12/05/2024
ቅዱስ ቁርዓን የማን ቃል (ንግግር) ነው?
ሱረቱ ሐ ሚም አል-ሰጅዳህ 41:2–(ይህ ቁርአን) እጅግ በጣም ርኅሩኅ በጣም አዛኝ ከሆነው (አላህ) የተወረደ ነው።
“ከአለማት ጌታ የተወረደ ነው።” (ሱረቱል አል ዋቂዐህ 80)
✔ቅዱስ ቁርአን የአላህ ንግግር (ከላመሏህ) ነው።
✔ቅዱስ ቁርአን ቃላቱንና ፍቺውን አጠቃሎ የያዘ የአላህ (ሱወ) ቃል (ንግግር) ነው::
✔ ከአላህ (ሱወ) የተወረደ (የተላለፈ) ፍጡር ያልሆነ የፈጣሪ ቃል ነው ።
ቅዱስ ቁርዓን ለእኛው ውዱ ነብይ ሙሀመድ (ሰአወ) ከአላህ (ሱወ) የተሰጠ እውነተኛ ለመሆናቸው ማረጋገጫ የሆነ ተአምር (ሙእጅዛ) ነው ::
እስከቂያማ (ትንሳኤ) ድረስም በአላህ (ሱወ) ሙሉ በሙሉ የተጠበቀ ነው :: ከቁርአን ውስጥ አንድንም ነገር የተስተባበለ ጉድለት ወይም ጭማሬ ወይም ማዛባት በጭራሽ የለበትም።
ቁርአን የአሏህ ቃል ነዉን By Dr Zakir Naik Amahric
Downlod p1Mp3▶ http://goo.gl/c0u1AE
P2 Downlod Mp3▶ http://goo.gl/9lP3rD
P1 Youtub▶ https://youtu.be/bsEMWf_dN2Y
P2 Youtub➤ https://youtu.be/XS_NTBHaBFc
ቅዱስ ቁርአን የአላህ(ሱወ) ቃል መሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም!! እንዴት ካሉም ማስረጃችን እነሆ ….
————————————–
“ከአለማት ጌታ የተወረደ ነው።” (አል ዋቂዐህ 80)
አል-በቀራህ 2:2–ይህ መጽሐፍ (ከአላህ ለመኾኑ)
ጥርጥር የለበትም፤ ለፈራህያን** መሪ ነው፡፡
(** አላህን ለሚፈሩ)
ሱረቱ አል-ሰጅዳህ 32:2–የመጽሐፉ መወረድ ጥርጥር
የለበትም፤ ከዓለማት ጌታ ነው።
“እኛ ቁርዓንን ባንተ ላይ ማውረድን እኛው አወረድነው።” (አል ኢንሣን 23)
“ያ ፉርቃን በባሪያው ላይ ለአለማት አስጠንቃቂ ይሆን ዘንድ ያወረደው(አምላክ) ክብርና ጥራት ተገባው።” (አል ፉርቃን 1)
“እኛ ቁርአኑን እኛው አወረድነው እኛም ለሱ ጠባቂዎች ነን።” (አል ሂጅር 9)
“ከአጋሪዎች አንዱ ጥገኝነት ቢጠይቅ የአላህ ቃል ይሰማ ዘንድ አስጠጋው… ” (አል ተውባ 6)
ሱረቱ አልሹዐ 26:5–ከአልረሕማንም ዘንድ፣ አዲስ
የተወረደ ቁርአን አይመጣላቸውም፤ ከርሱ የሚሸሹ ቢሆኑ እንጂ።
————————————–
“ወደ እናንተም ገላጭ የሆነ ብርሃን “ቁርዓን” አወረድን” (አል ኒሳእ 174)
መፅሀፉም ለሁሉም ነገር አብራሪ መሪም እዝነትም ለሙስሊሞች አብሳሪ ሆኖ ባንተ ላይ አወረድነው “(አል ነህል 89)
“መፅሀፉም ለሁሉም ነገር አብራሪ መሪም እዝነትም ለሙስሊሞች አብሳሪ ሆኖ ባንተ ላይ አወረድነው።” (አል ነህል 89)
“ከቁርአንም ለምእመናን መድሃኒት እዝነት የሆነ እናወርዳለን።” (አል ኢስራእ 82)
”እናንተ ሰዎች ሆይ! ከጌታችሁ ግሳጼ(ቁርዓን) በእርግጥ መጣችላችሁ።” (ዩኑስ 57)
”ሙሉ የሆነ ጥበብ በተሞላበት ቁርአን(መጣቻቸው) ግን አስፈራሪዎቹ አይብቃቁም።” (አል ቀመር 5)
ሱረቱ አል-ነምል 27:6–አንተም ቁርአንን ጥበበኛና ዐዋቂ
ከሆነው (ጌታህ) ዘንድ በእርግጥ ትሠጣለህ።
—————————————
ሱረቱ ዩሱፍ 12:3–እኛ ይህንን ቁርአን ወደ አንተ በማውረዳችን በጣም መልካም ዜናዎችን በአንተ ላይ እንተርክልሃለን፤ እነሆ ከርሱ በፊት (ካለፉት ሕዝቦች ታሪክ) በእርግጥ ከዘንጊዎቹ ነበርክ።
—————————————
”ያሲን ጥበብ በተመላበት ቁርኣን እምላለሁ።” (ያሲን 1-2)
ሱረቱ ሙሐመድ 42-2 –እነዚያም ያመኑ፣ በጎዎችንም
የሠሩ በሙሐመድ ላይም በተወረደው እርሱ ከጌታቸው ሲሆን እውነት ስለ ሆነ ያመኑ ከነርሱ ላይ ኃጢያቶቻቸውን
ያብብሳል፤ ሁኔታቸውንም ሁሉ ያበጃል።
47:9–ይህ እነሱ አላህ ያወረደውን ስለጠሉ ነው፤ ስለዚህ ሥራዎቻቸውን አበላሸባቸው።
47:26–ይህ እነሱ ለነዚያ አላህ ያወረደውን ለጠሉት በነገሩ ከፊል እንታዘዛችኋለን ያሉ በመሆናቸው ነው፤ አላህም መደበቃቸውን
ያውቃል።
—————————————
ሱረቱ አል- ረዕድ 13:1–አ. ለ. መ. ረ (አሊፍ ላም ሚም ራ)
(1) ይህች (አናቅጽ) ከመጽሐፉ አንቀጾች ናት፤ ያም ከጌታህ ወዳንተ የተወረደው እውነት ነው፤ ግን አብዛኛዎቹ ሰዎች
አያምኑም።
—————————————
“ወደ አንተም መጽሐፉን ከበፊቱ ያለውን መጽሐፍ አረጋጋጭና በእርሱ ላይ ተጠባባቂ ሲኾን በእውነት አወረድን… ”
(አል-ማኢዳህ 48)
ሱረቱ ሐ ሚም አል-ሰጅዳህ 41:2–(ይህ ቁርአን) እጅግ በጣም ርኅሩኅ በጣም አዛኝ ከሆነው (አላህ) የተወረደ ነው።
—————————————
“እናንተ ሰዎች ሆይ! ከጌታችሁ ዘንድ በእርግጥ አስረጅ መጣላችሁ ወደ እናንተም ገላጭ የሆነን ብርሃን(ቁርአንን) አውርደን።” (አል ኒሳል 174)
ሱረቱ አል-ሒጅር 15:9–እኛ ቁርኣንን እኛው አወረድነው፡፡
እኛም ለእርሱ ጠባቂዎቹ ነን፡፡
————————————–
ሩህ(የህይወት መንፈስ)ቁርዓንን አወረድን ይላል።
“እንደዚሁም ወደ አንተ ከትእዛዛችን ሲኾን መንፈስን(ቁርኣንን) አወረድን።” (አል ሹራ 52)
ሱረቱ ሁድ 11:1–አ.ለ.ረ. (አሊፍ ላም ራ፤ ይህ
ቁርአን) አንቀጾቹ በጥንካሬ የተሰከኩ፣ ከዚያም የተዘረዘሩ የሆነ መጽሐፍ ነው፤ ጥበበኛ ውስጠ ዐዋቂ ከሆነው ዘንድ
(የተወረደ) ነው።
————————————–
ሱረቱ አል-አንዓም 6:7–ባንተም ላይ በወረቀት የተጻፈን
መጽሐፍ ባወረድንና በእጆቻቸው በነኩት ኖሮ እነዚያ የካዱት ሰዎች «ይህ ግልጽ ድግምት እንጅ ሌላ አይደለም» ባሉ ነበር፡፡
————————————–
“አንቀጾቹ የተብራሩ የሆነ መፅሀፍ ነው። አረብኛ ቁርአን ሲሆን ለሚያውቁ ህዝቦች(የተብራራ) ነው። አብሳሪና አስፍራሪ ሲሆን(ተወረደ) አብዛኞዎቻቸውም ተዉት እነሱም አይሰሙም።” (አል ፋሲለት 3-4)
“እርሱ የከበረ ቁርአን ነው።” (አል ዋቂዐህ 77)
ሱረቱ አል-አሕቃፍ 46:2–የመጽሐፉ መውረድ አሸናፊ ጥበበኛ
ከሆነው አላህ ነው ::
—————————————
ሱረቱ አል-ጃሢያ 45:2–የመጽሐፉ መወረድ አሸናፊ፣ ጥበበኛ
ከኾነው አላህ ነው።
————————————–
ሱረቱ አል-አዕራፍ 7:2–(ይህ) ወደ አንተ የተወረደ መጽሐፍ
ነው፤ በደረትህም ውስጥ ከርሱ ጭንቀት አይኑር፤
—————————————
ሱረቱ አል-ፉርቃን 25:1–ያ ፉርቃንን (1) በባሪያው ላይ፣
ለዓለማት አስፈራሪ ይሆን ዘንድ፣ ያወረደው (አምላክ)፣ ክብርና ጥራት ተገባው።
—————————————-
ሱረቱ አል-ዱኻን 44:5–ከኛ ዘንድ የሆነ ትእዛዝ ሲሆን (አወረድነው) እኛ (መልክተኞችን) ላኪዎች ነበርን።
—————————————-
ሱረቱ አል-ዐንከቡት 29:48–ከርሱ በፊትም መጽሐፍን
የምታነብ በቀኝህም የምትጽፈው አልነበርክም፤ ያን ጊዜ አጥፊዎቹ በእርግጥ በተጠራሩ ነበር።
————— ————— ——–
ሱረቱ አል- አሕዛብ 33:2–ጌታህም ወደ አንተ የሚወርደውን
ተከተል፤ አላህ በምትሠሩት ሁሉ ውስጠ ዐዋቂ ነውና።
————— ————— ——–
አል-ዙመር 39:1–የመጽሐፉ መወረድ፣ አሸናፊው ጥበበኛው ከሆነው አላህ ነው።
39:2–እኛ ወደ አንተ መጽሐፉን በውነት (የተመላ) ሲሆን አወረድነው፤ አላህንም ሀይማኖትን እርሱ ብቻ ያጠራህ ሆነህ
ተገዛው።
ሱረቱ ጣሀ 20:2–ቁርአንን፣ ባንተ ላይ እንድትቸገር አላወረድንም።
20:3–ግን አላህን ለሚፈራ ሰው መገሰጫ
ይሆን ዘንድ (አወረድነው)።
20:4–ምድርንና የላይኛዎቹን ሰማያት ከፈጠረ አምላክ ተወረደ።
ሱረቱ ኢብራሂም 14:1–አ.ለ.ረ. (አሊፍ ላም ራ፤ ይህ
ቁርአን)፤ ሰዎችን በጌታቸው ፈቃድ ከጨለማዎች ወደ ብርሃን፤ አሸናፊ ምስጉን ወደሆነው ጌታ መንገድ ታወጣ ዘንድ
ወዳንተ ያወረድነው መጽሐፍ ነው።
————— ————— ——–
ሱረቱ አል ከህፍ 18:1–ምስጋና ለአላህ ለዚያ መጽሐፉን
በውስጡ መጣመምን (1) ያላደረገበት ሲኾን በባሪያው ላይ ላወረደው ይገባው።
ሱረቱ አል-ሰጅዳህ 32:2–የመጽሐፉ መወረድ ጥርጥር
የለበትም፤ ከዓለማት ጌታ ነው።
32:3–ይልቁንም ቀጠፈው ይላሉን?
አይደለም፤ እርሱ ከጌታህ ዘንድ የኾነ እውነት
ነው፤ በርሱ ከአንተ በፊት አስፈራሪ (ነቢይ)፤
ያልመጣባቸውን ህዝቦች ልታስፈራራበት
(ያወረደልህ ነው)፤ እነርሱ ሊመረምሩ
ይከጅላልና።
ሱረቱ አል-ፉርቃን 25:32 እነዚያ የካዱትም፦ ቁርአን በርሱ
ላይ ለምን በጠቅላላ አንድ ጊዜ አልተወረደም? አሉ፤ እንደዚሁ
በርሱ ልብህን ልናረጋ፣ ( ከፋፍለን አወረድነው)፤ ቀስ በቀስ
መለያየትም ለየነው።
ሰላምም ቀጥታን በተከተለ ሰው ላይ ይኹን፡፡* (ጣሃ 47)
☞
Like ☑ Comment ☑ Share ☑
12/05/2022
ውይይት‼
ዕውን ያ ሁሉን ቻይ የሆነው አንዱ አምላክ [ፈጣሪ] ለሰዎች ኃጢኣት ሲል ተሰቀለን..?‼
ሙሥሊሙ "" አምላክ [ፈጣሪ] እውን ይሞታልን?
ክርስቲያኑ ፦ አዎን! "
ሙሥሊሙ ፦ ማን ገደለው?
ክርስቲያኑ ፦ ሰዎች "!
ሙሥሊሙ ፦ ሰዎች?😳😳 ለምን? እንዴትስ ሞተ?
ክርስቲያኑ ፦ ለሰው ልጆች ኃጢአት ሲል ሰዎች ወገሩትም አሰቃይተው ሰቀሉትም ።
ሙሥሊሙ ፦ እኮ የገደሉት የፈጠራቸው ሰዎች ናቸውን?
ክርስቲያኑ ፦ አዎ !
ሙሥሊሙ ፦ እኮ ለሰዎች ኃጢአት ሲል? ሰዎች ፈጣሪያቸውን ገደሉት?😳😳
ክርስቲያኑ ፦አዎ !
ሙሥሊሙ ፦እነዛን ፈጣሪን ይዘው የገደሉትን ሰዎች ግን ማን ፈጠራቸው?
ክርስቲያኑ ፦ አምላክ (ፈጣሪ) ነዋ ።
ሙሥሊሙ ፦ ታዲያ ይህ አምላክ ፍትሃዊ ነው ትላለክ?
ክርስቲያኑ ፦ ማለት? እንዴት ?😳
ሙሥሊሙ ፦ ፈጣሪ (አምላክ) ለሰው ልጆች ኃጢያት ሲል ሰዎች ከገደሉት እና እርሱንስ(ፈጣሪን) የገደሉት ሰዎች ሌላ ኃጢአት ሰሩ ማለት አይደለም?!
ክርስቲያኑ ፦ አዎ እነርሱማ የገሃነም ናቸው"!
ሙሥሊሙ ፦ ስለዚህ አምላክ ፍትሃዊ አይደለምን ?
ክርስቲያኑ ፦ ማለት ?😳
ሙሥሊሙ ፦ አምላክ(ፈጣሪ) ለግማሹ ኃጢአት ሲሞት ግማሹን ሐፂያት ውስጥ ጨመረ "! 😊 ግን ከዚህ ሁሉ ኃጢአታቸውን መማር እየቻለ ፈጣሪ በሰዎች እጅ ተይዞ፣ ተደብድቦ፣ ተሰቃይቶ፣ ተሰቅሎ መገደሉ ለምን አስፈለገው !?
መፍጠር የአምላክ ባህሪ መፈጠር ደግሞ የሰው ባህሪ መወለደ የሰው ባህሪ ፍጡርን በማህጸን ውስጥ መፍጠር የአምላክ ባህሪ ሆኖ ሳለ አምላክ ተወለደ አምላክ ሞተ አምላክ ደሙን አፈሰሰ ማለት ምነኛ ከፋ…!! አምላኬ ሆይ ከሚሉህ ሁሉ የጠራህ ነህ ።
11/05/2022
እኔፕሮቴስታንት ነኝ እየሱስን ስለምወደው እስልምናን ከተቀበልኩ እንዳላጣው እሰጋለሁ ምን ትሉኛላችሁ?
ሙስሊም:-
"እስልምናን ስትቀበል እየሱስን አታጣም፤ (እስልምና ውስጥ) ስለ እየሱስ ትክክለኛ ማንነት እውነትን በግልፅ ትማራለህ!"
ለአምላክ መልእክተኞች (ነብያት) ... አብረሃም፣ ሙሴ፣ እየሱስ፣ መሀመድ (ዓለይሂሙ ሰላም) የነብያትን ደረጃ ሰጥተህ ብቻውን የፈጠረህን አንድ አምላክ ታመልካለህ...
የእየሱስ ክርስቶስ እናት የሆነችንውን ቅድስት ድንግል ማርያምን በኢስላም ውስጥ ያላትን ክብር ትሰጣለህ (ከቁርኣን 114 ምዕራፍ መካከል 19ኛው ምዕራፍ የማርያም ምዕራፍ ይባላል)... እስልምና የክርስቶስ ጠላት አድርገው ሚሰብኳችሁ ስህተት ነው፤ እስልምና ለእየሱስም ሆነ ለእናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም አክብሮት አለው።
05/05/2022
እየሱ'ስ ክርስቶ'ስ አምላክ #ላለመሆኑ 10 ወሳኝ ማስረጃዎ'ች‼
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
1- እየ'ሱስ ክር'ስቶስ አልነበረም፡፡ ‼
እንደሚታወቀው አምላክ ሁሉን አዋቂ ነው፡፡ ከዕውቀቱ የሚደበቅ ምንም ነገር የለም፡፡ እ'የሱስ ክርስ'ቶስ ግን እንደ መፅሀፍ "ቅዱ'ስ" ገለፃ ይህንን መስፈርት አያሟላም፡፡
" ስለዚያች ቀን ወይም ስለዚያች ሰዓት ግን የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ #ልጅም [ኢየሱስ ክርስቶስም] ቢሆን ከአባት [ከእግዚአብሔር] በቀር ።"
(የማርቆስ ወንጌል 13:32)
2- እየሱስ ክርስቶስ አንዲትም ጊዜ ብሎ አያቅም‼
በብሉይ ኪዳን እግዚአብሄር እጅግ ብዙ ቦታዎች ላይ አምላክነቱን ሲያውጅና ሲገልፅ እንመለከታለን!
እየሱስ ክርስቶስ ግን በተቃራኒው ስለዚህ ጉዳይ ትንፍሽ አላለም፡፡
እስኪ ከብሉይ ኪዳን ለአብነት እንመልከት‼
" እግዚአብሔርም አለው። ፤ ብዛ፥ ተባዛም፤ "
(ዘፍጥረት 35:11)
" አለውም። የአባቶችህ አምላክ እግዚአብሔር እኔ ነኝ፤ ወደ ግብፅ መውረድ አትፍራ፥ በዚያ ትልቅ ሕዝብ አደርግሃለሁና።"
(ኦሪት ዘፍጥረት 46:3)
"እግዚአብሔርም ሙሴን አለው። የእስራኤልን ልጆች ማንጐራጐር ሰማሁ። ወደ ማታ ሥጋን ትበላላችሁ፥ ማለዳም እንጀራን ትጠግባላችሁ፤ እኔም እግዚአብሔር አምላካችሁ እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ በላቸው። "
(ኦሪት ዘጸአት 16:11,12)
" ከግብፅ ምድር ከባርነት ቤት ያወጣሁህ እግዚአብሔር ። "
(ኦሪት ዘጸአት 20:2)
3- እየሱስ በአዲስ ኪዳን የሰው ልጅ ተብሎ ተጠርቷል‼ እራሱ መፅሀፍ "ቅዱስ" እንደሚነግረን ደግሞ ይነግረናል‼
" ኢየሱስም። ለቀበሮዎች ጉድጓድ ለሰማይም ወፎች መሳፈሪያ አላቸው፥ ለሰው ልጅ ግን ራሱን የሚያስጠጋበት የለውም አለው።"
(የማቴዎስ ወንጌል 8:20)
" ነገር ግን በምድር ላይ ኃጢአትን ያስተሰርይ ዘንድ ለሰው ልጅ ሥልጣን እንዳለው እንድታውቁ፥ በዚያን ጊዜ ሽባውን። ተነሣ፤ አልጋህን ተሸከምና ወደ ቤትህ ሂድ አለው።"
(የማቴዎስ ወንጌል 9:6)
http://goo.gl/l9WyYf https://goo.gl/6DMB83
" የሰው ልጅ የሰንበት ጌታ ነውና።"
(የማቴዎስ ወንጌል 12:8)
" ለደቀ መዛሙርቱ። የሰው ልጅ በሰው እጅ ይሰጥ ዘንድ አለውና እናንተ ይህን ቃል በጆሮአችሁ አኑሩ አለ።"
(የሉቃስ ወንጌል 9:44)
ሌላ ቦታ ባይብልን ስናነብ ደግሞ የሰው ልጅ መታመን እንደሌለበት ይነግረናል፡፡
(መዝሙረ ዳዊት ምዕ. 146)
----------
1፤ ሃሌ ሉያ። ነፍሴ ሆይ፥ እግዚአብሔርን አመስግኚ።
2፤ በሕይወቴ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ፤ በምኖርበት ዘመን ሁሉ ለአምላኬ እዘምራለሁ።
3፤ ማዳን በማይችሉ በሰው ልጆችና በአለቆች አትታመኑ።
4- እየሱስ ክርስቶስ የነበረው ስልጣንና ሀይል የእርሱ አልነበረም፡፡‼
✔ " ኢየሱስ አብ ሁሉን በእጁ እንደ ሰጠው ከእግዚአብሔርም እንደ ወጣ ወደ እግዚአብሔርም እንዲሄድ አውቆ፥"
(የዮሐንስ ወንጌል 13:3)
✔ " እኔ ከራሴ አልተናገርሁምና፤ ነገር ግን የላከኝ አብ እርሱ የምለውን የምናገረውንም ትእዛዝ ሰጠኝ።"
(የዮሐንስ ወንጌል 12:49)
✔" እኔ ከራሴ አንዳች ላደርግ አይቻለኝም፤ እንደ ሰማሁ እፈርዳለሁ ፍርዴም ቅን ነው፥ የላከኝን ፈቃድ እንጂ ፈቃዴን አልሻምና።"
(የዮሐንስ ወንጌል 5:30)
✔ " ስለዚህ ኢየሱስ መለሰ እንዲህም አላቸው። ትምህርቴስ ከላከኝ ነው እንጂ ከእኔ አይደለም፤"
(የዮሐንስ ወንጌል 7:16)
Like & Share ይቀጥላል .......
16/02/2022
!
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
3፥19 አላህ ዘንድ የተወደደ ሃይማኖት ኢሥላም ብቻ ነው፡፡ إِنَّ الدِّينَ عِندَ اللَّهِ الْإِسْلَامُ
ፕሮቴስታንት፦ "እምነት እንጂ ሃይማኖት አያድንም" የሚል መፈክር አላቸው፥ ከፕሮቴስታንት የተሃድሶ አምስቱ የብቸኝነት መፈክር አንዱ "መዳን በእምነት ብቻ"sola fide" የሚል ነው። እኛም እንደ ሙሥሊምነታችን እውነት ሃይማኖት አያድንምን? ለሚለው ጥያቄ ምላሽ ኢንሻሏህ እንሰጣለን።
"ዲን" دِين የሚለው ቃል "ዳነ" دَانَ ማለትም "ሃይመነ" "ደነገገ" "ፈረደ" "በየነ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ሃይማኖት" "ፍትሕ" "ፍርድ" "ሕግ" "መርሕ"doctrine" ማለት ነው፦
2፥256 "በሃይማኖት" ማስገደድ የለም፡፡ لَا إِكْرَاهَ فِي الدِّينِ
1፥4 "የፍርዱ" ቀን ባለቤት ለኾነው፡፡ مَالِكِ يَوْمِ الدِّينِ
12፥76 አላህ ባልሻ ኖሮ በንጉሡ "ሕግ" ወንድሙን ሊይዝ አይገባውም ነበር፡፡ كَانَ لِيَأْخُذَ أَخَاهُ فِي دِينِ الْمَلِكِ إِلَّا أَن يَشَاءَ اللَّهُ
እነዚህ አናቅጽ ላይ "ሃይማኖት" "ፍርድ" "ሕግ" ለሚለው የገባው ቃል "ዲን" دِين መሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል፥ ዲን የእምነት እሴት፣ የእምነት አንቀጽ እና የሥነ-ምግባር ግብዓት ነው። ዲን ምእመናንን ወንድማማች የሚያደርግ መርሕ ነው፦
9፥11 ቢጸጸቱም፣ ሶላትንም ቢሰግዱ፣ ዘካንም ቢሰጡ "የሃይማኖት ወንድሞቻችሁ" ናቸው፡፡ فَإِن تَابُوا وَأَقَامُوا الصَّلَاةَ وَآتَوُا الزَّكَاةَ فَإِخْوَانُكُمْ فِي الدِّينِ
49፥10 "ምእመናን ወንድማማቾች ናቸው"፡፡ إِنَّمَا الْمُؤْمِنُونَ إِخْوَةٌ
"አኽ" أَخ ማለት "ወንድም" ማለት ሲሆን "ኡኽት" أُخْت ማለት ደግሞ "እኅት" ማለት ነው፥ "ኢኽዋህ" إِخْوَة ወይም "ኢኽዋን" إِخْوَان ለሁለቱም ብዜት ሆኖ የሚያገለግል ቃል ነው። ዲን ማለት የእምነት መርሕ መሆኑ ካየን ዘንዳ ይህም ዲን ዲኑል ኢሥላም ነው፦
3፥19 አላህ ዘንድ የተወደደ ሃይማኖት ኢሥላም ብቻ ነው፡፡ إِنَّ الدِّينَ عِندَ اللَّهِ الْإِسْلَامُ
3፥85 ከኢሥላም ሌላ ሃይማኖትን የሚፈልግ ሰው ፈጽሞ ከእርሱ ተቀባይ የለውም፡፡ እርሱም በመጨረሻይቱ ዓለም ከከሳሪዎቹ ነው፡፡ وَمَن يَبْتَغِ غَيْرَ الْإِسْلَامِ دِينًا فَلَن يُقْبَلَ مِنْهُ وَهُوَ فِي الْآخِرَةِ مِنَ الْخَاسِرِينَ
"ኢሥላም" إِسْلَام የሚለው ቃል "አሥለመ" أَسْلَمَ ማለትም "ታዘዘ" "ተገዛ" "አመለከ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "መታዘዝ" "መገዛት" "ማምለክ" ማለት ነው፥ አሏህ ዘንድ ከዲኑል ኢሥላም ሌላ ሃይማኖትን ተቀባትነት የሌለው እና በመጨረሻይቱ ዓለም የሚያከስር ነው። አምላካችን አሏህ ለኢብራሂም፦ "አሥሊም" أَسْلِمْ ሲለው እርሱም፦ "አሥለምቱ" أَسْلَمْتُ አለ፦
2፥131 ጌታው ለእርሱ ”ታዘዝ” ባለው ጊዜ መረጠው፡፡ ለዓለማት ጌታ ”ታዘዝኩ” አለ፡፡ إِذْ قَالَ لَهُۥ رَبُّهُۥٓ أَسْلِمْ ۖ قَالَ أَسْلَمْتُ لِرَبِّ ٱلْعَٰلَمِينَ
22፥34 አምላካችሁም አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ ለእርሱም ብቻ "ታዘዙ"! ለአላህ ተዋራጆችንም አብስራቸው፡፡ فَإِلَـٰهُكُمْ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ فَلَهُ أَسْلِمُوا ۗ وَبَشِّرِ الْمُخْبِتِينَ
"አምላካችሁም አንድ አምላክ ብቻ ነው" የሚለው ኃይለ-ቃል ይስመርበት! በቀጣይ "ታዘዙ" ለሚለው ቃል የተቀመጠው "አሥሊሙ" أَسْلِمُوا ነው፥ ስለዚህ አንዱን አምላክ በብቸኝነት መታዘዝ፣ መገዛት፣ ማምለክ "ኢሥላም" ይባላል።
"ኢማን" إِيمَٰن የሚለው ቃል "አሚነ" أَمِنَ ማለትም "አመነ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "እምነት" ማለት ነው፥ የምናምነው ደግሞ ዲናችን ላይ የተቀመጠውን መርሕ ነው እንጂ ጣዖትን እኮ እንክዳለን፦
2፥256 “በጣዖትም የሚክድ እና በአላህ የሚያምን ሰው ለእርሷ መበጠስ የሌላትን ጠንካራ ዘለበት በእርግጥ ጨበጠ”፡፡ فَمَن يَكْفُرْ بِالطَّاغُوتِ وَيُؤْمِن بِاللَّهِ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَىٰ لَا انفِصَامَ لَهَا
የምናምነው የምናውቀውን ነው፥ የምናውቀው ደግሞ ከአሏህ ዘንድ የመጣውን መርሕ ነው። "ኢማን እንጂ ዲን አያድንም" የሚሉ ፕሮቴስታንቶች ሃይማኖት የእምነት መርሕ መሆኑን በቅጡ ስላልተረዱት ነው፥ ሃይማኖት ሥርወ-እምነት ነው። "ዶግማ" δόγμα ማለት "አንቀጸ-እምነት"creed" ማለት ሲሆን ያለ ዶግማ እምነት የማይታሰብ ነው፥ ስለዚህ ዲኑል ኢሥላም ድብን አድርጎ ያድናል፦
3፥103 የአላህን ገመድ ሁላችሁም ያዙ! አትለያዩም። ጠበኞችም በነበራችሁ ጊዜ በእናንተ ላይ የዋለውን የአላህን ጸጋ አስታውሱ! በልቦቻችሁም መካከል አስማማ፥ በጸጋውም ወንድማማቾች ኾናችሁ፡፡ በእሳት ጉድጓድ አፋፍም ላይ ነበራችሁ፥ ከእርስዋም አዳናችሁ፡፡ እንደዚሁ ትመሩ ዘንድ አላህ ለእናንተ አንቀጾቹን ያብራራል፡፡ وَاعْتَصِمُوا بِحَبْلِ اللَّهِ جَمِيعًا وَلَا تَفَرَّقُوا ۚ وَاذْكُرُوا نِعْمَتَ اللَّهِ عَلَيْكُمْ إِذْ كُنتُمْ أَعْدَاءً فَأَلَّفَ بَيْنَ قُلُوبِكُمْ فَأَصْبَحْتُم بِنِعْمَتِهِ إِخْوَانًا وَكُنتُمْ عَلَىٰ شَفَا حُفْرَةٍ مِّنَ النَّارِ فَأَنقَذَكُم مِّنْهَا ۗ كَذَٰلِكَ يُبَيِّنُ اللَّهُ لَكُمْ آيَاتِهِ لَعَلَّكُمْ تَهْتَدُونَ
ከእሳት ጉድጓድ ተንጠልጥሎ ለመውጣት የሚያስችል ብቸኛው የአሏህ ገመድ ዲኑል ኢሥላም ብቻ ነው፥ ከእሳት ጉድጓድ አፋፍ ላይ ሳለን አድኖ በሃይማኖት ወንድማማቾች አርጎናል። ሱመ አል-ሓምዱ ሊሏህ!
አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ ወሒድ
30/08/2021
ኢስላም ማለት ምን ማለት ነው?
- ኢስላም ማለት አላህን እንድና ብቸኛ በማድረግ መታዘዝና የእሱን ትእዛዝ በማክበር መገስገስ
ሲሆን እንዲሁም ከሽርክ መራቅ ነው፡፡
አላህ (ሱ.ወ) በሱረቱል በቀራህ ቁጥር 112 ላይ
እንዲህ ይለናል፡-
(“እንደውም፤ እርሱ በጎ ሰሪ ሆኖ ፊቱን ለአላህ የሰጠ (ፍጹም ታዛዥ የሆነ) ሰው፤ ለርሱ በጌታው ዘንድ ምንዳው አለው፤ (በእንዲህ አይነቶቹ ሰዎችም) በነሱም ላይ ፍርሃት የለባቸውም
እነሱም አያዝኑም” ይለናል፡፡
30/08/2021
ኢስላምን ከተቀበልክ እየሱስንም አታጣም!
ለብዙ ሰዎች ሙስሊሞች በዒሳ (ኢየሱስ) (ዐ.ሰ) ማመናቸው ይደንቃቸዋል። አንድ ሙስሊም በዒሳ (ዐ.ሰ) ነብይነት እስካላመነ ድረስ ፈፅሞ ሙስሊም ሊሆን አይችልም። ኢየሱስ (ዐ.ሰ) ከአላህ ክቡር ነቢያት አንዱ ነበር። ቁርዓንም ዒሳን (ዐ.ሰ) መልካም በሆኑ ስሞች አውስቶታል። አንዳንዴ ዒሳ (ዐ.ሰ) በሌላም ቦታ አል-መሲህ (ክርስቶስ) አንዳንዴም የመርየም ልጅ በማለት ጠርቶታል። ሁሉም ሙስሊም ያከብረዋል፤ ይወደዋል፤ ያልቀዋል። ተመልከቱ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ የዓለማችን ሙስሊሞች ዒሳ በሚለው ስያሜ መጠራታቸው ያስደስታቸዋል። እንዲሁም በብዙ ሺዎች የሚገመቱ ሙስሊም ሴቶችም መርየም በሚለው በኢየሱስ እናት ስም መጠሪያቸውን በማድረጋቸው ይኮራሉ።
ቁርኣን እንደ ወንጌል ወይም እንደ አዲስ ኪዳን መልዕክት ስለኢየሱስ ብቻ አያወራም። ቁርዓን ጠቅላይ መልዕክት ነው። በተብራራ ሁኔታ ስለፈጣሪ አንድነትና ብቸኝነት፣ ፈጣሪን በብቸኝነት መገዛት እንደሚገባን ይተነትናል። ስለአብዛኞቹ የፈጣሪ ነቢያትና መልዕክተኞችም ያወራል። ከዚህ ሁሉ በተጨማሪ ስለ ኢየሱስ (ዐ.ሰ) ድንቅ እውነታዎችም ጠቅሷል። እናቱ መርየም ንፁህና ቅድስት የአላህ አገልጋይ ነበረች። አንድ ወቅት የአላህ መልኣክ ወደ ርሷ ዘንድ በመምጣት ልጅ ያበስራታል። መርየም ከማንም ወንድ ጋር ግንኙነት ሳይኖራት ከአላህ ዘንድ በሆነ “የይሁን ቃል” ወደዚህች ምድር ይመጣል። ልጁም በተዓምራዊ ውልደት ይወለዳል። ይህ ተዓምራዊ ውልደት ሙስሊሞችንና ክርስቲያኖችን በተለያየ ጎራ አሰልፏቸዋል።
እኛ ሙስሊሞች ለነቢያት በሚሰጥ የፈጣሪ ተዓምር እናምናለን። ሙሳ/ሙሴ (ዐ.ሰ) በዘንጉ (ወደ እባብ የምትቀየር) የተጻራሪዎቹን ጠንቋዮች ሁሉ እባብ አልዋጠም? በብትሩ የቀይ ባህር ለሁለት አልከፈለም? ይህ ተዐምር ነው ብለን ከተቀበልን ለምን የዒሳ (ኢየሱስ) (ዐ.ሰ) ውልደትን ልዩ እናደርገዋለን? አላህ የዒሳን (ኢየሱስ) (ዐ.ሰ) አወላለድ እሱ በሻው መልክ ይሆን ዘንድ ፈለገ፤ ፈፀመውም! ወደራሱ ወደ ኢየሱስ ስንመለስ፣ የርሱ ዘመን ሰዎች መለኮታዊውን ኃይል የዘነጉበት ወቅት ነበር። ስለሆነም፤ ሰዎችን ወደ መለኮታዊው ኃይል ለመጥራት ከሞት ሰዎችን አላስነሳምን? የታወሩትን አይናቸውን አላበራምን? የስጋ ደዌ የያዛቸውን አልፈውስምን? ይህ ተዓምር ከአላህ ዘንድ የተሰጠ ድንቅ ስጦታ ከሆነ፣ የርሱን ተዐምራዊ ውልደት እንደሌላው ተዓምር በተዓምርነት መቀበሉ ምኑ ላይ ይከብዳል? ኢየሱስ የተለያዩ ተዓምራትን ከማሳየቱ በላይ በወቅቱ ለህዝቦቹ ስለሰማያዊው ኃይል እያስተማረ ነበር። ቁርኣንም እነዚህን ሁሉ ተዓምራት በፈጣሪ ፍቃድ ብቻ የተፈጸሙ እንጂ ሌላ እንዳልሆኑ በጽኑ ያስረዳል።
የኢየሱስ መልዕክት እንደሌሎቹ ነቢያቶች ሁሉ የተውሂድ (አላህን በብቸኝነት ማምለክ) ጥሪ ነበር። እንዲሁም፤ ሰዎችን የመልካም ሥነ-ምግባር ባለቤት እንዲሆኑ ለሌሎች እንዲያዝኑና እንዲራሩ ጥሪ አድርጓል። ዒሳ ህዝቦቹ ከፈጣሪ ትዕዛዝ በስተጀርባ ያለውን ሰማያዊ ኃይልና ክብር ይረዱ ዘንድ በፅኑ ታግሏል።
ግና ዒሳ በህዝቦቹ አልተከበረም ተናቀ፣ ተገፋ፣ ተዋረደ። ይባስ ብለውም ሊሰቅሉት እና ሊገሉት ተስማሙ። እዚህ ላይ ሁለተኛው የሙስሊሞችና የክርስቲያኖች በዒሳ ላይ ያላቸው ልዩነት ይመጣል። ክርስቲያኖች ዒሳን ተሰቅሏል ብለው ሲያምኑ ሙስሊሞች ግን ይህን ሀሳብ አንቀበልም። መልሱንም ክርስቲያኖች ከራሳቸው መፅሀፍ ይፈልጉ ዘንድ እንጠይቃለን። ተመልከቱ፣ ኢየሱስ የሞትን ፅዋ ያነሳለት ዘንድ ጌታውን እንደተማፀነ ከጠላቶቹ ይታደገው ዘንድም ፈጣሪውን እንደለመነ በመፅሀፍ ቅዱስ ማርቆስ ወንጌል ምዕራፍ 14 ቁጥር 36 እና በሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 22 በቁጥር 42 በሚገባ ተቀምጧል። ታዲያ የነቢያቱን ልመና የማይመልሰው ፈጣሪም ልመናውን ተቀበለው። ከሴረኞቹ ሴራ፣ ከጠላቶቹ ደባ ታደገው። በተዐምር ይወለድ ዘንድ ያስቻለው ፈጣሪ እርሱን ከመሰቀል ማዳን ያቅተዋልን? በፍፁም! ወደ ሰማይም አነሳው (ቁርዓን አል-ኒሳእ 4÷157-158ን ይመልከቱ)።
ከዚህ ክስተት በኋላም የኢየሱስ የመልዕክተኛነት ሚና አይጠናቀቅም። ሙስሊሞች ዒሳ (ዐ.ሰ) ወደፊት ተመልሶ ወደ ምድር እንደሚመጣና ፍትህና ነፃነትን ለማስፈን እንደሚታገል እናምናለን። ከእርሱ ጠላት ከሆነው ደጃልም ጋር እንደሚዋጋና ሁሉን ሰይጣናዊ አመለካከት አስወግዶ ሰላምን እንደሚያወርድ ቀናተኛውን መንገድ እንደሚያስይዝ እናምናለን።
ያኔ እውነተኛ የኢየሱስ ተከታዮች ድልን ያገኛሉ። ያልተገባውን ደረጃ የሰጡት ኃይሎች ሁሉ ይዋረዳሉ። ይከስማሉ። ሰው ነውና ከዚያም የቆየውን ቆይቶ እንደማንኛውም ሰው ይሞታል። ይቀበራልም።
30/08/2021
አሰላሙ አሌይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱህ