09/04/2026
እውቁ ኢትዮጵያዊ ገጣሚ፣ ባለቅኔ፣ ፀሃፊ ተውኔት . . .
ሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድህን "እናት ዓለም ጠኑ" (1967) ትያትር ቃለ ተውኔት ላይ :-
'አፋዊ ሆንን!
ሕያዊ ሳንሆን አፋዊ!
ቃለ ሕይወት ሳንሆን፣ ብኩን ቃለ-አፍ ብቻ!
እንጂ! ቤታችን አንድ ነው፡፡
“ቤት” ብለን ለልጆቻችን ያወረስናቸው
ፍቅር የሞተበት ቤታችን! አንድ ነው፡፡
አባቶቻችን ልባም
እኛ አፋም፡፡
እሳት ዐመድ ወለደ ሆንን እንጂ- ቤታችንስ አንድ ነው፡፡ . . . ' በማለት የዛሬውን መራር እውነት ይተነብያል።
በፖሊሲ እና በቴክኖሎጂ ጉዳዮች መወያየት እና መከራከር የነበረበት የዛሬው ትውልድ ወርዶ ወርዶ በባህል ልብስ ሲነታረክ ትዝ ብሎኝ ፈልጌ አጋራኋችሁ🙏🙋