መጠጊያ ፍለጋ እንዲንከራተቱ አስገደዳቸው። በመጨረሻም በ1813 ዓ.ም. በበርማ (የአሁኗ ምያንማር) ለመቀመጥ ወሰኑ፤ ይህች አገር ማንኛውም አማካሪ እንዳይሄዱባት አጥብቆ

"አንድ ቀን ቢሊ ግርሃም ሞተ የሚል ዜና ልታነቡ ወይም ልትሰሙ ትችላላችሁ። ለአፍታ እንኳ እንዳታምኑት! እኔ አሁን ካለሁበት ይልቅ በዚያን ጊዜ ይበልጥ በህይወት እኖራለሁ፤ ያደረግኩት አድራሻ...
19/06/2026

"አንድ ቀን ቢሊ ግርሃም ሞተ የሚል ዜና ልታነቡ ወይም ልትሰሙ ትችላላችሁ። ለአፍታ እንኳ እንዳታምኑት! እኔ አሁን ካለሁበት ይልቅ በዚያን ጊዜ ይበልጥ በህይወት እኖራለሁ፤ ያደረግኩት አድራሻዬን መቀየር ብቻ ነው።"
ወንጌላዊ ቢሊ ግራሃም

የፕላኔታችን ግዙፉ ተደባዳቢ እና ከባድ ሚዛን ዊሪስትለር ሻቁሌ ኦ'ኒያል "የእኔ እጅግ ምርጡ ዉሳኔ ህይወቴን ለኢየሱስ መስጠቴ ነዉ" ሲል ተናገረ::
19/06/2026

የፕላኔታችን ግዙፉ ተደባዳቢ እና ከባድ ሚዛን ዊሪስትለር ሻቁሌ ኦ'ኒያል "የእኔ እጅግ ምርጡ ዉሳኔ ህይወቴን ለኢየሱስ መስጠቴ ነዉ" ሲል ተናገረ::

ታላቁ ሼክ ሙፍቲ ከእስልምና ወደ ክርስትና ሽግግር ካደረገ በኋላ በአንድ ጊዜ 20,000.00 ሙስሊሞችን እየመራቸዉ ወደ ኢየሱስ ማምጣቱን ተከትሎ በእንዶኔዢያ ዉስጥ የወንጌል ችቦ እየተቀጣጠለ...
16/06/2026

ታላቁ ሼክ ሙፍቲ ከእስልምና ወደ ክርስትና ሽግግር ካደረገ በኋላ በአንድ ጊዜ 20,000.00 ሙስሊሞችን እየመራቸዉ ወደ ኢየሱስ ማምጣቱን ተከትሎ በእንዶኔዢያ ዉስጥ የወንጌል ችቦ እየተቀጣጠለ ነዉ ተባለ::
++++++++++++++++++++++++++++++
"ለእኔ ኢየሱስ ተገልጦልኛል:ኢየሱስ እንዶኔዢያ ዉስጥ ነዉ:ኢየሱስ እንዶኔዢያን እየተቆጣጠራት ነዉ" የምሉ መፎክሮችን ያነገቡ ሰልፈኞች የእንዶኔዢያ ጎዳናዎችን መሙላታቸዉን ከስፍራዉ ሾልኮ የወጣ መረጃ አመልክቷል::

አምላኬ ሆይ ለስምህ እዘምራለሁ ምስጋና በአፌ ነውበማለዳ ምሕረትህን፣ በሌሊትም እውነትህን አስባለሁበእጣ ክፍሌ ስለቆምኩ በፊትህ ክብርህን እንዳወራአጥናለሁ፤ ሁልጊዜ የመረጥከኝም አንተው ነህ ...
14/06/2026

አምላኬ ሆይ ለስምህ እዘምራለሁ ምስጋና በአፌ ነው
በማለዳ ምሕረትህን፣ በሌሊትም እውነትህን አስባለሁ
በእጣ ክፍሌ ስለቆምኩ በፊትህ ክብርህን እንዳወራ
አጥናለሁ፤ ሁልጊዜ የመረጥከኝም አንተው ነህ ለዚህ ሥራ።

 #መጽሐፍ ቅዱስ ስለ እግዚአብሔር አብ እና ስለ ኢየሱስ ማንነት በግልፅ ምን እንደሚያስተምር ❓️⛔️መጽሐፍ ቅዱስ ስለ እግዚአብሔር አብ እና ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ማንነት፣ እንዲሁም በመካከላ...
14/06/2026

#መጽሐፍ ቅዱስ ስለ እግዚአብሔር አብ እና ስለ ኢየሱስ ማንነት በግልፅ ምን እንደሚያስተምር ❓️

⛔️መጽሐፍ ቅዱስ ስለ እግዚአብሔር አብ እና ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ማንነት፣ እንዲሁም በመካከላቸው ስላለው አንድነትና መለኮታዊ ግንኙነት በግልፅ ያስተምራል።

#1ኛ]] እግዚአብሔር እና ኢየሱስ በባሕርይና በሕልውና አንድ ናቸው

⚫️ጥቅስ፦ “እኔና አብ አንድ ነን።” — የዮሐንስ ወንጌል 10፥30

⛔️ምክንያት፦ 👀ኢየሱስ ይህንን ሲናገር በዓላማ ብቻ ሳይሆን በመለኮታዊ ተፈጥሮና በሥልጣን ከአብ ጋር እኩል መሆኑን መግለጡ ነው። ይህንን በሰሙ ጊዜ አይሁድ “ራሱን አምላክ አደረገ” ብለው ሊወግሩት ድንጋይ አንስተዋል።

#2ኛ]] ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ ፍጹም አምላክ ነው:-

⚫️ጥቅስ፦ “በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ።” — የዮሐንስ ወንጌል 1፥1

⛔️ምክንያት፦ 👀እዚህ ላይ “ቃል” የተባለው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው (ዮሐ 1፥14)።

🟣🦻ጥቅሱ ፍጥረት ከመፈጠሩ በፊት ኢየሱስ ዘላለማዊ እንደነበረና እርሱ ራሱ እግዚአብሔር እንደሆነ በግልፅ ያስረዳል።

#3ኛ][ ኢየሱስ ዘላለማዊ (ያለፈውና የሚመጣው) አምላክ ነው:-

🔵ጥቅስ፦ “ኢየሱስም፦ እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ አብርሃም ሳይወለድ እኔ አለሁ አላቸው።” — የዮሐንስ ወንጌል 8፥58

⛔️ምክንያት፦ 👀“እኔ አለሁ” (በግሪክ Ego Emi) የሚለው ቃል እግዚአብሔር በብሉይ ኪዳን ለሙሴ የተናገረውን መለኮታዊ ስም (ያህዌ) የሚያመለክት ነው።

👉 ኢየሱስ ከአብርሃም በፊት የነበረ ዘላለማዊ አምላክ መሆኑን እያረጋገጠ ነው።

#4ኛ]] አብን ማየት የሚቻለው በኢየሱስ በኩል ብቻ ነው:-

🟢ጥቅስ፦ “እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም። እኔን ያየ አብን አይቶአል።” — የዮሐንስ ወንጌል 14፥6፣9

⛔️ምክንያት፦ 👀እግዚአብሔር አብ የማይታይ መንፈስ ስለሆነ፣ እርሱን ሙሉ በሙሉ ተረድቶ ማየት የሚቻለው በሰው አካል ተገልጦ የመጣውን ልጁን ኢየሱስን በማወቅና በማመን ብቻ ነው።

#5ኛ]] የመለኮት ሙላት ሁሉ በኢየሱስ ውስጥ በሰውነት ይኖራልጥቅስ፦ “በእርሱ የመለኮት ሙላት ሁሉ በሰውነት ተገልጦ ይኖራልና፤” — ወደ ቆላስይስ ሰዎች 2፥9

⛔️ምክንያት፦👀 ኢየሱስ ወደ ምድር ሲመጣ አምላክነቱን አልተወም። እርሱ ፍጹም ሰው እንደመሆኑ መጠን፣ የእግዚአብሔር መለኮታዊ ባሕርይ፣ ኃይልና ክብር ሁሉ በእርሱ ውስጥ በተሟላ ሁኔታ ይገኛል።

🔵ባጭሩ፦ #መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ እና ኢየሱስ ክርስቶስ (ወልድ) በመለኮትና በባሕርይ አንድ የሆኑ፣ ነገር ግን በማንነት (አካል) የተለያዩ መሆናቸውንና ኢየሱስም እግዚአብሔር በሥጋ የተገለጠበት ፍጹም አምላክና ፍጹም ሰው እንደሆነ ያስተምራል።

ከ49 ሀገራት የተወጣጡ 17,000.00 ሰዎች የእግዚአብሔር ልጅ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን አምነዉ በመዳን የዉኃ ጥምቀት መፈፀማቸዉን ምንጮች ገለፁ::
10/06/2026

ከ49 ሀገራት የተወጣጡ 17,000.00 ሰዎች የእግዚአብሔር ልጅ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን አምነዉ በመዳን የዉኃ ጥምቀት መፈፀማቸዉን ምንጮች ገለፁ::

የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊልያም ሩቶ መፅሐፍ ቅዱሳቸውን ይዘው ዘወትር እሁድ በቤተክርስቲያን 🙏
10/06/2026

የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊልያም ሩቶ መፅሐፍ ቅዱሳቸውን ይዘው ዘወትር እሁድ በቤተክርስቲያን 🙏

በእንግሊዝ ዋና ከተማ ለንደን የተሰበሰቡ በሚሊዬን የምቆጠሩ ሰልፈኞች "ኢየሱስ ንጉስ ነዉ" የምለዉን ቃል ደጋግመዉ ስያስተጋቡ መዋላቸዉን ምንጮች ገለፁ::
10/06/2026

በእንግሊዝ ዋና ከተማ ለንደን የተሰበሰቡ በሚሊዬን የምቆጠሩ ሰልፈኞች "ኢየሱስ ንጉስ ነዉ" የምለዉን ቃል ደጋግመዉ ስያስተጋቡ መዋላቸዉን ምንጮች ገለፁ::

መፍትሔው ጸሎት ነው‼️ ትሁቷ ቀዳማዊት እመቤት ❤ ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሄድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ።መዝሙረ ዳዊት 122:1
07/06/2026

መፍትሔው ጸሎት ነው‼️ ትሁቷ ቀዳማዊት እመቤት ❤
ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሄድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ።
መዝሙረ ዳዊት 122:1

Address

Hagere Mariam

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የደሙ ሀይል posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share