M'r Fikre

M'r Fikre THE SUN WILL RISE AND WE WILL TRY AGAIN TOMORROW.

በኤርትራ ጨለማ እስር ቤት የተረሳችው ሲሃም!🥹💔  : የአስራ አምስት ዓመት ታዳጊ እያለች የነፃነት አየሯን የተነጠቀችው ፤ ዛሬ የ29 ዓመት ወጣት  ሆናለች ፤ ሲሃም አሊ አብዱ።ሲሃም አሊ ፤...
15/09/2026

በኤርትራ ጨለማ እስር ቤት የተረሳችው ሲሃም!🥹💔

: የአስራ አምስት ዓመት ታዳጊ እያለች የነፃነት አየሯን የተነጠቀችው ፤ ዛሬ የ29 ዓመት ወጣት ሆናለች ፤ ሲሃም አሊ አብዱ።

ሲሃም አሊ ፤ ላለፉት 14 አሰቃቂ ዓመታት ያለ ምንም የፍርድ ቤት ክስ፣ በወንጀል ሳትጠየቅ፣ እና የት እንዳለች እንኳ በውል ሳይታወቅ በለጋ እድሜዋ በእስር እየማቀቀ ትገኛለች ።
የዚህች አሜሪካዊ ዜግነት ያላት ንፁህ ታዳጊ ወንጀል አንድ እና አንድ ብቻ ነበር፤ የኤርትራ ከፍተኛ ባለስልጣን የነበሩት አባቷ ከፕሬዚዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ ጋር በፈጠሩት የፖለቲካ ፀብ የቂም ሰለባ መሆኗ።

አቶ አሊ አብዱ የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስትር እና የፕሬዚዳንቱ ቀኝ እጅ ነበሩ። ከትጥቅ ትግሉ ዘመን አንስቶ አብረው የዘለቁት አቶ አሊ፣ ምናልባትም ቀጣዩ የሃገሪቱ መሪ ሊሆኑ እንደሚችሉ በብዙዎች ዘንድ ይገመት ነበር። ነገር ግን፣ ሁሉም ነገር በአንድ አሳዛኝ ቅፅበት ተቀለበሰ።

የጥል መንስኤው የዓለምን ትኩረት የሳበው ያ ታዋቂ የአልጀዚራ ቃለ-መጠይቅ ነበር። ጋዜጠኛዋ ፕሬዚዳንት ኢሳይያስን "አምባገነን ነዎት፤ አካባቢውን በሁከት እያመሱ ነው" ብላ ፊት ለፊት ስትሞግታቸው፣ ፕሬዚዳንቱ የደም ስሮቻቸው እስኪገተሩ እና ላባቸው እስኪጠምቅ ድረስ በንዴት ጦፉ። በካሜራ ፊት የታየው ይሄው አሳፋሪ ስሜታዊነት፣ በመሪው ልብ ውስጥ መርዝ ፀነሰ።

ቃለ-መጠይቁ እንደተጠናቀቀም፣ ፕሬዚዳንቱ ሚኒስትራቸውን አሊ አብዱን አስጠርተው ቪዲዮው እንዳይተላለፍ ጥብቅ ትዕዛዝ ሰጡ። ሚኒስትሩ "ይህ የዓለም አቀፍ ሚዲያ ጉዳይ በመሆኑ ከእኛ አቅም ውጪ ነው" የሚል እውነታ ሲያስረዱ፣ ፕሬዚዳንቱ በቁጣ ገነፈሉ፤ ሚኒስትራቸውንም በቦክስ እና በርግጫ ደበደቡ።

ከዚህች እጣ ፈንታ ቀያሪ ቀን በኋላ፣ አሊ አብዱ የፕሬዚዳንቱን በቀለኛነት ጠንቅቀው ስለሚያውቁ አገር ጥለው ለመሰደድ ወሰኑ። ለስራ ወደ ጀርመን በተጓዙበት አጋጣሚ ስርዓቱን ከድተው ወደ አውስትራሊያ ኮበለሉ። ይህ ውሳኔያቸው ግን በአስመራ ለቀረችው የ15 ዓመቷ ልጃቸው የሲኦል በር ከፋች ሆነ።

አባቷ ልጃቸውን ለማትረፍ በሚል 7,000 ዶላር ከፍለው በህገ-ወጥ መንገድ በሱዳን በኩል እንድትወጣ ለማድረግ ቢሞክሩም፣ ሲሃም የሱዳንን ድንበር ልትረግጥ ጥቂት ሲቀራት በኤርትራ የደህንነት ኃይሎች እጅ ወደቀች። ከዚያች ቀን ጀምሮ እስከ ዛሬዋ ሰዓት ድረስ፣ ሲሃም ያለችበት ቦታ በእርግጠኝነት አይታወቅም።

ነገር ግን የተለያዩ የመብት ተሟጋቾች መረጃ እንደሚያሳየው፣ ይህቺ ምስኪን ወጣት የተጣለችው 'ኤራ ኤሮ' በተባለው፣ በበረሃ ውስጥ በሚገኝ እና ከሰው እይታ በተሰወረ የምድር ስር የኮንቴነር እስር ቤት ውስጥ ነው። ይህ ስፍራ የቀድሞ ከፍተኛ ባለስልጣናት ያለ ፀሐይ ብርሃን በስቃይ ህይወታቸው ያለፈበት የምድር ላይ ሲኦል ነው።

የአባቷን የፖለቲካ ሸክም እንድትሸከም የተፈረደባት ሲሃም፣ የልጅነት ህልሟ፣ የወጣትነት ብሩህ ተስፋዋ፣ እና ነፃነቷ ሙሉ በሙሉ ተነጥቋል። ዓለም አቀፍ የመብት ተሟጋቾች ድምፃቸውን ቢያሰሙም፣ የኤርትራ መንግስት ዛሬም ድረስ ስለ እርሷ ህያውነት ትንፍሽ አላለም። የ15 ዓመቷ ህፃን፣ አሁንም በጨለማ ውስጥ የፍትህ ደወል የሚደወልበትን ቀን እየጠበቀች ትገኛለች።

ሻሸመኔ ወይስ ደብረ አብርሃን?! የኮሪደር ልማት ከተሞች ላይ ትልቅ ለውጥ እየመጣ ነው። መቅደም የለባቸው ብዙ ነገሮች ቢኖሩም ልማት ነው መበረታታት አለበት።ይህ የምትመለከቱት የሻሸመኔ ከተማ...
15/09/2026

ሻሸመኔ ወይስ ደብረ አብርሃን?!

የኮሪደር ልማት ከተሞች ላይ ትልቅ ለውጥ እየመጣ ነው። መቅደም የለባቸው ብዙ ነገሮች ቢኖሩም ልማት ነው መበረታታት አለበት።

ይህ የምትመለከቱት የሻሸመኔ ከተማ እና የደብረብርሃን ከተማ የኮሪደር ልማት ነው እንዴት ያነፃፅሩታል?

📸1 ሻሸመኔ 📸2 ደብረብርሃን

#ሻሸመኔ #ኮሪደር #ደብረብርሃን

"ከእንግዲህ ነጭ ሴት አልፈልግም፤ 3 ጊዜ ሞክሬ አልተሳካልኝም! ፍቅር በአስተርጓሚ አይሆንም!" በአለም አቀፍ ደረጃ በ'90 Day Fiancé' ሾው ዝነኛ የሆነው ቢኒያም ሽብሬ፣ ከባለቤቱ ከ...
15/09/2026

"ከእንግዲህ ነጭ ሴት አልፈልግም፤ 3 ጊዜ ሞክሬ አልተሳካልኝም! ፍቅር በአስተርጓሚ አይሆንም!" በአለም አቀፍ ደረጃ በ'90 Day Fiancé' ሾው ዝነኛ የሆነው ቢኒያም ሽብሬ፣ ከባለቤቱ ከአሪ ጋር መለያየቱን ይፋ በማድረግ ያልተጠበቀ እውነታ አፈነዳ!

በዓለም ዙሪያ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ተመልካቾች በጉጉት ሲከታተሉት የነበረው የቢኒያም እና የአሜሪካዊቷ አሪኤላ (Ariela) የፍቅር ታሪክ ምን ደረጃ ላይ ደረሰ ለሚለው ጥያቄ፣ ቢኒያም በሰይፉ በኢቢኤስ ፕሮግራም ላይ አስደንጋጭ ምላሽ ሰጥቷል። ሁለቱ ከተለያዩ ሁለት ዓመታት እንዳለፋቸው በይፋ የተናገረው ቢኒያም፤ "ነጮችን አግብተው የዘለቁ ቢኖሩም ለእኔ ግን አልሰራም፤ ከእንግዲህ በቃኝ!" በማለት ሦስት ጊዜ የሞከረው የውጭ ሀገር ግንኙነት ለምን እንደከሸፈ በግልጽ አውርቷል።

"ህይወትህ ሁሉ ካሜራ ፊት ድራማ ሲሆን፣ ሁልጊዜ በትንሽ በትልቁ ስትጣላ ፍቅር እንዴት ይዘልቃል?" የሚለው ቢኒ፤ በተለይ ደግሞ ስሜትን በቅኔና በሙቀት አውጥቶ ለመግለጽ የቋንቋው እና የባህሉ ልዩነት ትልቅ ፈተና እንደነበር አልሸሸገም። "ፍቅር በአስተርጓሚ አይሆንም፤ አሁን በቋንቋዬ የምትረዳኝን፣ እምነቴንና ባህሌን የምትጋራ የሀገሬን ልጅ ነው የምፈልገው" በማለት ልቡን ለአዲስ የሀበሻ ፍቅር ክፍት ማድረጉ በሶሻል ሚዲያ ላይ ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኗል።

ሌላው ተመልካቹን ያስገረመውና ያነጋገረው ጉዳይ ልጁን አቪን ያሳደገበት አደገኛ የሚመስል መንገድ ነው። ቢኒያም ልጁ ገና በ6 ወሩ በእጁ መዳፍ ላይ ቆሞ አክሮባት እንዲለማመድ ያደርግ እንደነበር ሲናገር፣ ሰይፉ "እግዚአብሔር ሆይ እንኳን የቢኒያም ልጅ አልሆንኩም!" በማለት በድንጋጤ ሲቀልድበት ታይቷል። "ልጁ የሚፈራው መሬት ላይ ሳቆመው እንጂ እጄ ላይ አይደለም" የሚለው ቢኒ፣ ዛሬ ላይ ልጁ በትምህርት ቤቱ "አባቴ ስፓይደርማን ነው" እያለ በኩራት የሚናገር ጎበዝ ስተንት ሰሪ እንደሆነ ገልጿል።

በተጨማሪም የፊታችን መስከረም 9 በኮንቬንሽን ሴንተር ከጠንካራው አገረሰላም አበራ ጋር በሚያደርገው የኢኤምኤምኤ (MMA) ፍልሚያ ዙሪያ የተፈጠረው ውዝግብም ትኩረት ስቧል። ዮኒ ቬጋስ "ቢኒያም ያሸንፋል" በሚል 10 ሚሊዮን ብር መወራረዱን ተከትሎ፤ ቢኒያም በስላቅ "5 ሚሊዮኑን በጎን ከሰጣችሁኝ እሸነፋለሁ" ብሎ መናገሩ አዳራሹን በሳቅ አናውጦታል። እስካሁን በተፋለመባቸው ውድድሮች ሁሉ ተሸንፎ የማያውቀው፣ ረጅሙ ግጥሚያው 2 ደቂቃ ብቻ የፈጀ፣ አጭሩ ደግሞ በ6 ሰከንድ ባልሞላ ጊዜ ተጋጣሚውን አዘርሮ የጨረሰው ቢኒያም፤ "የተናካሽ ውሻ ጩኸት አያበዛም… መልሴን ሜዳው ላይ በቦክሴ እሰጣለሁ" ሲል አስጠንቅቋል።

ከዚህ ሁሉ ዝና እና የገንዘብ ወሬ ጀርባ ግን የማይታመን የመከራ ህይወት አለ። በልጅነቱ የቤተሰቡ ሀብት በደርግ ተወርሶ ጎዳና የወደቀው፣ የትራንስፖርት መክፈያ አጥቶ በረሃብ የተመላለሰው ቢኒያም፤ በደቡብ ሱዳን በስደት በነበረበት ወቅት በሰከረ ጀነራል መኪና ምክንያት እንደ ሌባ ተጠርጥሮ በፖሊሶች ሰደፍ ፊቱ እስኪፈራርስ ድረስ ተደብድቦ ነበር። የፖሊስ ኮሚሽነሩ በዳንሱ ተሰጥኦ እስካወቀው ድረስ በሞትና በህይወት መካከል የነበረበት ያ አሰቃቂ ምሽት ዛሬም ከአእምሮው አይጠፋም።

ከአሜሪካ የሱፐር ቦል መድረክ እስከ አዲስ አበባው የኮንቬንሽን ሴንተር ፍልሚያ… የቢኒያም ሽብሬ መስከረም 9 በሚደረገው ግጥሚያ ላይ ምን የሚያሳይ ይመስላችኋል? 🥊

"ልጃችንን ለማናውቀው የቴሌ ሠራተኛ አንሰጥም!" ዶክተር ሮዳስ ታደሰ ማንነቱን ደብቆ «ዳዊት እባላለሁ» በማለት እጮኛውን ያስጠየቀበት እና 26ቱ ፈታኝ ጥያቄዎች በአንድ ቅጽበት የተሰረዙበት ...
15/09/2026

"ልጃችንን ለማናውቀው የቴሌ ሠራተኛ አንሰጥም!" ዶክተር ሮዳስ ታደሰ ማንነቱን ደብቆ «ዳዊት እባላለሁ» በማለት እጮኛውን ያስጠየቀበት እና 26ቱ ፈታኝ ጥያቄዎች በአንድ ቅጽበት የተሰረዙበት አነጋጋሪው የሽምግልና ሚስጥር!

በስነ-ከዋክብት ምርምሩና በመንፈሳዊ መጻሕፍቱ መላው ኢትዮጵያ የሚያውቀው መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ፤ «መቼ ነው የምታገባው?» የሚለው የማያባራ የሕዝብ ጉትጎታ በመጨረሻም አብቅቶ የሰርጉን ዜና ይፋ አድርጓል። ነገር ግን ከሰርጉ መርሐ ግብር በላይ የማኅበራዊ ሚዲያ መነጋገሪያ የሆነው በሽምግልናው ወቅት የተፈጠረው ያልተጠበቀ ድራማዊ ክስተት ነው!

ዶክተር ሮዳስ ነገሩ ያልተጠበቀ ሰርፕራይዝ እንዲሆንለት በማሰብ፣ እጮኛው ሳምራዊት መላኩ ለቤተሰቦቿ ስለ ትክክለኛ ማንነቱ አንዲትም ቃል እንዳትናገር ያደርጋታል። ቤተሰቦቿ «ይህ የምትጠራሪው ልጅ ማነው?» ብለው ሲያፋጥጧት «ቴሌኮሚኒኬሽን ውስጥ የሚሠራ ዳዊት የሚባል ሰው ነው» በማለት «በጎ ውሸት» የተባለውን መረጃ ትሰጣቸዋለች።
የሙሽሪት ቤተሰቦችም በበኩላቸው «እኛ የማናውቀው፣ ማንነቱ በውል ያልተጣራ ሰውማ ልጃችንን በጭራሽ አይወስዳትም!» በሚል ፅኑ አቋም ሽማግሌዎችን ላብ የሚያጠምቁ 26 የሚደርሱ ወፍራም እና ፈታኝ ጥያቄዎችን አዘጋጅተው ጦር ግንባር ይመስል ይጠባበቁ ጀመር።

የሽምግልናው ቀን ደረሰ። ዶክተር ሮዳስ 12 ታዋቂ ሽማግሌዎችን (እንደ አርቲስት ስለሺ ደምሴ/ጋሻ አበራ ሞላ፣ ጋዜጠኛ ጥበቡ በለጠ እና ቀኝ አዝማች ትእዛዙ ኩሬ ያሉትን) መጽሐፍ ቅዱስ፣ የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕልና ከቃና ዘገሊላ የመጣ ወይን አስይዞ ላከ። የንስሐ አባቱ የሙሽራውን ማንነት ሲገልጹ «30 መጻሕፍትን ያበረከተው፣ የአንድሮሜዳው ባለቤት መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ ነው!» ሲሉ አዳራሹ በድንጋጤ ተናጋ!
ለዳዊት ተብለው የተዘጋጁት 26ቱ አጣብቂኝ ጥያቄዎች ወዲያውኑ ውድቅ ተደርገው «ልጃችንን ሰጥተናል!» የሚለው ቃል በአዳራሹ አስተጋባ። ዝነኝነት እና እውነተኛ ክብር በአንድ ጀምበር የተዘጋጀውን ፈተና አፈራረሰው ማለት ይቻላል!

ሙሽሪት ሳምራዊት መላኩ በሁለቱም ወገን ከካህናት ቤተሰብ የተገኘች፣ ታናሽ ወንድሟ ዲያቆን የሆነና በመንፈሳዊ ሕይወቷ እጅግ የታነጸች ሴት ናት። ዶክተር ሮዳስም «እስካሁን 30 መጻሕፍትን ጽፌያለሁ፤ 31ኛዋ መጽሐፌ ደግሞ በብዕርና በቀለም ሳትሆን በቃልኪዳን፣ በጸሎትና በሕይወት የምትጻፍ አዲሷ የትዳር አጋሬ ናት» በማለት በገዛ ቃሉ ገልጿታል።

የሰርጉ ዝርዝር መረጃ ለምትፈልጉ ሁሉ፡-
ቀኑ፡ የፊታችን እሁድ መስከረም 10 ቀን
ቦታው፡ ቶታል ሰፈረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል (ከጦር ኃይሎች ወደ ቶታል በሚወስደው መንገድ፣ ዱባይ ኤምባሲ አጠገብ)
መርሐ-ግብሩ፡ ከሌሊቱ 10 ሰዓት ጀምሮ ሥርዓተ ተክሊሉ የሚፈጸም ሲሆን፣ ከጠዋቱ 2:00 እስከ 4:00 ባለው ጊዜ በካቴድራሉ አውደ ምሕረት ላይ ታላቅ መንፈሳዊ መርሐ ግብር ይደረጋል። ዶክተር ሮዳስ «ደስታን ሲካፈሉት ይበዛል» በማለት አክባሪዎቹ ሁሉ ሳይጠሩ እንደተጠሩ ቆጥረው እንዲገኙ በይፋ ጥሪውን አቅርቧል። በተጨማሪም ከአረጋውያንና ሕሙማን ምርቃት ለመቀበል ወደ መቄዶንያ የሚያቀናበት የበጎ አድራጎት መርሐ ግብርም ተዘጋጅቷል። ከሚዜዎቹ መካከልም ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ይገኝበታል።

ለዶክተር ሮዳስና ለሳምራዊት የአብርሃምና የሣራን ያማረ የተባረከ ትዳር ይሁንላቸው! 🕊️✨

ዓለምን ያነጋገረው የፑቲን ብርቅዬ ግብዣ !❤️🙏በዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ መድረክ ላይ፣ ድምፅ ሳይሰማ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ቃላትን የሚናገሩ ታሪካዊ ቅጽበቶች አሉ። ከነዚህም አንዱ፣ በቅርቡ በተ...
15/09/2026

ዓለምን ያነጋገረው የፑቲን ብርቅዬ ግብዣ !❤️🙏

በዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ መድረክ ላይ፣ ድምፅ ሳይሰማ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ቃላትን የሚናገሩ ታሪካዊ ቅጽበቶች አሉ። ከነዚህም አንዱ፣ በቅርቡ በተካሄደው የብሪክስ (BRICS) የመሪዎች ጉባኤ ላይ የታየውና የብዙዎችን ትኩረት የሳበው ልዩ ክስተት ነው። የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን እና የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ወደ ስብሰባው አዳራሽ በአንድ መኪና ውስጥ ሆነው ማምራታቸው፣ ከተራ የትራንስፖርት ጉዞ ባለፈ ጥልቅ ፖለቲካዊ መልዕክት ያዘለ ሆኖ አልፏል።

ክስተቱ በቀላሉ የሚታለፍ አይደለም። ፕሬዝዳንት ፑቲን ወደ ውጭ ሀገራት በሚያደርጉት ማንኛውም ጉዞ፣ የራሳቸውን ልዩ የፕሬዝዳንት መኪና ይዘው መጓዝ የተለመደ ተግባራቸው ነው። መኪናቸው እጅግ ጥብቅ የሆነ የደህንነት ፕሮቶኮል የሚተገበርበት በመሆኑ፣ ሌላ ሀገር መሪ ቀርቶ የቅርብ ባለስልጣናት እንኳን አብረዋቸው ሲጓዙ ማየት እጅግ ብርቅ ነው። በዚህ ደረጃ በተጠበቀና በልዩ ሁኔታ በተዘጋጀ መኪና ውስጥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይን ጋብዘው አብረው መጓዛቸው ፤ ሩሲያ ለኢትዮጵያ ያላትን የላቀ ክብርና እምነት ያሳያል።

በመሪዎቹ መካከል ያለውን የጠበቀ ግላዊ ቅርበት ያንፀባርቃል፤የሁለቱን ሀገራት ስትራቴጂካዊ አጋርነት እና የጋራ ራዕይ ለዓለም ማህበረሰብ ያሳውቃል።

መሪዎቹ የተጓዙበት መኪና በሩሲያ ቴክኖሎጂ የተመረተውና "Aurus Senat" በመባል የሚታወቀው ይህ የቅንጦት ሊሙዚን፣ የሩሲያ ፕሬዝዳንታዊ ኮንቮይ ዋነኛ የጀርባ አጥንት ነው።

መኪናው ከማንኛውም ዓይነት ከባድ ጥቃት (armored) ሙሉ በሙሉ የተጠበቀና ለፕሬዝዳንቱ ልዩ ደህንነት ሲባል በከፍተኛ የቴክኖሎጂ ውጤቶች የታጠረ ነው።

ከውጭ ሀገር ምርቶች ጥገኝነት ለመላቀቅ በሩሲያ ኢንጂነሮች የተሰራ በመሆኑ፣ የሀገሪቱን የቴክኖሎጂ አቅምና ልዕልና የሚወክል ኩራት ነው።

ከጥበቃው ባሻገር፣ በመኪናው ውስጥ ያሉ መሪዎች ያለምንም ረብሻ ሚስጥራዊ ውይይቶችን እንዲያደርጉ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ አለው።

እነዚህ ሁለት ተፅዕኖ ፈጣሪ መሪዎች በዚህ ታሪካዊ መኪና ውስጥ የጋራ ጉዞ ማድረጋቸው፣ "በአዲሱ የዓለም አቀፍ የፖለቲካ ሥርዓት ውስጥ አብረን እንጓዛለን" የሚል ጠንካራ የዲፕሎማሲ ቋንቋን ያስተጋባ ክስተት ሆኖ ተመዝግቧል።

"አመራሩ የመልካም አስተዳደር ችግርን መቅረፍ ዋነኛ ትኩረቱ ሊያደርግ ይገባል" ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደየሰሜን ሽዋ ዞንና የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር  ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ...
15/09/2026

"አመራሩ የመልካም አስተዳደር ችግርን መቅረፍ ዋነኛ ትኩረቱ ሊያደርግ ይገባል" ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

የሰሜን ሽዋ ዞንና የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች የ2018 እቅድ አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ውይይት እያደረጉ ነው።

በመድረኮች ላይ ተገኝተው የስራ መመሪያና ቀጣይ ተግባራት ላይ መልእክት ያስተላለፉት ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፣አመራሩ አካባቢያዊ ነባራዊ ሁኔታ ታሳቢ ያደረገ የአመራር ብቃት መፍጠርና ለህዝብ ጥያቄ በቅርብ ምላሽ የመስጠት አቅምን ማዳበር እንደሚገባ አሳስበዋል።

አመራሩ የተስተካከለ የፖለቲካ አውድ በመፍጠር ለሰላም፣ለልማትና ለመልካም አስተዳደር የተመቸ እሳቤ ማዳበርና በተግባር መፈጸም ይኖርበታል ነው ያሉት።

የህዝቡ ዋነኛ ችግር የኾነውን የጽንፈኝነት አስተሳሰብን በመታገል ምቹ ከባቢ መፍጠር ይገባል ነው ያሉት ርእሰ መስተዳድሩ በተለይም ፍላጎትን በሃይል ለማስመለስ የታጠቀ የጽንፈኝነት ሃይል ስላለ ይህን መታገል ዋነኛ ስራ መኾን አለበት ብለዋል።

ርእሰ መስተዳድሩ አክለውም በሃይማኖትና በፖለቲካ መካከል የሚፈጠርን ልዩነት እና ጽንፈኝነት በማስወገድ የጋራ ትርክት መፍጠር ይገባል። ይህ የሚሳካው ደግሞ አመራሩ ራሱን ከሃይማኖትና አካባቢያዊ ወገንተኝነት ነጻ አድርጎ ማህበረሰብን ነጻ ማውጣት ሲቻል ነው ሲሉ አሳስበዋል።

ርእሰ መስተዳድሩ በአካባቢያችን ያሉትን ሃብት ልንፈጥርባቸው የምንችላቸው ዘርፎች በመለየት ትኩረት መስጠትና ከፍጆታ የወጣና ገበያ መር የኾነ ምርት ላይ በማተኮር በራሱ ገቢ የሚተማመን ማህበረሰብ መፍጠር ይኖርብናል ሲሉ ተናግረዋል።

በገቢው የሚተማመንና በኢኮኖሚ የዳበረ ማህበረሰብ ስንፈጥር ደግሞ ጽንፈኝነትንና ሙስናን የሚጠየፍና የሚታገል ማህበረሰብ መፍጠር ይችላል ሲሉም ኢኮኖሚው በፖለቲካ አስተሳሰብ ውስጥ ያለውን ዋጋ አንስተዋል።

ርእሰ መስተዳድሩ በመልእክታቸው፣ዞኑ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ ማሳደግና ፍላጎቱን በቀላሉ ማሳካት እንዳለበት አሳስበው በየአካባቢው ያለውንና በራሱ አቅም መሰራት የሚችሉ ፕሮጀክቶችንና መሰረተ ልማቶችን የመፈጸም አቅም ሊኖር ይገባል ነው ያሉት።

ሰብዓዊ ሃብት ልማት ዋነኛ የዚህ ዓመት ትኩረት መኾኑን ያነሱት ርእሰ መስተዳድሩ፣ በተለይም ለትምህርት ዘርፉ የምንሰጠው ትኩረት ከድህነት ቀና እንድል የሚያደርግ በመኾኑ በትምህርት ሽፋንና ጥራት ላይ በመስራት ዘላቂ ሰብዓዊ ልማት ማፍራት ይኖርብናል ብለዋል።

ርእሰ መስተዳደሩ በማጠቃለያ መልእክታቸው የህብረተሰቡ የመልካም አስተዳደር ጥያቄን ለመመለስና የህግ የበላይነት በማረጋገጥ ፈጣን ምላሽ የመስጠት ልምድ የአመራሩ የብቃት ማሳያ መኾን አለበት ብለዋል።

በዚህ ዓመት በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች የአመራሩ ዋነኛ ትኩረት ከሚኾኑት መካከልም

👉አመራሩ እያንዳንዱ ተግባር በተጨባጭ እና እውነታው ምን ይመስላል የሚለውን መለየትና መገምገም፣

👉የማህበረሰቡን አገልግሎት አሰጣጥና ፍላጎት በመለየት ህሊናዊ በመኾነ እይታ መቃኘትና አዳጊ የኾነ ማህበረሰባዊ አመለካከት መፍጠር፣

👉ሀገራዊ ስትራቴጅካዊ እቅዶችን ተረድቶ እንዴት ይተግበር የሚለው ላይ ትኩረት ማድረግ እና

👉አመራሩ የመሪነት ሚናን መረዳት፣ ማህበረሰቡን መደገፍና በየደረጃው የአመራር ብቃት ማሳደግ የዚህ ዓመት ትኩረት ሊኾኑ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።

15/09/2026

የእራስህን ወገን በሀሳብ ስለተለያየህ ብቻ.." #ስኳድ" .. ብለህ እየጠራህ .. እድል ካገኘህ እንደምታጠ ፋው እየዛትክ ... እንደ ሀገር ተፃምጄ ለውጥ አመጣለህ ስትል አታፍርም ወይ 🤔

የኮማንዶ ክፍለ ጦር በማንኛውም ጊዜ የሚሰጠውን ግዳጅ ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን አሥታወቀ‼️
15/09/2026

የኮማንዶ ክፍለ ጦር በማንኛውም ጊዜ የሚሰጠውን ግዳጅ ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን አሥታወቀ‼️

ኤርትራን ወደ ሲንጋፖር የቀየረ ኢሳየስ አፈወርቂ ፥ አሁን ደሞ ትግራይን ለማልማት አብረን እንሰራለን እያለ ነው‼️ (“ፅምዶ ለሰላምና ልማት” ይላል😂)
15/09/2026

ኤርትራን ወደ ሲንጋፖር የቀየረ ኢሳየስ አፈወርቂ ፥ አሁን ደሞ ትግራይን ለማልማት አብረን እንሰራለን እያለ ነው‼️ (“ፅምዶ ለሰላምና ልማት” ይላል😂)

📌 #ኢሳያስን ያመነ ጉም የዘገነ😅❝የቀይ ባህር ደህንነት ጉዳይ የጠረፉ ተዋሳኝ ሀገራት ብቻ ጉዳይ ነው❞ እያለ በየመድረኩ ሲቦ`ተረፍ የከረመው ኢሱ ጭሱ የየመን ሁቲ ታጣቂዎች የየመን ምእራባዊ...
15/09/2026

📌 #ኢሳያስን ያመነ ጉም የዘገነ😅
❝የቀይ ባህር ደህንነት ጉዳይ የጠረፉ ተዋሳኝ ሀገራት ብቻ ጉዳይ ነው❞ እያለ በየመድረኩ ሲቦ`ተረፍ የከረመው ኢሱ ጭሱ የየመን ሁቲ ታጣቂዎች የየመን ምእራባዊ ቀይ ባህርን በመቆጣጠር የባብ አል-መንደብን መተላለፊያ ሰርጥ ለሳውዲ የንግድ መርከቦች ዝግ አድርገው ሲያበቁ በሳውዲ ላይ ተከታታይነት ያለው ጥቃት በመፈጸም ላይ ይገኛሉ።
ሳውዲ አረቢያ ከየመን የሁቲ ታጣቂዎች የተሰነዘረባትን ጥቃት ለመቀልበስ ብሎም የባብ አል-መንደብ መተላለፊያ ሰርጥን ለማስከፈት ❝ ❞ የሚል ጥሪ ለወዳጆቿ ስታቀርብ ኢሱ ጭሱ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ኦስማን ሳሌህ በኩል ‟ #ይቅርብኝ” የሚል ምላሽ ሰጥቷል - ኢሳያስን ያመነ ጉም የዘገነ !
የደደቢት ጅላን`ፎዎች ኢሳያስ ያስጠልለናል ብለው #ጽምዶ #ቅምዶ ሲሉ ይውላሉ። ጥቁር አንበሳ ተነስቶ የማይታጠፍ ክንዱን ሲያሳርፍባቸው ኢሱን ቢጠሩት አይሰማቸውም። ያኔ በማስታወቂያ ሚኒስትሩ የማነ ገ/መስቀል በኩል ‟ኤርትራ የኢትዮጵያ ግጭት በውይይት እንዲፈታ ጥሪ ታቀርባለች” የሚል መግለጫ/ማላገ`ጫ በ ❝X❞ ገጹ ይለጥፋል።
💦
ኢትዮጵያ አሰብን ጨምሮ ደቡባዊ ቀይ ባህርን በእጇ የምታስገባበት ቀን ከመቼውም ጊዜ በላይ ተቃርቧል !!

Address

Africa
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when M'r Fikre posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The School

Send a message to M'r Fikre:

Shortcuts

Share